Telegram Group Search
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #EOTC " የቤተ ክርስቲያን መከራ ከውጭ ብቻ አይደለም ከውስጥም እንጂ፤ ከባዕድ ብቻም አይደለም ከወዳጅም እንጂ ፤ የወዳጅ ፈታኝ እንደሚብስም ታውቆ ያደረ ነገር ነው " - ቅዱስነታቸው ግንቦት ወር ላይ የሚካሄደው ዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተጀመረ።   የጉባኤውን መጀመር አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ…
#EOTC #ETHIOPIA

ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፦

" የማኅበረሰባችን ችግር በቤተ ክርስቲያን ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ በሀገር ደረጃ እየቀጠለ ያለው አለመግባባትም ለጠቅላላ ማኅበረ ሰባችን ፈተና ከሆነ ውሎ አድሮአል፤ የቤተ ክርስቲያናችን ፈተና ምንጭ ከሆኑትም አንዱና ዕድል ሰጩ ይህ ሀገራዊ አለመግባባት ነው።

በዚህ አለመግባባት ምክንያት ገዳማውያን መነኮሳት፤ መምህራን ካህናት ምእመናን አብያተ ክርስቲያናት ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸዋል ፤ #በሰላም_ወጥቶ_መግባትም_አጠራጣሪ_ሆኖአል ፤ ይህንን ችግር ለመፍታት የሚደረግ ጥረትም ጎልቶ አይታይም፡፡

በመሆኑም ይህ ክሥተት እውን ኢትዮጵያውያን የራሳችንን ችግር በራሳችን መፍታት የማንችል ሰዎች ነን ወይ ? ለኛስ ከኛ የበለጠ ማን ይመጣልናል ? የሚለውን ጥያቄ ልናነሣ ግድ ነው። ስለዚህ ለሀገር ህልውናና ድኅነት የሚበጅ ነገር እንዲመጣ ቤተ ክርስቲያን ባላት ሃይማኖታዊና ሰብአዊ ኃላፊነት ጠንክራ መስራት ይጠበቅባታል። "

#ኦርቶዶክስተዋሕዶ #ኢትዮጵያ
#የግንቦት_ርክበ_ካህናት_ቅዱስ_ሲኖዶስ_ምልአተ_ጉባኤ

@tikvahethiopia
Explore the future of construction at Big 5 Construct Ethiopia's Construction VR Experience Hub!

Step into the innovative world of digital construction and witness how technology is reshaping the construction sector. Experience a first-time VR construction setup in a construction event in Ethiopia as you engage in safety awareness at construction sites and discover 3D replicas of Ethiopia's iconic projects.

Don't miss this exclusive opportunity to register for free and attend the exhibition

Register for free entry: https://bit.ly/3UsrL5I

🗓️30 May - 01 June 2024
🕛Day 1: 12:00 - 18:00
🕙Day 2 & 3: 10:00 - 18:00
📍Millennium Hall, Addis Ababa, Ethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#DARMA

ግሬስ ኮንስትራክሽን ኬሚካልስ " DARMA " በሚባል ብራንድ የሚታወቁ ከ 15 በላይ የውሀ ስርገት መከላከያ፤ የወለል እና ግድግዳ ፊኒሺንግ አንዲሁም ከ ኮንክሪት ጋር የተያያዙ ማንኛውንም አይነት ኬሚካሎችን ከ8 አመታት በላይ በጥራት፤በፍጥነት እና በታማኝነት በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡ 

ተጠቃሚዎች ላላቸው ጥቄዎች በነጻ የሚያማክር በመሀንዲሶች የታገዘ ቴክኒክ ክፍል መኖሩም ለብዙዎች መተማመንን ፈጠሮላቸዋል፡፡

ግሬስ ኮንስትራክሽን ኬሚካልስ ከግንቦት 22 እስከ 24 በሚሊኒየም አዳራሽ በሚካሄደው የBIG 5 CONSTRUCT ETHIOPIA አለምአቀፍ ኤግዚቢሽን የወርቅ ደረጃ ስፖንሰር መሆኑንና ምርቶቹንም እንዲጎበኙ ሲጋበዝዎ በታለቅ ደስታ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በ ስ.ቁ 0964234444 ወይም 0929337886 ይደውሉ ወይም ወሎ ሰፈር አይቤክስ ሆቴል ጀርባ በሚገኘው ዋና ቢሮ ብቅ ይበሉ፡፡
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹 ከነገ ግንቦት 21 ጀምሮ ለ7 ቀናት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ የምክክር ምዕራፉን ይጀምራል። ከ2 ሺህ በላይ ሰዎችም ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃን። የስብሰባው ሥርዓቶች ምንድናቸው ? 1. ማንኛውም ተሳታፊ #በነጻነት ሀሳቡን የመግለጽ መብት አለው። ሆኖም ተሳታፊዎች ከጥላቻ፣ ከአዋራጅ እና ከተንኳሽ ንግግሮችመቆጠብ፤ 2. በምክክሩ ጊዜ መደማመጥን…
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

በአዲስ አበባ የተጀመረው የአጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ምን መልክ አለው?

በአዲስ አበባ የተጀመረው የአጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ከዛሬ ግንቦት 21 ጀምሮ ለ7 ተከታታይ ቀናት ይካሄዳል። በሂደቱ ከ2,500 በላይ ተሳታፊዎች ይሳተፋሉ።

በዋናነት ከዚህ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ምን ይጠበቃል?

- 2,500 ከሚሆኑት ተሳታፊዎች በቀጣይ ለሚደረገው ሀገራዊ ምክክር አዲስ አበባን ወክለው የሚሳተፉ ተወካዮች ይመረጣሉ

- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምክክር ጉባኤ ይሰየማል

- በአዲስ አበባ ደረጃ በሀገራዊ ምክክሩ ላይ መቅረብ አለባቸው የሚባሉ አጀንዳዎች ይዘጋጃሉ።

በእነዚህ 7 ቀናት ምክክር ኮሚሽኑ ምን ሊያከናውን አቅዷል?

#ቀን_1 እና #ቀን_2

- በመጀመሪያው ቀን በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ የምክክር ምዕራፉ መክፈቻ ሥነ-ስርአት ይካሄዳል። (ይሄ መርሐግብር ዛሬ ጠዋት በዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል)

ከመጀመሪያው ቀን የከሰዓቱ መርሐግብር ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ቀን መጨረሻ ድረስ፦

- 11 የሚሆኑት የህብረተሰብ ክፍሎች  ከ100 በማይበልጥ ቡድን ተከፍለው ይወያያሉ።

- እያንዳንዱ ቡድን ህበረተሰቡን ወክሎ በሚቀጥሉት የምክክር ሂደቶች ሊሳተፉ
የሚችሉ 22 እጩዎችን ይለያሉ።

#ቀን_3

- በቡድን ሲደረግ የነበረው ምክክር ውጤት በየተራ ለቤቱ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ይካሄድበታል።

- ከተለዩ እጩዎች ውስጥ 11 የህብረተሰቡ ወኪሎች በሚስጥር ድምጽ አሰጣጥ ይመርጣሉ፡፡

በዚሁ ቀን በተጓዳኝ በከተማ አስተዳደር ደረጃ የተወከሉ ቁጥራቸው 1,220 የሚደርሱ ባለድርሻ አካላት ውይይት ይደረጋል። (ባለድርሻ አካላት የሚባሉት ታዋቂ ሰዎች፤ ፖለቲከኞች ከተቋማትና ማኅበራት የሚሳተፉ አካላት ናቸው።)

#ቀን_4

ዋናው የመክፈቻ  ሥነ-ስርዓት (Launching Ceremony) ይከናወናል

- ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ዲፕሎማቶችና ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችን ጨምሮ 3,500 ተሳታፊዎች በዋናው የመክፈቻ  ሥነ-ስርዓት ላይ ተሳታፊ ይሆናሉ።

#ቀን_5

- ተሳታፊዎቹ በ5 ቡድን ( ከወረዳ የተወከሉ (ብዛት 121 )፤ መንግስት፤ የፖለቲካ ፖርቲዎች፤ መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት፤ ታዋቂ ሰዎች (ብዛት 1220) ተከፍለው የአጀንዳ ምክክራቸውን ይቀጥላሉ፤ አጀንዳዎቻቸውን ይለያሉ።

በተጨማሪ ከአምስቱ ቡድኖች በተናጠል የምክክር ውጤቶችን የሚያጠናክሩና የሚያዳዳብሩ 5 ተወካዮች በድምሩ 25 ተወካዮች ይመረጣሉ።

#ቀን_6

- ጠዋት 1,340 ተሳታፊዎችን የያዘ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምክክር ጉባኤ ይሰየማል፡፡ 

- 5ቱም ቡድኖች ለጉባኤው የምክክራቸውን ውጤት ሪፖርት ያቀርባሉ፤ በሪፖርቱ ላይም ውይይት ይደረጋል።

- ከየቡድኑ የተመረጡ 25ቱ ሰዎች በጋራ የ5ቱን ቡድኖች አጀንዳ አንድ ላይ በማምጣት ኮሚሽኑ ባስቀመጠው መሰፈርት መሰረት ያደራጃሉ፡፡

#ቀን_7

- 25ቱ ወኪሎች ያደራጆቸውን አጀንዳዎች ለጠቅላላ ጉባኤው ያቀርቡና ሙሉ ቀን ውይይት ይደረግበታል፡፡  

- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አጀንዳ ግብዓት ተለይቶ ለኮሚሽኑ ይሰጣል፡፡

- 25ቱ ተወካዮች የከተማ አስተዳደሩን የተጠቃለለ እጀንዳ ለማደራጀት ሦስት መስፈርቶች ይጠቀማሉ። እነዚህም አስቸኳይ ፤ አስፈላጊ እና  ከፍተኛ ውክልና ያለው በሚል የሚለዩ ይሆናሉ።

#TIKVAHETHIOPIA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢንተርን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንተር ሀኪሞች ከስራ ሰዓትና ክፍያ ጋር በተያያዘ ቅሬታ እንዳላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ኢንተርን ሀኪሞቹ ምን አሉ ? “ ከጥቂት ዓመታት በፊት የሆስፒታሉ የኢንተርን ሀኪሞች የሥራ ሰዓት ወደ 24 ሰዓታት ዝቅ እንዲል ተደርጎ ነበር። ነገር ግን የኮሌጁ ግለሰብ / #ዳይሬክተር ሲቀየር በራሱ ውሳኔ የራሱን መላምት በመፍጠር መልሶ ወደ 36 ሰዓታት ከፍ አድርጎታል።…
#ኢንተርን #UoG

“ በኢንተርን ምዘና የተጻፈ መስፈርት የለም ” - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንተርን ሀኪሞች

“ ቢሮ መጥተው ይጠይቁ ” - ዩኒቨርሲቲው

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ2016/17 ዓ/ም ኢንተርን ሀኪሞች ፦
- በኢንተርንሽፕ ምን ያህል መስራትና መማር እንዳለብን፣
- ምን መስራትና ምን እውቀት ማምጣት እንዳለብን፣
- በኢንተርን ምዘና የተፃፈ ሰዓትና መስፈርት ባለመኖሩ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎቲው ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው ለህክምና መስጫ ተረኛ አዳሪ እረፍት (Day off) እንዲሰጣቸው ኢንተርን ከመጀመራቸው ከሳምነት በፊት በደብዳቤ በመጠየቃቸው የ3 ወራት ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

“ ሥራ ከመጀመራችን ከ3 ቀናት በፊት በሥራና ትምህርት ገበታችን ላይ እንደማንገኝ በደብዳቤ አሳውቀን ከትምህርት ገበታችን ሳንገኝ ቀርተናል ” ብለው ፣ በዚህም የ3 ወራት ደመወዛቸው እንደተቆረጠና ሥራ ቢጀምሩም እንዳልተከፈላቸው አስረድተዋል።

ለተከታታይ 34 ሰዓታት ያለ እረፍት መስራት፣ በሳምንት ከ90 - 94 ሰዓታት መስራት፣ አለፍ ሲልም እስከ 118 ሰዓታት በመስራት አስቸጋሪና ከአቅም በላይ የሆነው አሰራር ካልተቀየረ፦
📌 የአእምሮ መዛል፣ የመንፈስ መቃወስ የሚስከትል
📌 የህክምና ስህተት የሚፈጥር
📌 ከሥራ በቂ እውቀት የማያስገኝ
📌 የእኩልነት መብት የሚጥስ መሆኑን በማስረዳት ሥራና ትምህርት ከመጀመራቸው በፊት ጠይቀው በሥራ ጫናና በሌሎች ምክንያቶቾ ጥያቄውን ክትትል ሳያደርጉበት እንደቆዩ አስረድተዋል። 

“ ሆኖም ግን በጥያቄው ዙሪያ ተወያይተን መፍትሄ እናገኛለን ብለን ስንጠብቅ ቅጣት ተጣለብን ” ብለው፣ ለ4 ቀናት ከቆዩ በኋላ ወደ ሥራ ገበታ ቢመለሱም የ3 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው ተናግረዋል።

የኢንተርን ምዘና መስፈርቱን፣ የሥራና መማሪያ ሰዓት ገደብ አለመቀመጡን በተመለከተ ለተነሳው ቅሬታ ምላሽ የጠየቅናቸው የጤና ሳይንሱ አካል ዶክተር ሙሉጌታ፣ “ ይህን ጥያቄ ካላቸው ቢሮ መጥተው ይጠይቁ ” ብለዋል።

“ ተገቢ ዶክሜንት አለ። ስርዓተ ትምህርቱ አለ። ይህን የሚያስፈጽሙ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች አሉ። በእነርሱ በኩል መልስ እንሰጣለን ” ሲሉ አክለዋል።

የደመወዝ መቆረጡን በተመለከተ በሰጡት ቃልም፣ “ ነገሩን ለማሳጠር ያህል ባለፈው ዶክተር አይንሸት የሰጠው መልስ ተገቢ ነው። የተለዬ መልስ ተጨማሪ መረጃ የለኝም ” ነው ያሉት።

ዶ/ር አይንሸት የደመወዝ ቅሬታውን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ የኢንተርን ሀኪሞቹ ጥያቄ አቀራረብ ልክ ባለመሆኑ የ3 ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው ገልጸው ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Attention ⚠️

" ራኒቲዲን #ካንሰርን ሊያመጣ የሚችል ንጥረ ነገር በውስጡ በመገኘቱ ምክንያት #ታግዷል " - የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን

ለጨጓራ ተያያዥ ህመሞች በመድኃኒትነት ጥቅም ላይ ሲውል የነበረው ' ራኒቲዲን ' የተባለው መድሃኒት በኢትዮጵያ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውል #ማገዱን የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

የባለስልጣኑ የመድኃኒት ደህንነት ክትትልና የሕክምና ሙከራ መሪ ስራ አስፈጻሚ አስናቀች ዓለሙ ፤ " በመጀመሪያ ደረጃ በሌሎች ሀገር የወጡ ሪፖርቶችን አይተን ነበር። ስለዚህ በሀገራችንስ ይሄ መድሃኒት እንዴት ነው ? የሚለውን በማገናዘብ የላብራቶሪ ምርመራ አድርገናል " ብለዋል።

በዚህም መድሃኒቱ ካንሰር ሊያመጣ የሚችል ' N-nitrosodimethylamine ወይም NDMA ' የተሰኘ ንጥረ ነገር እንደተገኘበት መሪ ስራ አስፈፃሚዋ ገልፀዋል።

" በመሆኑም ይህንን መድሃኒት ከምዝገባ ፋይላችን አውጥተናል። የተሰራጩ መድሃኒቶችም #እንዲሰበሰቡ እና ጥቅም ላይ እንዳይውሉ መልእክት አስተላልፈናል " ብለዋል።

" በዚህ በሰረትም ጥቅም እንዳይውል #ታግዷል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

" የጤና ባለሙያዎችም፣ የጤና ተቋማትም ሌሎች አማራጭ መድሃኒቶችን እንዲያዙ እና እንዲጠቀሙ ይህንን መድሃኒት #እንዳይጠቀሙ " ሲሉም አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2024/05/30 02:37:46
Back to Top
HTML Embed Code: