Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-93336-93337-93338-93339-93340-93341-93342-93343-93344-93345-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/93339 -
Telegram Group & Telegram Channel
#HaileResortJimma

“ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል" - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ

የሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ ሆቴልና ሪዞርት 10ኛ መዳረሻ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ዛሬ (ሐሙስ ታኀሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም) ተመርቋል።

ሆቴሉ 3 የመመገቢያ አደራሾች፣ የልጆች መጫወቻ፣ ሞሮኮ ባዝ እንዳሉት፣ ለ210 ሰዎች ቋሚ የሥራ እድል እንደፈጠረ፣ ለወደፊት ደግሞ ወደ 400 ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ተነግሮለታል።

ሆቴሉ አሁን የተጠናቀቁ ወደ 106 ክፍሎች እንዳሉት፣ ሁሉም ሰጠናቀቁ ደግሞ ወደ 114 ክፍሎች እንደሚኖሩት ተመልክቷል።

በመርሀ ግብሩ የተገኙት ሻለቃ ኃይሌ ባደረጉት ንግግር፣ በአንድ ዓመት ከስምንት ወራት የሆቴሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ላጠናቀቁት ሠራተኞች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

ጅማ ላይ የኮንስትራክሽን እቃ ውድ መሆኑን የገለጹት ሻለቃ ኃይሌ፣ “ብሎኬት ከአዲስ አበባ እየተጓጓዘ ነው የተሰራው” ሲሉ ተናግረዋል።

“ኮንስትራክሽኑን ውድ ያደረገው የመንገዱ መበላሸት ነው” ያሉት ኃይሌ፣ “ብሎኬቶች እየተሰባበሩ ነበር። ሁሉ ሰው በአውሮፕላን መጓጓዝ አይችልም” ነው ያሉት።

የሆቴሉን ወጪ በተመለከተ በገለጹበት አውድ ደግሞ፣ “ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል” ብለዋል።

የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በመርሀ ግብሩ ተገኝተው ባደረጉት ገለጻ ደግሞ፣ “ጅማ አባጅፋር ሁሉንም የምታቅፍ ከተማ ናት። ባለሃብቶች ጅማን ለመቀየር ከኅይሌ እንዲማሩ ማሳያ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትጃኒ ናስር ፥ “ኃይሌ ሲጠራ እንስቃለን፣ ኃይሌ ሲጠራ እንባችን ይመጣል፣ ኃይሌ እንኳን አገኘንህ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል።

“ሱልልታ ላይ የኃይሌን ሆቴል ሳይ እንዲህ አይነት ሆቴል ጅማ ላይ ቢገነባ ብዬ ተመኝቼ ነበር። አሁን እንደዚህ ተሰርቶ አየሁትና እንባዬ ነው የመጣው። የተመረቀው ለኃይሌ ሳይሆን ለጅማ ህዝብ ነው” ሲሉ አመስግነዋል።

በ10ሩም የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች 900  ሩሞች እንዳሉ፣ ለ2500 ሠራተኞች የሥራ እድል እንደተፈጠረ ተመልክቷል።

ፎቶ ፦ በግዛቱ አማረ

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/93339
Create:
Last Update:

#HaileResortJimma

“ ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል" - ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ

የሻለቃ ኃይሌ ገብረ ስላሴ ሆቴልና ሪዞርት 10ኛ መዳረሻ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ ዛሬ (ሐሙስ ታኀሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም) ተመርቋል።

ሆቴሉ 3 የመመገቢያ አደራሾች፣ የልጆች መጫወቻ፣ ሞሮኮ ባዝ እንዳሉት፣ ለ210 ሰዎች ቋሚ የሥራ እድል እንደፈጠረ፣ ለወደፊት ደግሞ ወደ 400 ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ተነግሮለታል።

ሆቴሉ አሁን የተጠናቀቁ ወደ 106 ክፍሎች እንዳሉት፣ ሁሉም ሰጠናቀቁ ደግሞ ወደ 114 ክፍሎች እንደሚኖሩት ተመልክቷል።

በመርሀ ግብሩ የተገኙት ሻለቃ ኃይሌ ባደረጉት ንግግር፣ በአንድ ዓመት ከስምንት ወራት የሆቴሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ላጠናቀቁት ሠራተኞች በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል።

ጅማ ላይ የኮንስትራክሽን እቃ ውድ መሆኑን የገለጹት ሻለቃ ኃይሌ፣ “ብሎኬት ከአዲስ አበባ እየተጓጓዘ ነው የተሰራው” ሲሉ ተናግረዋል።

“ኮንስትራክሽኑን ውድ ያደረገው የመንገዱ መበላሸት ነው” ያሉት ኃይሌ፣ “ብሎኬቶች እየተሰባበሩ ነበር። ሁሉ ሰው በአውሮፕላን መጓጓዝ አይችልም” ነው ያሉት።

የሆቴሉን ወጪ በተመለከተ በገለጹበት አውድ ደግሞ፣ “ወደ 1.7 ቢሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል” ብለዋል።

የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጣሃ ቀመር በመርሀ ግብሩ ተገኝተው ባደረጉት ገለጻ ደግሞ፣ “ጅማ አባጅፋር ሁሉንም የምታቅፍ ከተማ ናት። ባለሃብቶች ጅማን ለመቀየር ከኅይሌ እንዲማሩ ማሳያ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ትጃኒ ናስር ፥ “ኃይሌ ሲጠራ እንስቃለን፣ ኃይሌ ሲጠራ እንባችን ይመጣል፣ ኃይሌ እንኳን አገኘንህ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል።

“ሱልልታ ላይ የኃይሌን ሆቴል ሳይ እንዲህ አይነት ሆቴል ጅማ ላይ ቢገነባ ብዬ ተመኝቼ ነበር። አሁን እንደዚህ ተሰርቶ አየሁትና እንባዬ ነው የመጣው። የተመረቀው ለኃይሌ ሳይሆን ለጅማ ህዝብ ነው” ሲሉ አመስግነዋል።

በ10ሩም የኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች 900  ሩሞች እንዳሉ፣ ለ2500 ሠራተኞች የሥራ እድል እንደተፈጠረ ተመልክቷል።

ፎቶ ፦ በግዛቱ አማረ

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA













Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/93339

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The messaging service and social-media platform owes creditors roughly $700 million by the end of April, according to people briefed on the company’s plans and loan documents viewed by The Wall Street Journal. At the same time, Telegram Group Inc. must cover rising equipment and bandwidth expenses because of its rapid growth, despite going years without attempting to generate revenue.

Can I mute a Telegram group?

In recent times, Telegram has gained a lot of popularity because of the controversy over WhatsApp’s new privacy policy. In January 2021, Telegram was the most downloaded app worldwide and crossed 500 million monthly active users. And with so many active users on the app, people might get messages in bulk from a group or a channel that can be a little irritating. So to get rid of the same, you can mute groups, chats, and channels on Telegram just like WhatsApp. You can mute notifications for one hour, eight hours, or two days, or you can disable notifications forever.

TIKVAH ETHIOPIA from ar


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA