Telegram Group & Telegram Channel
[ ገንዘብ ካለህ ሴት ልጅ ጥላህ አትሄድም ]

ሀብታም ከሆንክ፣ የተደላደለ ኑሮ የምትኖር ከሆነ፣ በወጣህ በገባህ ቁጥር በስጦታ ካንበሸበሽካት፣ የምትፈልገውን ሁሉ ከገዛኽላት ... ሴት ልጅ መቼም ጥላህ አትሄድም።

ውሸት .... ውሸት .... ውሸት

ሴትን ልጅ በገንዘብ አትይዛትም።

ኤለን መስክን ታውቀዋለህ ... ያ እንደውም የቴስላ መኪና አምራች ኩባንያ ባለቤት፣ የጠፈር ምርምር ጣቢያ ባለቤት እና ቲውተር ይባል የነበረውን ማህበራዊ ሚዲያ ገዝቶ X ብሎ ስሙን የቀየረው .... አዎ እሱ። ይኼውልህ የመጀመሪያ ሚስቱን አግብቶ ስድስት ልጆች ወልዷል። አንዴ መንታ፣ አንዴ ደሞ ሶስት ልጆችን በአንድ እርግዝና ... እንዴት ቢጫወተው ነው አልክ ... ተወው እሱ ይቅር። በዚህች አለም ላይ ሁሉም ነገር ላለው እንዳሽቃበጠ ነው። ብቻ ወደ ቁምነገራችን ስንመለስ ... ይህች ሴት አብራው የቆየችው ለስምንት አመት ብቻ ነው። ምነው ስትባል ግንኙነታችን "ጤናማ" አልነበረም አለች። እህህ ... ያ ሁሉ ሀብት እና ገንዘብ እያለው ሲሏት .... ገንዘብ የትኛውንም ነገር ጤናማ አያደርግም ብላ ውልቅ።

በዚህ የተናደደው ኤለን ቆይ ምን የመሰለችውን አግብቼ ባላደብንሽ ብሎ መነሳት .... ከሁለት አመት በኋላ እንደፎከረው ምራቅ የምታስውጥ አክተር አግብቶ ለሁለት አመት ሲያጫውት ከርሞ ተለያየ። ከአንድ አመት በኋላ ያልጨረስነው ፍቅር አለን ብለው እንደገና ተጋቡ። ያላለቀው ፍቅር የቆየው ለሶስት አመታት ብቻ ነው። እቺኛዋም በቃኝ ብላ ሄደች። አሁን እሱም ገንዘቡ የትኛዋንም ሴት እንደማያቆይለት አምኖ በየሄደበት እየወለደ ሴቶቹም በጋራ ልጅ እያሳደጉ መኖርን መርጠዋል።

ይሄ ሰው የአለማችን ቁጥር አንድ ሀብታም ነው። የእሱ ገንዘብ ሴትን ካላቆየ የአንተ ሰባራ ሳንቲም በየትኛው አቅሙ ነው "በብሬ እይዛታለሁ" ብሎ ልብህን ያሳበጠው?

ቢል ጌትስ ጋር እንምጣ። ይሄ ሰው የማይክሮሶፍት ኩባንያ ባለቤት ነው። ለ27 አመት አብራው የቆየችው ሚስቱ ጥላው ስትሄድ ምክንያት ያደረገው "በግል ጉዳይ አልተግባባንም" የሚለውን ነው። አየህ ገንዘብ ከ27 አመታት በኋላ የሚመጣ የግል ጉዳይንም አይፈታም።

የአማዞኑ ባለቤት ጄፍ ቤዞስም ለ25 አመት የኖረው ትዳሩ ባለው የገንዘብ ብዛት አልዳነም። ብር አለኝ ብሎ ውሽማ ይዞ እሽኮለሌ ሲል አንተም ብርህም ገደል ግቡ ብላው እብስ። የምትካፈለውን ብር አስባ እንዳይመስልህ .... ትንሽ ነው የወሰደችው።

እንግዲህ አስበው እነዚህ ሁሉ ሰዎች ያላቸውን ብር አንተ እድሜ ልክህን አታገኘውም ... ግን ሴቷን በብሬ እይዛለሁ ብለህ ታስባለህ።

ደ|ደ|ብ ካልሆንክ በስተቀር የየትኛዋንም ሴት ታማኝነት በገንዘብ እንደማትገዛው መረዳት አለብህ።

በፍቅር ስም አብረህ ስትጃጃል ስለከረምክ ጥላህ አትሄድም ማለት አይደለም።

ጥሩ ሰው ነህ ማለት አስደግፋህ አትሸበለልም ማለት አይደለም። አንተ መልካም ስለሆንክላት ትሳሳልሃለች ማለት አይደለም።

ብልጥ ሁን ወዳጄ

ሴትን ልጅ አስሮ የሚያስቀምጣት ገንዘብህ፣ ፍቅርህ፣ ጥሩነትህ፣ መልክህ፣ የአልጋ ላይ ነብርነትህ አይደለም .... ፍላጎቷ ብቻ ነው።

እንደውም ገንዘብህ አስሮ እንደሚያስቀምጣት በተማመንክ ቁጥር የመሄዷ ነገር እርግጥ እየሆነ ይመጣል።

ጢባርህንም .... ትቢትህንም .... እብሪትህንም በልኩ አድርገው። አለበለዚያ ታበርድልሃለች !!

~

... ብቻ ነገሩ ውስብስብ ነው !!

~

      

          

                    © Abby Junior


www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group



tg-me.com/Islam_and_Science/6307
Create:
Last Update:

[ ገንዘብ ካለህ ሴት ልጅ ጥላህ አትሄድም ]

ሀብታም ከሆንክ፣ የተደላደለ ኑሮ የምትኖር ከሆነ፣ በወጣህ በገባህ ቁጥር በስጦታ ካንበሸበሽካት፣ የምትፈልገውን ሁሉ ከገዛኽላት ... ሴት ልጅ መቼም ጥላህ አትሄድም።

ውሸት .... ውሸት .... ውሸት

ሴትን ልጅ በገንዘብ አትይዛትም።

ኤለን መስክን ታውቀዋለህ ... ያ እንደውም የቴስላ መኪና አምራች ኩባንያ ባለቤት፣ የጠፈር ምርምር ጣቢያ ባለቤት እና ቲውተር ይባል የነበረውን ማህበራዊ ሚዲያ ገዝቶ X ብሎ ስሙን የቀየረው .... አዎ እሱ። ይኼውልህ የመጀመሪያ ሚስቱን አግብቶ ስድስት ልጆች ወልዷል። አንዴ መንታ፣ አንዴ ደሞ ሶስት ልጆችን በአንድ እርግዝና ... እንዴት ቢጫወተው ነው አልክ ... ተወው እሱ ይቅር። በዚህች አለም ላይ ሁሉም ነገር ላለው እንዳሽቃበጠ ነው። ብቻ ወደ ቁምነገራችን ስንመለስ ... ይህች ሴት አብራው የቆየችው ለስምንት አመት ብቻ ነው። ምነው ስትባል ግንኙነታችን "ጤናማ" አልነበረም አለች። እህህ ... ያ ሁሉ ሀብት እና ገንዘብ እያለው ሲሏት .... ገንዘብ የትኛውንም ነገር ጤናማ አያደርግም ብላ ውልቅ።

በዚህ የተናደደው ኤለን ቆይ ምን የመሰለችውን አግብቼ ባላደብንሽ ብሎ መነሳት .... ከሁለት አመት በኋላ እንደፎከረው ምራቅ የምታስውጥ አክተር አግብቶ ለሁለት አመት ሲያጫውት ከርሞ ተለያየ። ከአንድ አመት በኋላ ያልጨረስነው ፍቅር አለን ብለው እንደገና ተጋቡ። ያላለቀው ፍቅር የቆየው ለሶስት አመታት ብቻ ነው። እቺኛዋም በቃኝ ብላ ሄደች። አሁን እሱም ገንዘቡ የትኛዋንም ሴት እንደማያቆይለት አምኖ በየሄደበት እየወለደ ሴቶቹም በጋራ ልጅ እያሳደጉ መኖርን መርጠዋል።

ይሄ ሰው የአለማችን ቁጥር አንድ ሀብታም ነው። የእሱ ገንዘብ ሴትን ካላቆየ የአንተ ሰባራ ሳንቲም በየትኛው አቅሙ ነው "በብሬ እይዛታለሁ" ብሎ ልብህን ያሳበጠው?

ቢል ጌትስ ጋር እንምጣ። ይሄ ሰው የማይክሮሶፍት ኩባንያ ባለቤት ነው። ለ27 አመት አብራው የቆየችው ሚስቱ ጥላው ስትሄድ ምክንያት ያደረገው "በግል ጉዳይ አልተግባባንም" የሚለውን ነው። አየህ ገንዘብ ከ27 አመታት በኋላ የሚመጣ የግል ጉዳይንም አይፈታም።

የአማዞኑ ባለቤት ጄፍ ቤዞስም ለ25 አመት የኖረው ትዳሩ ባለው የገንዘብ ብዛት አልዳነም። ብር አለኝ ብሎ ውሽማ ይዞ እሽኮለሌ ሲል አንተም ብርህም ገደል ግቡ ብላው እብስ። የምትካፈለውን ብር አስባ እንዳይመስልህ .... ትንሽ ነው የወሰደችው።

እንግዲህ አስበው እነዚህ ሁሉ ሰዎች ያላቸውን ብር አንተ እድሜ ልክህን አታገኘውም ... ግን ሴቷን በብሬ እይዛለሁ ብለህ ታስባለህ።

ደ|ደ|ብ ካልሆንክ በስተቀር የየትኛዋንም ሴት ታማኝነት በገንዘብ እንደማትገዛው መረዳት አለብህ።

በፍቅር ስም አብረህ ስትጃጃል ስለከረምክ ጥላህ አትሄድም ማለት አይደለም።

ጥሩ ሰው ነህ ማለት አስደግፋህ አትሸበለልም ማለት አይደለም። አንተ መልካም ስለሆንክላት ትሳሳልሃለች ማለት አይደለም።

ብልጥ ሁን ወዳጄ

ሴትን ልጅ አስሮ የሚያስቀምጣት ገንዘብህ፣ ፍቅርህ፣ ጥሩነትህ፣ መልክህ፣ የአልጋ ላይ ነብርነትህ አይደለም .... ፍላጎቷ ብቻ ነው።

እንደውም ገንዘብህ አስሮ እንደሚያስቀምጣት በተማመንክ ቁጥር የመሄዷ ነገር እርግጥ እየሆነ ይመጣል።

ጢባርህንም .... ትቢትህንም .... እብሪትህንም በልኩ አድርገው። አለበለዚያ ታበርድልሃለች !!

~

... ብቻ ነገሩ ውስብስብ ነው !!

~

      

          

                    © Abby Junior


www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group

BY ISLAMIC SCHOOL


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/Islam_and_Science/6307

View MORE
Open in Telegram


ISLAMIC SCHOOL Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram and Signal Havens for Right-Wing Extremists

Since the violent storming of Capitol Hill and subsequent ban of former U.S. President Donald Trump from Facebook and Twitter, the removal of Parler from Amazon’s servers, and the de-platforming of incendiary right-wing content, messaging services Telegram and Signal have seen a deluge of new users. In January alone, Telegram reported 90 million new accounts. Its founder, Pavel Durov, described this as “the largest digital migration in human history.” Signal reportedly doubled its user base to 40 million people and became the most downloaded app in 70 countries. The two services rely on encryption to protect the privacy of user communication, which has made them popular with protesters seeking to conceal their identities against repressive governments in places like Belarus, Hong Kong, and Iran. But the same encryption technology has also made them a favored communication tool for criminals and terrorist groups, including al Qaeda and the Islamic State.

To pay the bills, Mr. Durov is issuing investors $1 billion to $1.5 billion of company debt, with the promise of discounted equity if the company eventually goes public, the people briefed on the plans said. He has also announced plans to start selling ads in public Telegram channels as soon as later this year, as well as offering other premium services for businesses and users.

ISLAMIC SCHOOL from us


Telegram ISLAMIC SCHOOL
FROM USA