tg-me.com/Mebacha/114
Last Update:
ብልኋ እንቁራሪት
-----------
(ሚካኤል_እንዳለ)
አንዲት እንቁራሪት በኩሬ ውስጥ ያለች
የሚቃጠል መንደር ፥ ከሩቁ እያየች
ትፀልይ ጀመረ ፥ እንደዚህ እያለች
.
.
እባክህ ጌታዬ ይህን እሳት አጥፋው
ባለበት እንዲቆም ግዛቱን አታስፋው
ብላ ለፈጣሪ ፥ አዝና ስትናገር
ለካስ ካጠገቧ እባብ ቆሞ ነበር
እሱም በመገረም ፥ በጸሎቷ ነገር
የሽሙጥ እያየ እንዲህ ይላት ጀመር
.
.
እንደው ምን ትገርሚ እንደምን ትደንቂ
እሳቱ እንዲጠፋ ፥ ጌታን 'ምጠይቂ
እሱ 'ሚደድ እዛ እሩቅ ነው ካንቺ ዘንድ
በምን ደርሶብሽ ነው ያንቺን ቤት የሚያነድ ?
ደሞም ከውሃ ውስጥ ቁጭ ብለሽ ያለሽው
የማይደርስብሽን ፥ እሳት የምትፈሪው
እያለ በሹፈት ፥ ከልቡ ሳቀባት
ወደታች በንቀት አዘቅዝቆ እያያት
.
.
ይ'ን ጊዜ እቁራሪት እየተገረመች
በእባብ ጅልነት በጣም እያዘነች
እንዲት ትለው ጀመር ቀና ብላ እያየች
አዎ ትክክል ነህ ፥ እሳቱ እሩቅ ነው
እኔም ያለሁበት ዙሪያውን ውሀ ነው
ነገር ግን አስተውል እጅግ አትሳት
ቃጠሎውን ቶሎ ወዲያው ካላቆሙት
ከ'ኔ ዘንድ መ'ተው ነው ውሀ የሚቀዱት
.
.
እናም ያላወከው እውነታው ይሄ ነው
ምንም'ኳ እዚህ ብቀመጥ ከውሃው
እዛ እሩቅ ቢሆን መንደሩ 'ሚነደደው
ካልጠፋ በጊዜ ፥ አምላክ ካላቆመው
የ' ኔም ቤት ነውና ተዝቆ የሚያልቀው
.
.
ስለዚህ ወዳጄ አያጥቃህ ጅልነት
ቃጠሎው ባይደርስም እኔ ካልሁበት
እዛ ነዶ ነዶ ፥ እጅግ ከባሰበት
ባልዲ ተሸክመው ሲመጡ ለመቅዳት
ይከቱኛል ወስደው ፥ ከሚነደው እሳት
.
.
ይህን አውቄ ነው ከሩቁ መፍራቴ
አጥፋው በሚል ፀሎት ምድር መደፋቴ
የአቅሜን ያህል እነሱን መርዳቴ
ብላ ስትናገር ፥ እባብን ገረመው
ማየት ያልቻለውን ገልጣ ስታሳየው
.
.
እናም እሩቅ ያለ ከ' እኛ የማይደርስ
የሌላ ነው ያልነው ፥ እሳቱ ሲለኮስ
ስለማይቀር እዚ ፥ መምጣቱ ቀስ በቀስ
ትልቅ እገዛ ነው
የሰው ችግር አይቶ ፥ ለኔ ብሎ ማልቀስ
---
(ሚካኤል እንዳለ)
ሰኔ 1 , 2012 ዓ.ም
አ.አ አስኮ
መነሻ ሃሳብ - ዳኒኤል ክብረት
BY መባቻ ©
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/Mebacha/114