Telegram Group & Telegram Channel
"ርዕሱን ለአድማጭ"
ርዕሱ ነው
( አምባዬ ጌታነህ )

እኔ የአንቺ ደሐብ-ብኩን ደግ አፍቃሪ፣
ለክብረሽ መግለጫ - ፊደልሽን ቆጣሪ፣
እየተቅለሰለስኩ በልጅሽ ፊት ስኖር፣
ከማዘን በስተቀር ስቄ አላቅም ከምር።
ያም ለዛ ያም ለዛ ሲያጋድል እያየሁ፣
በጊዜ ዳኛ ላይ ፍትህ እየተራብሁ፣
ሁሌ እንዳጉተመተምሁ
'ልጅ አሳድግ ብየ
ካገር እኖር ብየ
ለባሻ ዳርኩለት ሚስቴን 'ህቴ ብየ።'
እንዳለው ገበሬ፣
አለሁኝ እንዳለሁ
ግፍ ሆኖብኝ ክብሬ።

አባት ማጣት ሀዘን - እናት ማጣት ህመም፣
ሆኖ እንደ እግር እሳት እልፍ አመት ቢፈጅም፣
በተበዳይ ልብ ውስጥ ለምፅ እንደሚያሳርፍ ገዳይ አውቆ አያቅም፣
እኔ ያለ ወላጅ መቅረቴ አያመውም።

ሰማይ የግፍ እምባ ሊጥል አቀርዝዟል፣
ጋራ ሸንተረሩ በዝምታ ነግሷል፣
ሜዳ ወንዛ ወንዙ ቅጠሉ ጠንዝሏል፣
እናት ሞቅ አጥልቃ፣
ቁርንጮዋን ታጥቃ፣
ፊቷ ተነጫጭቷል፣
አባት ወደ ማታ ባዘን አጎንብሷል፣
የእኔም የነገ እጣ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ለዛሬ ያለምነው ቅዠት ሲሆን ተስፋ፣
አንተ የፍጥረት አምላክ
የምህረት ዝናብህን ባጥል እንኳ አካፋ።
ነፃ በሆነች ምድር ነፃ አውጪዎች ሞልተው ነፃ ህዝብ ጠፋ።
እኒህ ነፃ አውጪዎች
የለውጡ አምበሳዎች
በቀን አስር ጊዜ ' እመኑን 'የሚሉን፣
ከምናየው እውነት የተፃረረውን
' መሲህ ነን ' የሚሉን
ከእመኑን ባሻገር እንድናምን 'ሚሹት ውሸቱ ምን ይሆን፣

ባለሁለት ወንበር ምቾት ካልተሰማኝ፣
የምለውን ሰምቶ ሰርቶ ካልታዘዘኝ
አባወርነቴን ከተፈታተነኝ
የእሱ መኖር ለእኔ ..
መሄጃ መቆሚያ ማረፊያ ካሳጣኝ፣
እንዴት መላ አላስብ፣
እንዴት ሴራ አልሸርብ
የምን እያቀፉ እንደ ልጅ ማባበል፣
ሳለ ብልህ ዘዴ
በመፈንቅለ ስም መሪነትን መግደል።

እንዲህ ነው እንግዲህ የኛ ዘመን ጣጣ፣
የየዋህ እስትንፋስ የንፁህ እድል እጣ።
ያደለው በሰው ልብ እንደተናፈቀ በክብር ይሞታል፣
ያለደለው ደግሞ የራሱን ቁም ሙቶ ሊገድል ይኖራል፣
ምንድን ነው ሰው መሆን ያዘነ ማስመሰል፣
በውስጥ እየሳቁ ለቅሶ ምን ያደርጋል፣
ፍረድ አንተ ጌታ...
የኃጢያት እልፍኜን
ና ደብድብ ጣራዋን
ወየ ኡኡ ብየ ላቅልጠው ዋይታየን
ቅጣኝ ለክህደቴ
አርገው እውነት የምር የውሸት ለቅሶየን።

እናም በኔ ዘመን...
የእውነት ዘውድ ተጭኖ የሚታየው አሁን፣
ቀዳዳን በር አረጎ ሚያይ ልዩነትን
አንድነትን ትቶ የሚስብክ ጥልን።
በአንድ መንጋ ሚሄድ፣
ያለ ሀሳብ ሚነጉድ
ግን
እስከየት ድረስ ነው?
ጎዳናው ሚያዘልቀው
እስከ መቼ ድረስ በጎጥ አንድ መንገድ፣
በንፁሃን ደም ላይ..
ንፁሃንን ከሶ እያሰሩ መሄድ።
ነውስ?
'ውሻ በቀደደው ጅብ ሠፍቶ ይገባል
ፍየል በግ ቢያጣ እንኳ
ቋንጣውን ሸምጥጦ ይሮጣል እንዲባል
ሆነ በቃ እንግዲህ
የዚች አገር እጣ በተራ መበደል?!

ተው
እንተው
በዳይ ከተበዳይ እኩል ፍትህ ካለ ካልሰከነ ነገር፣
ቤትን ካላቆመ
አንደኛው ጭራሮ ሌላው ሆኖ ማገር፣
ምስጥ የበላት ጎጆ ትመስላለች ሀገር።
"
' ? '
በበረሀ ጋመን ጠውልጎ ያልረባው፣ማውጣት የተሳነው የማህፀንሽ ፍሬ፣
ለአርባ አምስት አመታት ንጉሥ ያልወጣብሽ ምን ኀጥያት ሰርተሽ ነው ንገሪኝ ሀገሬ?

ምንዱባን ኢትዮጵያ - ምትለምኝ ሰጥተሽ፣
ጥበብሽ ሳይቆሽሽ
የምታጥቢ ፈተሽ
ሩህሩኋ የኔ
ጥጥ ፈታይዋ እናቴ፣
ምን ልብ ነው ያለሽ
እኔ እየጠላሁሽ
አንቺ ምትሳሽልኝ ንገሪኝ በሞቴ?

' መደምደሚያ '
በአንድ ቋንቋ ዘየ የሰራነው መንደር፣
ምን ብንኩራራበት አይሆነንም ሀገር።
ይብቃን መጋደሉ፣
ይብቃን መላቀሱ፣
መርገምት ነው ይሄ
እንፀልይ ወደ እርሱ።
ደግሞ
ያሻው ቢከፋኝም፣
ያሻ ብቀየምም፣
ወንድምነትክን ግን
ለሰከንድ አልፍቅም
ሲነኩህ ያመኛል ይሰማዋል ጎኔ፣
ይህ ሁሉ ግፍ ይቁም በአንተ በእሷ በእኔ
ልዩነቱ ይብቃን አንድ እንሁን ወገኔ።


ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@Getemlemitemaw
@Getem_lemitemaw
@Getemlemitemaw



tg-me.com/Getem_lemitemaw/632
Create:
Last Update:

"ርዕሱን ለአድማጭ"
ርዕሱ ነው
( አምባዬ ጌታነህ )

እኔ የአንቺ ደሐብ-ብኩን ደግ አፍቃሪ፣
ለክብረሽ መግለጫ - ፊደልሽን ቆጣሪ፣
እየተቅለሰለስኩ በልጅሽ ፊት ስኖር፣
ከማዘን በስተቀር ስቄ አላቅም ከምር።
ያም ለዛ ያም ለዛ ሲያጋድል እያየሁ፣
በጊዜ ዳኛ ላይ ፍትህ እየተራብሁ፣
ሁሌ እንዳጉተመተምሁ
'ልጅ አሳድግ ብየ
ካገር እኖር ብየ
ለባሻ ዳርኩለት ሚስቴን 'ህቴ ብየ።'
እንዳለው ገበሬ፣
አለሁኝ እንዳለሁ
ግፍ ሆኖብኝ ክብሬ።

አባት ማጣት ሀዘን - እናት ማጣት ህመም፣
ሆኖ እንደ እግር እሳት እልፍ አመት ቢፈጅም፣
በተበዳይ ልብ ውስጥ ለምፅ እንደሚያሳርፍ ገዳይ አውቆ አያቅም፣
እኔ ያለ ወላጅ መቅረቴ አያመውም።

ሰማይ የግፍ እምባ ሊጥል አቀርዝዟል፣
ጋራ ሸንተረሩ በዝምታ ነግሷል፣
ሜዳ ወንዛ ወንዙ ቅጠሉ ጠንዝሏል፣
እናት ሞቅ አጥልቃ፣
ቁርንጮዋን ታጥቃ፣
ፊቷ ተነጫጭቷል፣
አባት ወደ ማታ ባዘን አጎንብሷል፣
የእኔም የነገ እጣ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ለዛሬ ያለምነው ቅዠት ሲሆን ተስፋ፣
አንተ የፍጥረት አምላክ
የምህረት ዝናብህን ባጥል እንኳ አካፋ።
ነፃ በሆነች ምድር ነፃ አውጪዎች ሞልተው ነፃ ህዝብ ጠፋ።
እኒህ ነፃ አውጪዎች
የለውጡ አምበሳዎች
በቀን አስር ጊዜ ' እመኑን 'የሚሉን፣
ከምናየው እውነት የተፃረረውን
' መሲህ ነን ' የሚሉን
ከእመኑን ባሻገር እንድናምን 'ሚሹት ውሸቱ ምን ይሆን፣

ባለሁለት ወንበር ምቾት ካልተሰማኝ፣
የምለውን ሰምቶ ሰርቶ ካልታዘዘኝ
አባወርነቴን ከተፈታተነኝ
የእሱ መኖር ለእኔ ..
መሄጃ መቆሚያ ማረፊያ ካሳጣኝ፣
እንዴት መላ አላስብ፣
እንዴት ሴራ አልሸርብ
የምን እያቀፉ እንደ ልጅ ማባበል፣
ሳለ ብልህ ዘዴ
በመፈንቅለ ስም መሪነትን መግደል።

እንዲህ ነው እንግዲህ የኛ ዘመን ጣጣ፣
የየዋህ እስትንፋስ የንፁህ እድል እጣ።
ያደለው በሰው ልብ እንደተናፈቀ በክብር ይሞታል፣
ያለደለው ደግሞ የራሱን ቁም ሙቶ ሊገድል ይኖራል፣
ምንድን ነው ሰው መሆን ያዘነ ማስመሰል፣
በውስጥ እየሳቁ ለቅሶ ምን ያደርጋል፣
ፍረድ አንተ ጌታ...
የኃጢያት እልፍኜን
ና ደብድብ ጣራዋን
ወየ ኡኡ ብየ ላቅልጠው ዋይታየን
ቅጣኝ ለክህደቴ
አርገው እውነት የምር የውሸት ለቅሶየን።

እናም በኔ ዘመን...
የእውነት ዘውድ ተጭኖ የሚታየው አሁን፣
ቀዳዳን በር አረጎ ሚያይ ልዩነትን
አንድነትን ትቶ የሚስብክ ጥልን።
በአንድ መንጋ ሚሄድ፣
ያለ ሀሳብ ሚነጉድ
ግን
እስከየት ድረስ ነው?
ጎዳናው ሚያዘልቀው
እስከ መቼ ድረስ በጎጥ አንድ መንገድ፣
በንፁሃን ደም ላይ..
ንፁሃንን ከሶ እያሰሩ መሄድ።
ነውስ?
'ውሻ በቀደደው ጅብ ሠፍቶ ይገባል
ፍየል በግ ቢያጣ እንኳ
ቋንጣውን ሸምጥጦ ይሮጣል እንዲባል
ሆነ በቃ እንግዲህ
የዚች አገር እጣ በተራ መበደል?!

ተው
እንተው
በዳይ ከተበዳይ እኩል ፍትህ ካለ ካልሰከነ ነገር፣
ቤትን ካላቆመ
አንደኛው ጭራሮ ሌላው ሆኖ ማገር፣
ምስጥ የበላት ጎጆ ትመስላለች ሀገር።
"
' ? '
በበረሀ ጋመን ጠውልጎ ያልረባው፣ማውጣት የተሳነው የማህፀንሽ ፍሬ፣
ለአርባ አምስት አመታት ንጉሥ ያልወጣብሽ ምን ኀጥያት ሰርተሽ ነው ንገሪኝ ሀገሬ?

ምንዱባን ኢትዮጵያ - ምትለምኝ ሰጥተሽ፣
ጥበብሽ ሳይቆሽሽ
የምታጥቢ ፈተሽ
ሩህሩኋ የኔ
ጥጥ ፈታይዋ እናቴ፣
ምን ልብ ነው ያለሽ
እኔ እየጠላሁሽ
አንቺ ምትሳሽልኝ ንገሪኝ በሞቴ?

' መደምደሚያ '
በአንድ ቋንቋ ዘየ የሰራነው መንደር፣
ምን ብንኩራራበት አይሆነንም ሀገር።
ይብቃን መጋደሉ፣
ይብቃን መላቀሱ፣
መርገምት ነው ይሄ
እንፀልይ ወደ እርሱ።
ደግሞ
ያሻው ቢከፋኝም፣
ያሻ ብቀየምም፣
ወንድምነትክን ግን
ለሰከንድ አልፍቅም
ሲነኩህ ያመኛል ይሰማዋል ጎኔ፣
ይህ ሁሉ ግፍ ይቁም በአንተ በእሷ በእኔ
ልዩነቱ ይብቃን አንድ እንሁን ወገኔ።


ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
@Getemlemitemaw
@Getem_lemitemaw
@Getemlemitemaw

BY ግጥም ለሚጠማዉ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/Getem_lemitemaw/632

View MORE
Open in Telegram


ግጥም ለሚጠማዉ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Export WhatsApp stickers to Telegram on iPhone

You can’t. What you can do, though, is use WhatsApp’s and Telegram’s web platforms to transfer stickers. It’s easy, but might take a while.Open WhatsApp in your browser, find a sticker you like in a chat, and right-click on it to save it as an image. The file won’t be a picture, though—it’s a webpage and will have a .webp extension. Don’t be scared, this is the way. Repeat this step to save as many stickers as you want.Then, open Telegram in your browser and go into your Saved messages chat. Just as you’d share a file with a friend, click the Share file button on the bottom left of the chat window (it looks like a dog-eared paper), and select the .webp files you downloaded. Click Open and you’ll see your stickers in your Saved messages chat. This is now your sticker depository. To use them, forward them as you would a message from one chat to the other: by clicking or long-pressing on the sticker, and then choosing Forward.

Telegram announces Search Filters

With the help of the Search Filters option, users can now filter search results by type. They can do that by using the new tabs: Media, Links, Files and others. Searches can be done based on the particular time period like by typing in the date or even “Yesterday”. If users type in the name of a person, group, channel or bot, an extra filter will be applied to the searches.

ግጥም ለሚጠማዉ from us


Telegram ግጥም ለሚጠማዉ
FROM USA