tg-me.com/Ethiokene/1953
Last Update:
" " " " ኢየሱስ ማን ነው?" " " "
❖ ❖ ❖
"እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ?"
(የማቴዎስ ወንጌል 16:15)
ይሄ ጥያቄ ከክርስቶስ ለሐዋርያቱ የቀረበ ቢሆንም ህያው ሆኖ ይሰራልና ለእኛም የተጠየቀ ነው!
ስለዚህ እናንተ ክርስቶስን ማን እንደሆነ ትላላችሁ? የሚለውን ጥያቄያችንን ለልባችሁ በመተው በዚህ ተከታታይ ፅሁፍ የኢየሱስ ክርስቶስን ማንነት ከመጽሐፍ ቅዱስ እና ከኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ አንጻር እንማማራለን።
ኢየሱስ ክርስቶስ የክርሰትናችን መስራች የሃይማኖታችንም ራስ በመሆኑ እርሱን በሚገባ ማወቅ ከእኛ ከክርስቲያኖች ይጠበቃል። እርሱን ማወቃችንም ለሚከተሉት ዋና ዋና ተግባራት ይረዳናል።
1. እርሱን አውቀን በህወታችን ያለውን ድርሻ ተረድተን ለእርሱ እንድንታዘዝና በአግባቡ እንደናገለግለውና እንድናመልከው
2. የምናውቀውን ለማያውቁትና ላልተረዱት በሚገባ ለማስረዳትና ወደ እውነተኛው የክርስቶስ ማንነት እንዲመጡ ለማድረግ
3. በዘመናች ኢየሱስ ክርስቶስን በተመለከተ ሰዎች ያላቸው አስተሳሰብ አራምባና ቆቦ ስለሆነ ጥያቄዎችንም ስለሚጠይቁን ለእነርሱ መልስ ለመስጠት ነው።
4- ዋናው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ የዘለዓለም ህይወት ነው!! የሐ17-2፤4
ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በተመላለሰበት ጊዜ ሰዎች አውቀውት ተረድተውት እንደሆነ ይጠይቅ ነበር። ለምሳሌ በፊሊጶስ ቂሳርያ ሐዋርያቱን ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደሆነ ይሉታል ብሎ ጠይቋቸው ነበር። ሐዋርያቱም ክብር ይግባውና ሰዎች የሚሉትን ተርከውለታል ።ማቴ 16፡18፤ማር 8 ። በዚያ ዘመን የሚኖሩ ሰዎች ክርስቶስን ኤልያስ ነው፤ሙሴ ነው፤ ዩሐንስ ነው፡ ኤርሚያስ ነው ከነዚህም ካልሆነ ከነቢያት አንዱ ነው ይሉ ነበር። ሌሎቹም
ጋኔል አለበት ብለውታል የሐ 10፤20 ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የነቢያት አምላክ ነበር ሰዎች ባይረዱትም ቅሉ።
ሌሎቹም ካስተማራቸው ትምህርት የተነሳ ይህ ማን ነው የጸራቢው የየሴፍ ልጅ የማርያምስ ልጀ አይደለምን? ወንድሞቹ .. እህቶቹም በእኛ ዘንድ አይደሉምን? እያሉ ተሰነካከሉበት።ሉቃ 4፤16-22
ሆኖም ሁሉም ባያውቁትም ሐዋርያቱ ግን በሚገባ ተረድተውት ነበር ለዚህ ነው ሐዋርያው ቅዱሰ ጴጥሮስ አንተ የህያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ የመለሰው። ቅዱሰ ጴጥሮስም አንተ የህያው እግዚአብሔር ልጀ ነህ በማለቱ ብጹዕ ተባለ፤የቤተ ክርስቲያን አለት እንዲባል ሆነ።
ወገኖቸ በዛሬው ጊዜ ኢየሱስን አንዱ ፍጡር/ነብይ/ ሌላው መልአክ ሌላም ሌላም እያሉ ይሳለቁበታል በእርግጥ እኛ አውቀነው ይሆንን?
ለመሆኑ ይህ ኢየሱስ ማን ነው?
ኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢት ሳያናግር ሱባኤ ሳያስቆጥር እንዲሁ ከሰማያት የወረደ አይደለም። ይልቁንም ትንቢት አናግሮ ሱባኤ አስቆጥሮ ከሰማየ ሰማያት ወረደ እንጂ። ኢየሱስ ክርስቶስ ሱባኤ አስቆጥሮ ቢመጣም እንኳን ሱባኤውን እንቆጥራለን የሚሉ
አይሁድ ማወቅ አልቻሉም እርሱ የመጣው በደካማ ስጋ ነበርና።
ዛሬም ሰዎች ክርስቶስ በደካማ ስጋ መምጣቱን ተመልክተው ብዙዎች እርሱን በሚገባ ለማመንና ለማዎቅ አቃታቸው። ክብር ለእርሱ ይሁንና እርሱ ኢየሱስ ማን ነው። እርሱ የማሰናከያው ድንጋይ እርሱ የማዕዘኑ ድነጋይ፤ ያ ከአለት የፈሰሰው እና በጥም
የነበሩትን በበረሃ የተቃጠሉትን ያረካው ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ነው?
ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን፦
ይቀጥላል............
BY ✝ኢትዮ ግእዝ ወ አማርኛ ቅኔ እና ሌሎችም
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/Ethiokene/1953