Telegram Group & Telegram Channel
የድንግል መወለድ

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በሰላም አደረሳችሁ!

ሃናና ኢያቄም ሆይ እንኳን ደስ አላችሁ ! ልጅን ለቤት ሳይሆን ለዓለም ወለዳችሁ ። ቡሩክ ማኅፀን ያለሽ ሃና ሆይ ! ያለ ዘር ያለ ሩካቤ የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ። የልጅ ልጅ ለማየት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ችሎታ በቤተሰብሽ ለማየት ሃና ሆይ በስእለት ድንግልን ወለድሽ ! ከእግዚአብሔር የተገኘችውን ለእግዚአብሔር ሰጠሽ ። ከእግዚአብሔር ተገኝታ ፣ በእግዚአብሔር የኖረች ልጅ ወለድሽ ! ውስጣዊ ደም ግባት ያላትን ልጅ ወለድሽ ! እግዚአብሔር የሚያየውን ውበት የተጎናጸፈች ልጅ ወለድሽ ! አዳም በገነት በተስፋ ያያትን ፣ ያችን ሴት ያለ ወንድ ዘር የምትፀንሰውን ድንግል ወለድሽ ! የፀሐዩ የክርስቶስ እናት ምሥራቅ ማርያም ካንቺ ተወለደች ። እውነተኛው ኮከብ የተወለደባት ፣ ምድራዊ ክፋት ያልቀረባት ሰማይ ዛሬ ተወለደች ። ሃና ሆይ ኢሳይያስ የተናገረውን ትንቢት ሰምተሽ ነበር ። ያ ትንቢት በእኔ ይፈጸማል ብለሽ አልጠበቅሽም ። እግዚአብሔር ግን አሳቡን በጊዜው ይፈጽማልና ድብቅ በረከት ድንግልን ዛሬ ወለድሽ !

በስደት ዓለም ላይ ድርብ ስደት የገጠመሽ ፣ በሊባኖስ ተራሮች የአርዘ ሊባኖሱን የዘንካታውን የክርስቶስን እናት ወለድሽ ! ለአምላክ አያት እሆናለሁ ብለሽ አስበሽ አታውቂም ነበር ። ቡሩክ ልጅ ስትለምኚ አምላክን የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ! ሃና ሆይ በሕግ በሩካቤ ልጅን ወለድሽ ፣ ካንቺ የተወለደችው ድንግል ግን ከሕግ በላይ በሥልጣነ እግዚአብሔር በድንግልና ፀንሳ የምትወልድ ሆነች ። ላንቺ ጋብቻ ክብርሽ ነበር ፣ ለልጅሽ ድንግል መሆን ክብርዋና መጠሪያዋ ነው ። አንቺ እስከ ጊዜው ድንግል ነበርሽ ፣ ልጅሽ ግን ለዘላለም ድንግል ናት ። አንቺ ቤተሰቦችሽ ለወንድ አጩሽ ፣ ልጅስ ማርያም ግን አብ ለልጁ ማደሪያ እንድትሆን መረጣት ። አንቺ አምላክን በእምነት አየሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን በባሕርይ ልደት ወለደችው ። አንቺ ካንቺ በኋላ ያለች ልጅን ወለድሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን የሚቀድማትን ልጅ ወለደች ። ሃና ሆይ ! ደስ ይበልሽ ! የወለደም ያልወለደም በሚያዝንበት በዚህ ጎዶሎ ዓለም ሙሉ ጨረቃ ማርያም ካንቺ ተወለደች ።

ኢያቄም ሆይ ደስ ይበልህ ! የአብራክህ ክፋይ ድንግል ማርያም የባሕርያችን መመኪያ ሆነች ። ሰውና እግዚአብሔር የ5500 ዘመን ቀጠሮአቸውን በድንግል ማርያም ማኅፀን ፈጸሙ ። ምሳሌው አማናዊ የሚሆንባት ፣ ትንቢት የሚያርፍባት ፣ ንግርት የሚጠናቀቅባት ፣ ሱባዔ የሚቋጭባት ድንግል ዛሬ ተወለደች ። ክብርህ ከታላላቅ አባቶች ነው ። የዳዊት ልጅ መሆን ካኮራህ ፣ የዳዊት አምላክ ካንተ በመወለዱ እንዴት አትኮራም !! ለአምላክ አያት ለመሆን የበቃህ ኢያቄም በእውነት የተባረክህ ነህ ። እናንተ ዘረ ቅዱሳን ከአብርሃም እስከ ዳዊት ፣ ከዳዊት እስከ ኤልሳቤጥ ፣ ከሃና እስከ ድንግል ቅድስና አልነጠፈባችሁም የታደላችሁ ናችሁ ። ምነው የእናንተ ዘመድ ባደረገኝ !

የሰጪው እናት ከሁሉ ይልቅ ድሀ ነሽ ፣ ነገር ግን እንዳንቺ የበለጸገ ማንም የለም ። የቸሩ እናት አዛኝ ነሽ ፣ እንዳንቺ የሆነለት ማንም የለም ፣ ነገር ግን በበረት የወለድሽ ፣ በግብጽ የተሰደድሽ ነሽ ። ሕይወትሽ ቅኔ የሆነው ፣ ባንቺ ላይ ያለው ምሥጢር የማይፈታው የኢየሱስ እናት ማርያም እንኳን ተወለድሽ ! በመወለድሽ ብዙ ነገር እንማራለን ። እግዚአብሔር ጋብቻን እንደሚያከብር ከወላጆችሽ ተማርን ። ድንግልናን እንዳከበረ ካንቺ ተማርን ። እግዚአብሔር ለሚጠብቁት ቸር መሆኑን በስእለት በመወለድሽ አወቅን ። አንቺ ልጅሽን በበረት ብትወልጅ ፣ ያንቺ ልደትም በስደት በሊባኖስ ተራራ ላይ ሆነ ። ዓለም ለደግና ለደጎች ደግ ለክርስቶስ እንደማትሆን ተማርን ። አንቺን የመሰለች ልጅ ቢያገኙም ለእግዚአብሔር ሰጡ እንጂ የራሳቸው አላደረጉሽም ። እግዚአብሔር ጋ የተቀመጠ የት ይሄዳል ? ብለው ሰጡሽ ። መቅደስ ሆይ በመቅደስ አደግሽ ። አሮን ከገባባት ከቅድስተ ቅዱሳን የምትበልጪ የታላቁ ሊቀ ካህን የክርስቶስ መቅደስ ሆይ እሰይ ተወለድሽልን ። ድንግል ሆይ የልደትሽ በረከት ይድረሰን ። ኃጢአት ላደከመን ልጆችሽ ምልጃሽ አይለየን !

ሁሉን አዋቂ ወልድ ሆይ! ስለ ወዳጅህ ስለ አብርሃም ከማለት ስለ እናት ስለ ድንግል ማለት ይበልጣልና ። ከወዳጅ እናት ትልቃለችና ። ስለ አማኑኤል ስምህ ስለ ማርያም እናትህ ብለህ በዓይነ ምሕረት ተመልከተን ! ማዕበሉን ቀዝፈህ አሻግረን !

እንኳን ለድንግል ማርያም ልደት አደረሳችሁ!

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3940
Create:
Last Update:

የድንግል መወለድ

እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በሰላም አደረሳችሁ!

ሃናና ኢያቄም ሆይ እንኳን ደስ አላችሁ ! ልጅን ለቤት ሳይሆን ለዓለም ወለዳችሁ ። ቡሩክ ማኅፀን ያለሽ ሃና ሆይ ! ያለ ዘር ያለ ሩካቤ የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ። የልጅ ልጅ ለማየት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ችሎታ በቤተሰብሽ ለማየት ሃና ሆይ በስእለት ድንግልን ወለድሽ ! ከእግዚአብሔር የተገኘችውን ለእግዚአብሔር ሰጠሽ ። ከእግዚአብሔር ተገኝታ ፣ በእግዚአብሔር የኖረች ልጅ ወለድሽ ! ውስጣዊ ደም ግባት ያላትን ልጅ ወለድሽ ! እግዚአብሔር የሚያየውን ውበት የተጎናጸፈች ልጅ ወለድሽ ! አዳም በገነት በተስፋ ያያትን ፣ ያችን ሴት ያለ ወንድ ዘር የምትፀንሰውን ድንግል ወለድሽ ! የፀሐዩ የክርስቶስ እናት ምሥራቅ ማርያም ካንቺ ተወለደች ። እውነተኛው ኮከብ የተወለደባት ፣ ምድራዊ ክፋት ያልቀረባት ሰማይ ዛሬ ተወለደች ። ሃና ሆይ ኢሳይያስ የተናገረውን ትንቢት ሰምተሽ ነበር ። ያ ትንቢት በእኔ ይፈጸማል ብለሽ አልጠበቅሽም ። እግዚአብሔር ግን አሳቡን በጊዜው ይፈጽማልና ድብቅ በረከት ድንግልን ዛሬ ወለድሽ !

በስደት ዓለም ላይ ድርብ ስደት የገጠመሽ ፣ በሊባኖስ ተራሮች የአርዘ ሊባኖሱን የዘንካታውን የክርስቶስን እናት ወለድሽ ! ለአምላክ አያት እሆናለሁ ብለሽ አስበሽ አታውቂም ነበር ። ቡሩክ ልጅ ስትለምኚ አምላክን የምትወልድ ልጅ ወለድሽ ! ሃና ሆይ በሕግ በሩካቤ ልጅን ወለድሽ ፣ ካንቺ የተወለደችው ድንግል ግን ከሕግ በላይ በሥልጣነ እግዚአብሔር በድንግልና ፀንሳ የምትወልድ ሆነች ። ላንቺ ጋብቻ ክብርሽ ነበር ፣ ለልጅሽ ድንግል መሆን ክብርዋና መጠሪያዋ ነው ። አንቺ እስከ ጊዜው ድንግል ነበርሽ ፣ ልጅሽ ግን ለዘላለም ድንግል ናት ። አንቺ ቤተሰቦችሽ ለወንድ አጩሽ ፣ ልጅስ ማርያም ግን አብ ለልጁ ማደሪያ እንድትሆን መረጣት ። አንቺ አምላክን በእምነት አየሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን በባሕርይ ልደት ወለደችው ። አንቺ ካንቺ በኋላ ያለች ልጅን ወለድሽ ፣ ልጅሽ ማርያም ግን የሚቀድማትን ልጅ ወለደች ። ሃና ሆይ ! ደስ ይበልሽ ! የወለደም ያልወለደም በሚያዝንበት በዚህ ጎዶሎ ዓለም ሙሉ ጨረቃ ማርያም ካንቺ ተወለደች ።

ኢያቄም ሆይ ደስ ይበልህ ! የአብራክህ ክፋይ ድንግል ማርያም የባሕርያችን መመኪያ ሆነች ። ሰውና እግዚአብሔር የ5500 ዘመን ቀጠሮአቸውን በድንግል ማርያም ማኅፀን ፈጸሙ ። ምሳሌው አማናዊ የሚሆንባት ፣ ትንቢት የሚያርፍባት ፣ ንግርት የሚጠናቀቅባት ፣ ሱባዔ የሚቋጭባት ድንግል ዛሬ ተወለደች ። ክብርህ ከታላላቅ አባቶች ነው ። የዳዊት ልጅ መሆን ካኮራህ ፣ የዳዊት አምላክ ካንተ በመወለዱ እንዴት አትኮራም !! ለአምላክ አያት ለመሆን የበቃህ ኢያቄም በእውነት የተባረክህ ነህ ። እናንተ ዘረ ቅዱሳን ከአብርሃም እስከ ዳዊት ፣ ከዳዊት እስከ ኤልሳቤጥ ፣ ከሃና እስከ ድንግል ቅድስና አልነጠፈባችሁም የታደላችሁ ናችሁ ። ምነው የእናንተ ዘመድ ባደረገኝ !

የሰጪው እናት ከሁሉ ይልቅ ድሀ ነሽ ፣ ነገር ግን እንዳንቺ የበለጸገ ማንም የለም ። የቸሩ እናት አዛኝ ነሽ ፣ እንዳንቺ የሆነለት ማንም የለም ፣ ነገር ግን በበረት የወለድሽ ፣ በግብጽ የተሰደድሽ ነሽ ። ሕይወትሽ ቅኔ የሆነው ፣ ባንቺ ላይ ያለው ምሥጢር የማይፈታው የኢየሱስ እናት ማርያም እንኳን ተወለድሽ ! በመወለድሽ ብዙ ነገር እንማራለን ። እግዚአብሔር ጋብቻን እንደሚያከብር ከወላጆችሽ ተማርን ። ድንግልናን እንዳከበረ ካንቺ ተማርን ። እግዚአብሔር ለሚጠብቁት ቸር መሆኑን በስእለት በመወለድሽ አወቅን ። አንቺ ልጅሽን በበረት ብትወልጅ ፣ ያንቺ ልደትም በስደት በሊባኖስ ተራራ ላይ ሆነ ። ዓለም ለደግና ለደጎች ደግ ለክርስቶስ እንደማትሆን ተማርን ። አንቺን የመሰለች ልጅ ቢያገኙም ለእግዚአብሔር ሰጡ እንጂ የራሳቸው አላደረጉሽም ። እግዚአብሔር ጋ የተቀመጠ የት ይሄዳል ? ብለው ሰጡሽ ። መቅደስ ሆይ በመቅደስ አደግሽ ። አሮን ከገባባት ከቅድስተ ቅዱሳን የምትበልጪ የታላቁ ሊቀ ካህን የክርስቶስ መቅደስ ሆይ እሰይ ተወለድሽልን ። ድንግል ሆይ የልደትሽ በረከት ይድረሰን ። ኃጢአት ላደከመን ልጆችሽ ምልጃሽ አይለየን !

ሁሉን አዋቂ ወልድ ሆይ! ስለ ወዳጅህ ስለ አብርሃም ከማለት ስለ እናት ስለ ድንግል ማለት ይበልጣልና ። ከወዳጅ እናት ትልቃለችና ። ስለ አማኑኤል ስምህ ስለ ማርያም እናትህ ብለህ በዓይነ ምሕረት ተመልከተን ! ማዕበሉን ቀዝፈህ አሻግረን !

እንኳን ለድንግል ማርያም ልደት አደረሳችሁ!

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3940

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram Be The Next Best SPAC

I have no inside knowledge of a potential stock listing of the popular anti-Whatsapp messaging app, Telegram. But I know this much, judging by most people I talk to, especially crypto investors, if Telegram ever went public, people would gobble it up. I know I would. I’m waiting for it. So is Sergei Sergienko, who claims he owns $800,000 of Telegram’s pre-initial coin offering (ICO) tokens. “If Telegram does a SPAC IPO, there would be demand for this issue. It would probably outstrip the interest we saw during the ICO. Why? Because as of right now Telegram looks like a liberal application that can accept anyone - right after WhatsApp and others have turn on the censorship,” he says.

What Is Bitcoin?

Bitcoin is a decentralized digital currency that you can buy, sell and exchange directly, without an intermediary like a bank. Bitcoin’s creator, Satoshi Nakamoto, originally described the need for “an electronic payment system based on cryptographic proof instead of trust.” Each and every Bitcoin transaction that’s ever been made exists on a public ledger accessible to everyone, making transactions hard to reverse and difficult to fake. That’s by design: Core to their decentralized nature, Bitcoins aren’t backed by the government or any issuing institution, and there’s nothing to guarantee their value besides the proof baked in the heart of the system. “The reason why it’s worth money is simply because we, as people, decided it has value—same as gold,” says Anton Mozgovoy, co-founder & CEO of digital financial service company Holyheld.

Nolawi ኖላዊ from us


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA