Telegram Group Search
#ሴጅ_ማሠልጠኛ

20% ቅናሽ ከሰኔ 01-21/2016 ዓ.ም ለሁሉም ተመዝጋቢዎች።
ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principles and Practices of Accounting) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ

Telegram: https://www.tg-me.com/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin:
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#INSA

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ያዘጋጀው የ2016 ዓ/ም “ ብሄራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ” ፕሮግራም ምዝገባ እስከ ሰኔ 10/2016 ዓ/ም ድረስ መራዘሙን አሳውቋል።

እስካሁን በርካታ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።

ምዝገባው እስከ ሰኔ 10 ድረስ መራዘሙ ተጠቁሟል።

በሳይበር ደህንነት እና በተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶች እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።

የታለንት መስኮች ፦

- Cyber Security
- Cyber Development
- Embedded Systems
- Aerospace ሲሆኑ ስልጠናው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለ1 ወር ይሰጣል።

ተመራቂዎች ፦

° #እንደየችሎታቸው እና #እንደስራዎቻቸው ከተለያዩ ባለሀብቶች ጋር የማስተሳሰር፤

° ኢመደአን (INSA) ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ውስጥ ተቀጥረው መስራት የሚችሉበት ሁኔታ እንደሚማቻች ከተቋሙ ተሰምቷል።

የመመዝገቢያ ፖርታል ፦ https://talent.insa.gov.et

NB. እድሜ ፦ ከ11 አመት ጀምሮ ( #ኢትዮጵያውያን)

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በአላማጣ ከተማ የተፈጠረው ምንድን ነው ?

በአማራ ክልል በኩል እንደሆኑና የራያ አላማጣ አካባቢ አመራር እንደሆኑ የገለጹ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ አመራር ፥ " የሕወሓት ታጣቂዎች አላማጣ በሚገኙ ነዋሪዎች ላይ  የግድያ ጥቃት እየሰነዘሩ ነው " ሲሉ ከሰዋል።

እኚሁ ስሜ አይጠቀስ ያሉ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " ከሰሞኑን አንድ ወጣት በሕወሓት ታጣቂዎች በግፍ ተገሏል " ብሏል።

በታጣቂዎች የተገደለው ወጣት ስሙ ያሬድ መልካሙ እንደሚባል ፤ የመብራት ሀይል ሰራተኛም እንደነበር ፤ መብራት ለመስራት ወጥቶ ታጣቂዎች በግፍ እንደገደሉት አስረድተዋል።

ከሳምንት በፊትም " የሕወሓት ታጣቂዎች በወረወሩት ቦንብ ሁለት ሰዎች ሞተዋል። ሁለቱ ደግሞ ቆስለዋል " የሚል ቃል ሰጥተዋል። 

የሰሞኑን የአንድ ሰው ግድያ ተከትሎ የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ለሁለት ቀናት ሰላማዊ ሰልፍ እንደወጡ የቪድዮ ማስረጃ በመላክ ሁኔታውን አስረድተዋል።

አሁን ላይ የአላማጣ ከተማ ከንቲባ እንደሆኑ የገለጹት ዝናቡ ደስታ (ከትግራይ በኩል) ከሁለት ሳምንት በፊት በከተማው ጤና ጣብያ ፊት ለፊት ላይ በሚገኝ መጠጥ ቤት የቦንብ ጥቃት ተፈጽሞ የአንድ እናት ህይወት መጠፉቱን እና ሁለት ሰዎች መቁሰላቸውን አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአሁን ሰዓት አላማጣን #በከንቲባነት የሚመራትን አካል በተመለከተ ውዝግቦች የሚስተዋሉ ሲሆን ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አሁን ከተማዋን በከንቲባት የሚመራት ማነው ? ሲል የአማራ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮን ጠይቋል።

ቢሮው ምላሹ፣ " እኛ የምናውቀው ከተማው በክልላችን ስር እንዳለ ነው። ስለዚህ ከዚያ ውጪ ያለው ነገር #ምኞት_ብቻ_ነው " ብሏል።

በትግራይ በኩል ያለውን ምላሽ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል።

በአማራና ትግራይ ክልሎች መካከል የይባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው የራያ አላማጣ አካባቢዎች ከሰላም ስምምነቱ ወዲህም ከወራት በፊት በትግራይና አማራ ሚሊሻዎች በተደጋጋሚ የተኩስ ልውውጥ መደረጉ አይዘነጋም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Yemen

በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን የሆኑ ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ከየመን የባሕር ዳርቻ አቅራቢያ ተገልብጣ 39 ሰዎች ሞቱ።

እንደ IOM እና ከአደጋው ከተረፉ ሰዎች በተገኘ መረጃ ጀልባዋ 260 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍራ የነበር።

በካባድ ነፋስ ምክንያት መገልበጧ ተጠቁሟል።

መሞታቸው ከታወቀው 39 ሰዎች ውጪ ሌሎች 150 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም። እነሱን ለማግኘት ፍለጋ እየተደረገ ነው።

71 ሰዎች ከአደጋው ተርፈዋል።

የሩደም አካባቢ ባለሥልጣናት ጀልባዋ ላይ ተሳፈረው ከነበሩት 260 ስደተኞች በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደነበሩ አመልክተዋል።

#Reuters #IOMYemen #IOMspokesperson

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ክልል እና ከተማ አቀፉ የ8ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ መሰጠት ጀምሯል።

ፈተናው በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች (አዲስ አበባ እንዲሁም ድሬዳዋ) ዛሬ መሰጠት ጀምሯል።

ፎቶ ፦ ደሴ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሕዝብ_በዓላት_እና_የበዓላት_አከባበር_ረቂቅ_አዋጅ_.pdf
#Update

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ #አጽድቋል

ረቂቅ አዋጁ የተወሰኑ ማስተካከያዎች እንደተደረጉበት ተመላክቷል።

አዋጁ በ1 ድምፀ ተቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ " አዋጅ ቁጥር 1334/2016 " ሆኖ ነው የጸደቀው።

የጸደቀው አዋጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሕዝብ በዓላት እና የበዓላትን አከባበር የሚመለከት ሲሆን ፤ ክልሎች በራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ ህግ አውጥተው በክልል ደረጃ የሚከበሩ አዋጆችን አከባበር መወሰን ይችላሉ ተብሏል።

ይህ የሚመለከተው እንደ ኢሬቻ፣ ጊፋታ፣ ጨምባላላ፣ አሸንዳ ፣ ሻደይ ፣ አሸንድዬ ፣ ...ሌሎችንም ሲሆን ክልሎች በራሳቸው አዋጆችን አውጥተው አከባበሩን መወሰን እንደሚችሉ ተመላክቷል።

https://www.tg-me.com/TIKVAH ETHIOPIA/com.tikvahethiopia/87926

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ #አጽድቋል። ረቂቅ አዋጁ የተወሰኑ ማስተካከያዎች እንደተደረጉበት ተመላክቷል። አዋጁ በ1 ድምፀ ተቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ " አዋጅ ቁጥር 1334/2016 " ሆኖ ነው የጸደቀው። የጸደቀው አዋጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሕዝብ በዓላት እና የበዓላትን አከባበር የሚመለከት…
#Ethiopia

የህዝብ በዓላት እና የበዓላት አከባበርን ለመወሰን የወጣው አዋጅ በዛሬው እለት ጸድቋል።

ስለ አዋጁ ...

➡️ በልማድ ሲከበር የቆየውን " ግንቦት 20 " ብሔራዊ በዓልነቱ #አስቀርቷል፡፡ 

➡️ የሰማዕታትን ቀን ( #የካቲት_12 ) እና የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች ( #ህዳር_29 ) መስሪያ ቤቶች ክፍት ሆነው፤ #ታስበው ይውላሉ።

➡️ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ቀን ፣ የሰንደቀ አላማ ቀን ፣ የሴቶች ቀን ፣ የአፍሪካ ቀን ሌሎችም ታስበው ይውላሉ።

➡️ የዘመን መለወጫ (እንቁጣጣሽ) በዓል በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት ይከበራል።

➡️ ተከብረው በሚሉ ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላት ለሕዝብ አገልግሎት ክፍት መደረግ ያለባቸው ተቋማት ዝርዝር ተቀምጧል።

በዚህም  ፦
° የውሃ
° የመብራት
° የስልክ
° ሚዲያዎች (ቴሌቪዥን፣ ሬድዮ)
° የጤና ተቋማት እና መድሃኒት ቤቶች
° መከላከያ
° ፖሊስ
° ደህንነት
° የእሳት አደጋ መከላከል
° የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎቶች
° ነዳጅ ማደያዎች
° ሙዝየሞች ፣
° ፓርኮች ክፍት ሆነው ከሚውሉት ውስጥ ናቸው።

ስለ አዋጁ ምን ጥያቄ ተነሳ ?

አንድ የምክር ቤት አባል ፦

" የብሔር ብሔረሰቦችን በዓል ተከብረው ከሚውሉት በዓላት ለምን አልተካተተም ? ለምን ታስቦ ከሚውል ውስጥ ተካተተ ? ምክንያቱም ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች ሀገር ነች !! ታስቦ ይውላል እና ተከብሮ ይውላል የሚለው የተለያየ አጀንዳ አለው " የሚል ጥያቄ አንስተው ነበር።

የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ከኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ወርቅሰሙ ማሞ አንድ በዓል እንዲከበር እና ታስቦ እንዲውል የሚያደርገው የሚያመጣው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ተጠንቶ ነው ብለዋል፡፡

" ኢኮኖሚያችንስ ? " ሲሉ የጠየቁት ወ/ሮ ወርቀሰሙ " ሁል ጊዜ ስራ እየዘጋን ፤ በዓል እያከበርን መዋል በኢኮኖሚው ላይ የሚያመጣው ከፍተኛ ጫና አለ። ስለዚህ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ህዝቦች በዓል ታስቦ የሚውል በተለያዩ ነገሮች ደምቆ የሚውል ሊሆን ይችላል በሚል ነው በታሳቢነት እንዲቀጥል የተደረገው " ሲሉ አስረድተዋል።

#ShegerFM #TikvahEthiopia #HoPR

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፓይለቱ ወደ ኃላ እንዲመለስ ተነግሮት ነበር ፤ ከዛ በኃላ ግን አውሮፕላኑ የት እንደገባ አልታወቀም " - የማላዊ ፕሬዜዳንት የተሰወረው የማላዊ አውሮፕላን አልተገኘም። በአውሮፕላኑ ውስጥ ከም/ፕሬዜዳንቱ ጋር የቀድሞው ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ ባለቤት / የቀድሞ ቀዳማዊ እመቤት ሻኒል ዲዚምቢሪ እንደሚገኙበት ተነግሯል። አንዳንድ ሚዲያዎች እና የቀድሞ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ " በጣም ድቅድቅ…
#Update

የማላዊ ምክትል ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናትን ይዞ ሲጓዝ የነበረውን ከራዳር እይታ የተሰወረው አውሮፕላን #ስብርባሪ ተገኘ።

አውሮፕላኑ መከስከሱ ተረጋግጧል።

ምንም የተረፈ ሰው የለም።

በአውሮፕላኑ ውስጥ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ሳውለስ ቺሊማን እና የቀድሞው ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ ባለቤት / የቀድሞ ቀዳማዊ እመቤት ሻኒል ዲዚምቢሪን ጨምሮ 10 ሰዎች ነበሩ።

ሁሉም መሞታቸው ነው የተሰማው።

Photo Credit - Hopewell

@tikvahethiopia
#አፊኒ #ሲዳማ

በሲዳማ በህዝብ ዘንድ ቁጣ ፈጥሯል የተባለው መፅሀፍ ጉዳይ ምንድነው ?

ከሰሞኑ በዶ/ር አራርሶ ገረመዉ የተጻፈ " አፊኒ " የተሰኘ መጽሀፍ በአእምሮአዊ ንብረት ባለስልጣን ተመዝግቦ የባለቤትነት ፈቃድ ማግኘቱን ተከትሎ በሲዳማ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በኩል ጥያቄ ተነስቷል።

ቢሮው ለአእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን በላከው የቅሬታ ደብዳቤ " ለዶክተር አራርሶ ገረመዉ ' አፊኒ ' በሚል ስያሜ የተሰጠው የባለቤትነት እዉቅና በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል " በማለት ገልጿል።

የተሰጠዉ እውቅና " የባለቤት " የሚል ሀሳብ የያዘ ሲሆን ይህም የድርሰት ስራ በመሆኑ የቅጅና ተዛማጅ መሆን እንደሚገባዉና " የፈጠራው ባለቤት " የሚለው ቃልም አግባብ አይደለም በማለት ገልጿል።

በመሆኑም ' አፊኒ ' የመላዉ የሲዳማ ህዝብ እንጅ የደራሲዉ የዶ/ር አራርሶ ገረመዉ የፈጠራ ንብረት አለመሆኑ ታዉቆ ማስተካከያ እንዲደረግ በማለት ማብራሪያና ማስተካከያ ጠይቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ጉዳዩን ሰምቶ የመጽሀፉን ደራሲ አነጋግሯል።

ዶ/ር አራርሶ ገረመው ፤ የተፈጠረዉ ሁኔታ ከርሳቸዉ ቀድሞ ሶሻል ሚዲያዉን ማጥለቅለቁን ገልጸዋል ፤ " በዚህም አዝኛለሁ " ብለዋል።

ሁኔታውን በንግግር እንደፈቱት ገልጸው ጥያቄውን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ለመመለስና ማህበረሰቡን ለማስቀደም በማሰብ ' አፊኒ ' የሚለዉ ርእስ እንዲስተካከል በመወሰን ስራ መጀመራቸውን አስረድተዋል።

' አፊኒ ' የሚለው ርዕስ ተቆርጦ የወጣ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር አራርሶ ፥ አሁን ላይ መጽሀፉ ላይ ያለው ሙሉ አርእስት ' አፊኒ የሲዳማ ድንቅ ባህል ታላቅ ተቋም አስደማሚ የሰላም እሴት ' በሚል ለማስተካከል በደብዳቤ የአእምሯዊ ንብረት ባለስልጣንን መጠየቃቸውን ባለስልጣኑም እንደተቀበላቸውና ማስተካከያ እንደተደረገበት ገልጸዋል።

" ይህንን መጽሐፍ የጻፍኩት #የህዝቤን_ታሪክ ለማስተዋወቅ እና ለማጉላት መሆኑን በውስጡ ያሰፈርኩት አሳብ ይመሰክራል " ያሉት ደራሲው " በርዕሱ ምክኒያት የተፈጠረውን ቅራኔ በቀላሉ ከፈቃድ ሰጪው ጋር ተነጋግሮ መፍታት የሚቻል ቢሆንም በማህበራዊ ሚድያ የጥቂቶች ሀሳብ በዚህ ደረጃ መንጸባረቁ አስገርሞኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
አዳዲስ የአይቴል ስልኮችን በተመጣጣኝ ዋጋ!

ሁለት ሲምካርድ የሚቀበሉ፣ ኤፍ.ኤም ሬዲዮን ጨምሮ የተለያዩ ተጨማሪ ገጽታዎችን የተላበሱ አይ.ቲ 2163 እና አይ.ቲ 5027 የአይቴል ስልኮችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረባችንን በደስታ እንገልፃለን፡፡

በአቅራቢያዎ በሚገኙ የአገልግሎት ማዕከሎቻችን ያገኟቸዋል!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #SmartAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ለ2017 በጀት አመት 1 ትሪሊዮን የሚጠጋ በጀት ቀረበ። ዛሬ የሚኒስትሮች ም/ቤት ስብሰባ ተቀምጦ ነበር። በዚህም ስብሰባው ላይ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል። ከውሳኔዎቹ አንዱ ደግሞ የ2017 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ የበጀት አዋጅ ነው። በዚህም ፦ ➡️ ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች ፣ ➡️ ለካፒታል ወጪዎች ፣ ➡️ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ፣ ➡️ ለዘላቂ የልማት…
#Ethiopia

የፌዴራሉ መንግሥት የ2017 ጠቅላላ የወጪ በጀት 971.2 ቢሊዮን ብር ሆኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል።

ለክልል መንግሥታት የበጀት ድጋፍ የተመደበው 236.7 ቢሊዮን  ብር ነው።

አጠቃላይ የ2017 በጀት (971.2 ቢሊዮን) በ2016 በጀት ዓመት ከጸደቀው የወጪ በጀት አንጻር የ21.1 በመቶ እድገት እንዳለው  ተገልጿል።

ዛሬ ከሰዓት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ምክር ቤት ቀርበው በረቂቅ በጀቱ ዙሪያ ከምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በዚህም ወቅት ሚኒስትሩ ከ971.2 ቢሊዮን የወጪ በጀት ፦
451.3 ቢሊዮን ብር ለመደበኛ
283.2 ቢሊዮን ብር ለካፒታል
236.7 ቢሊዮን ብር ለብሔራዊ ክልላዊ መንግሥታት የበጀት ድጋፍ የተመደበ እንደሆነ አሳውቀዋል።

ለክልል መንግሥታት ከተመደበው ጠቅላላ የበጀት ድጋፍ ውስጥ 14 ቢሊዮን ብሩ የዘላቂ የልማት ግቦችን ለማስፈጸሚያ የሚውል ነው።

ከጠቅላላው የፌዴራል መንግሥት በጀት ከፍተኛውን ድርሻ (የጠቅላላውን 46.5 በመቶ) የያዘው ለመደበኛ በጀት የተመደው እንደሆነ የገንዘብ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ለመደበኛ ወጪ የተያዘው የበጀት ድልድል ሲታይ 127.2 ቢሊዮን ብሩ (28.2 በመቶ) ፦
° #ለደመወዝ
° #ለአበል እና ለልዩ ልዩ ክፍያዎች ተመደበ እንደሆነ ተናግረዋል።

ቀሪው 321.4 ቢሊዮን ብር ለስራ ማስኬጅ የተመደበ እንደሆነ ገልጸዋል።

ለመደበኛው ወጪ ከተደለደለው በጀት ለእዳ ክፍያ የተያዘው 139.3 ቢሊዮን እንደሆነም አመልክተዋል።

ለእዳ ክፍያ ከተያዘው ውስጥ 54.8 በመቶ ለሀገር ውስጥ እዳ ክፍያ ፤ ቀሪው 45.2 በመቶ ለውጭ ሀገር እዳ ክፍያ እንደሚውል ገልጸዋል።

ለፌዴራል መንግሥት ካፒታል በጀት የተመደበው 283.2 ቢሊዮን ብር ሲሆን የወጪ አሸፋፈኑ ሽፋን ሲታይም ፦
° 216.5 ቢሊዮን ብር ከትሬዠሪና ከመስሪያ ቤቶች የውስጥ ገቢ ፤
° 39.8 ቢሊዮን ብር ከፕሮጀክት እርዳታ
° 26.9 ቢሊዮን ብር ከፕሮጀክት ብድር ለመሸፈን የተያዘ እንደሆነ አብራርተዋል።

ከጠቅላላይ የካፒታል በጀት ውስጥ 187.1 ቢሊዮን ብር ቅድሚያ ትኩረት ለተሰጣቸው ፦
ለመንገድ
ለትምህርት
ለግብርና እና መስኖ
ለመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን
ለጤና
ለገጠር እና ከተማ ልማት ሴፍቲኔት ማስፈጸሚያ የተመደበ ነው ብለዋል።

በጦርነት ምክንያት የወደመውን ንብረት እና አገልግሎት ማስጪያ ተቋማትን ወደነበሩበት ለመመለስ እና ለማቋቋም ለተጀመረ ፕሮጀክት ከመንግሥት ትሬዠሪ ብድር 20 ቢሊዮን ተደግፎ መቅረቡን አሳውቀዋል።

የቀረበው ረቂቅ በጀት ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የፌዴራሉ መንግሥት የ2017 ጠቅላላ የወጪ በጀት 971.2 ቢሊዮን ብር ሆኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል። ለክልል መንግሥታት የበጀት ድጋፍ የተመደበው 236.7 ቢሊዮን  ብር ነው። አጠቃላይ የ2017 በጀት (971.2 ቢሊዮን) በ2016 በጀት ዓመት ከጸደቀው የወጪ በጀት አንጻር የ21.1 በመቶ እድገት እንዳለው  ተገልጿል። ዛሬ ከሰዓት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ምክር…
#ብር #ዶላር

የፌዴራል መንግሥት #የ2017_በጀት ሲዘጋጅ ብርን ከዶላር አኳያ ያለውን የምንዛሬ ተመን #የሚያዳክም ውሳኔ ተግባራዊ ይደረጋል በሚል ታሳቢነት እንዳልሆነ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ለተወካዮች ም/ ቤት ተናግረዋል።

በኢ-መደበኛው እና በባንኮች በሚደረግ ይፋዊ ምንዛሬ (official exchange) መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ እርምጃን አስመልክቶ  " ምንም የቀረበ ነገር የለም "  ብለዋል።

አቶ አህመድ ፥ የፌዴራል መንግሥት በጀት የተዘጋጀው " የነበረው አካሄድ #እንደሚቀጥል ታሳቢ ተደርጎ " ሲሉ ገልጸዋል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ " ዘንድሮ የነበረውን ይፋዊ የውጭ ምንዛሬ መጠን (official exchnage rate) ታሳቢ አድርጎ ነው በጀቱ የቀረበው " ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህን ማብራሪያ የሰጡት በም/ቤቱ የኢዜማ ተወካይ ዶ/ር አብርሃም በርታ ፥  " ህጋዊውን እና ኢ-መደበኛውን የውጭ ምንዛሬ ገበያ እኩል ለማድረግ የሚደረጉ ሙከራዎች እንዳሉ ከአንዳንድ ወገኖች እየሰማን ነው ፤ ... የውጭ መንግስታት #በብድር_ምክንያት በኢትዮጵያ ላይ ጫና በመፍጠር ይህንኑ ለማስፈጸም እንደሚንቀሳቀሱ የሚገልጹ መረጃዎችም አሉ ፤ እንዲህ አይነቱ እርምጃ የማንወጣው ችግር ውስጥ ይከተናል የሚል የባለሙያዎች ትንታኔ አለ " በማለት ላነሱት ሀሳብ ነው።

#EthiopianInsider #HoPR #TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የፌዴራሉ መንግሥት የ2017 ጠቅላላ የወጪ በጀት 971.2 ቢሊዮን ብር ሆኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል። ለክልል መንግሥታት የበጀት ድጋፍ የተመደበው 236.7 ቢሊዮን  ብር ነው። አጠቃላይ የ2017 በጀት (971.2 ቢሊዮን) በ2016 በጀት ዓመት ከጸደቀው የወጪ በጀት አንጻር የ21.1 በመቶ እድገት እንዳለው  ተገልጿል። ዛሬ ከሰዓት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ምክር…
#Ethiopia

የደቡብ ክልል ፈርሶ እንደ አዲስ የተዋቀሩት #ሁሉም አዳዲስ ክልሎች በጀት የሚደለደልላቸው በነበረው የድሮ ቀመር እንደሆነ ተገልጿል።

ገንዘብ ሚኒስቴር #አዲስ_ቀመር የማዘጋጀት ምንም ስልጣን እንደሌለው ይህ ስልጣን የፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሆነ አመልክቷል።

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የ2017 በጀት ረቂቅን ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባብራሩበት ወቅት ስለ አዳዲሶቹ ክልሎች የበጀት ድልድል ቀመር ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

" ከደቡብ አደረጃጀቶች ጋር በተያያዘ #የትኛው_ቀመር ነው ? የሚለው የምክር ቤቱ ስልጣን እንጂ የገንዘብ ሚኒስቴር ስልጣን አይደላም " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

" አዲስ ቀመር በሀገር አቀፍ ደረጃ ተጠንቶ ተግባራዊ እስኪሆን ድረስ የነበረው ቀመርና በፌዴሬሽን ም/ቤት በፀደቀው መሰረት ነው ገንዘብ ሚኒስቴር ድልድል የሚያደርገው " ብለዋል።

ሚኒስትሩ ፥ ሁሌም የፌዴራል መንግሥት #ለክልሎች አጠቃላይ ምን ያህል በጀት ይመደብ ? በሚል ካለው አቅም አንጻር እንደሚያስቀምጥ አስረድተዋል።

አሁን የተበተኑት ክልሎች በደቡብ ክልል ስር አንድ ላይ በነበሩበት ጊዜ የወጣ ቀመር እንዳለ አስታውሰዋል።

አሁን እየተሰራበት ያለው ያ የቀድሞው ቀመር እንደሆነ ጠቁመዋል።

ቀመሩ ምንድነው ?

አሁን እየተገበረ ያለው ቀመር የቀድሞው ደቡብ ክልል የነበረው በጀት ለአራቱ ክልሎች #ይከፋፈላል

መጀመሪያ ሲዳማ ሲወጣ ratio ተሰርቶ በዛ መንገድ ነው የተሰራው።

ደቡብ ምዕራብ ሲወጣም ratio ተሰርቷል።

ሌሎቹ ሁለቱም ሲወጡ ማለትም ደቡብ ኢትዮጵያ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ በተመሳሳይ ratio ተሰርቶ በዛ መንገድ ነው ድልድል የሚደረገው።

ይህ ደግሞ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት ነው የተካሄደው።

የነበረው ቀመር ማለት በአጭሩ ደቡብ ክልል በአንድ ላይ በነበረበት ወቅት ይመደብለት የነበረው በጀት በ ratio ለአዳዲሶቹ እንዲከፋፈል ይደረጋል።

አቶ አመህድ ገንዘብ ሚኒስቴር አዲስ ቀመር ተገዛጅቶ ተግባር ላይ እስካልዋለ ይህኑን ተፈጻሚ እንደሚያደርግ አሳውቀዋል።

" በቀጣይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ህዝብ ቆጠራ አልቆ ፣ አጠቃላይ የeconomic census እና survey በሚገባ ተጠናቆ ፤ አዲስ ቀመር በሚዘጋጅበት ጊዜ እና የተሟላ ቀመር ሲኖር አዲሱን ቀመር መሰረት በማድረግ ተግባራዊ   ይደረጋል (የበጀት ድልድሉ) " ብለዋል።

አዲስ ቀመር #የማዘጋጀት_ስልጣን ደግሞ የገንዘብ ሚኒስቴር ሳይሆን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣን እንደሆነ ተናግረዋል።

በአዳዲሶቹ ክልሎች ከበጀት ጋር በተያያዘ ፤ " የበጀት እጥረት " የሚሉ ጥያቄዎች እንደሚነሱ ይታወቃል።

የመንግሥት ሰራተኞች ደሞዝ መዘግየትና በአግባቡ አለመክፈልም በስፋትም ከአዳዲሶቹ ክልሎች የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
2024/06/12 00:03:20
Back to Top
HTML Embed Code: