Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-93782-93783-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/93783 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ጉዳዩ ዓለም አቀፍ የወንጀል ገጽታ ያለው ነው " -  የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር

የታገቱት ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው

" በህገወጥ ዓለምአቀፍ ደላሎች ተታለው ወደ ማይናማር ፣ ታይላንድ፣ ቻይና ድንበር አዋሳኝ አካባቢዎች ወደሚገኙ ህገወጥ ካምፓች ተወስደው የሚገኙ ዜጎችን ለማስመለስ በመንግስት የተጀመሩ ጥረቶች ቀጥለዋል።

ጉዳዩ ዓለም አቀፍ የወንጀል ገጽታ ያለው ነው።

እስካሁን በምናደርገው እንቅስቃሴ የ19 ሀገራት ዜጎች ተመሳሳይ በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ተታለውና ታግተው ወደ ማይናማር በመግባት ለከፋ ችግር የተዳረጉ መሆኑን ለመረዳት ችለናል።

ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ በማይናማር 380 የሚል ቁጥር ተጠቅሷል ይሄ የቁጥር የተወሰደው እዚህ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ ዜጎች ልጆቻቸው ታግተው እዚህ መጥተው ካመለከቱት ነው።

በዚህ መሰረት ክትትል ለማድረግ እንዲረዳን ቶኪዮ ለሚገኘው ኤምባሲያችን የተላለፈው ቁጥር ይህ ነው። ትክክለኛው የታጋቾች ቁጥር አይታወቅም።

ቶኪዮ የሚገኘው ኤምባሲያችን ከማይናማር ኤምባሲ ጋር ዜጎቻችንን ለማዳን በትብብር እየሰራ ነው። የ380 ዜጎች ስም ዝርዝር እና ፓስፖርት ኮፒ ቶኪዮ ለሚገኘው የማይናማር ኤምባሲ እንዲደርስ ተደርጓል።

የማይናማር መንግሥት ታጋቾችን ለመልቀቅ ጠረት በማድረግ ላይ ሲሆን ከአጋቾች አምልጠው ለመንግሥት እጅ የሚሰጡ ዜጎች ምህረት በማድረግ በነጻ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ትብብር በማድረግ ላይ ይገኛል።

ፈታኝ የሆነው ዋናው ጉዳይ የታገቱት ዜጎች የሚገኙት በማይናማር እና ታይላንድ መካከል በሚገኙ ከማይናማር መንግሥት ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ስፍራዎች መሆኑ ነው። ይህ ስራውን አክብዶታል።

ሌላው ፤ በዚህ ኢሰብዓዊ ወንጀል ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ሀገራት ሰው አዘዋዋሪዎች ተቀራርበው እየሰሩ መሆኑ ነው።

እስካሁን መንግሥት ከዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች ጋር ጭምር ባደረገው ጥረት በ6 ወር ውስጥ 34 ዜጎች ከአጋቾች ነጻ ወጥተው ወደ ታይላንድ እና ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ተደርጓል።

ከአጋቾች አምልጠው ህጋዊ ሰነድ ስለሌላቸው በእስር ቤቶች ታስረው የነበሩ 7 ዜጎቻችንም በምህረት እንዲለቀቁ ማድረግ ተችሏል።

ዜጎችን የመታደጉ ስራ ብዙ ጥረትን የሚጠይቅ በመሆኑ ቶኪዮ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ሚስዮን በተጨማሪ በኒዉዴልሂ የሚገኘው ኤምባሲም ተልዕኮ ተሰጥቶት መንቀሳቀስ ጀምሯል " ብለዋል።

NB. አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ወጣቶች ደህንነቱ ወዳልተጠበቀ ስፍራ እየሄዱ ያሉት ከስራ ቅጥር ጋር ተያያዥ በሆኑ የማተለያ ስልቶች በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል። የችግሩን ምንነት እና አስከፊነት ህብረተሰቡ እንዲያውቅ የማድረጉን ስራ ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia



tg-me.com/tikvahethiopia/93783
Create:
Last Update:

" ጉዳዩ ዓለም አቀፍ የወንጀል ገጽታ ያለው ነው " -  የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር

የታገቱት ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው

" በህገወጥ ዓለምአቀፍ ደላሎች ተታለው ወደ ማይናማር ፣ ታይላንድ፣ ቻይና ድንበር አዋሳኝ አካባቢዎች ወደሚገኙ ህገወጥ ካምፓች ተወስደው የሚገኙ ዜጎችን ለማስመለስ በመንግስት የተጀመሩ ጥረቶች ቀጥለዋል።

ጉዳዩ ዓለም አቀፍ የወንጀል ገጽታ ያለው ነው።

እስካሁን በምናደርገው እንቅስቃሴ የ19 ሀገራት ዜጎች ተመሳሳይ በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ተታለውና ታግተው ወደ ማይናማር በመግባት ለከፋ ችግር የተዳረጉ መሆኑን ለመረዳት ችለናል።

ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ በማይናማር 380 የሚል ቁጥር ተጠቅሷል ይሄ የቁጥር የተወሰደው እዚህ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ ዜጎች ልጆቻቸው ታግተው እዚህ መጥተው ካመለከቱት ነው።

በዚህ መሰረት ክትትል ለማድረግ እንዲረዳን ቶኪዮ ለሚገኘው ኤምባሲያችን የተላለፈው ቁጥር ይህ ነው። ትክክለኛው የታጋቾች ቁጥር አይታወቅም።

ቶኪዮ የሚገኘው ኤምባሲያችን ከማይናማር ኤምባሲ ጋር ዜጎቻችንን ለማዳን በትብብር እየሰራ ነው። የ380 ዜጎች ስም ዝርዝር እና ፓስፖርት ኮፒ ቶኪዮ ለሚገኘው የማይናማር ኤምባሲ እንዲደርስ ተደርጓል።

የማይናማር መንግሥት ታጋቾችን ለመልቀቅ ጠረት በማድረግ ላይ ሲሆን ከአጋቾች አምልጠው ለመንግሥት እጅ የሚሰጡ ዜጎች ምህረት በማድረግ በነጻ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ትብብር በማድረግ ላይ ይገኛል።

ፈታኝ የሆነው ዋናው ጉዳይ የታገቱት ዜጎች የሚገኙት በማይናማር እና ታይላንድ መካከል በሚገኙ ከማይናማር መንግሥት ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ስፍራዎች መሆኑ ነው። ይህ ስራውን አክብዶታል።

ሌላው ፤ በዚህ ኢሰብዓዊ ወንጀል ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ሀገራት ሰው አዘዋዋሪዎች ተቀራርበው እየሰሩ መሆኑ ነው።

እስካሁን መንግሥት ከዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች ጋር ጭምር ባደረገው ጥረት በ6 ወር ውስጥ 34 ዜጎች ከአጋቾች ነጻ ወጥተው ወደ ታይላንድ እና ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ተደርጓል።

ከአጋቾች አምልጠው ህጋዊ ሰነድ ስለሌላቸው በእስር ቤቶች ታስረው የነበሩ 7 ዜጎቻችንም በምህረት እንዲለቀቁ ማድረግ ተችሏል።

ዜጎችን የመታደጉ ስራ ብዙ ጥረትን የሚጠይቅ በመሆኑ ቶኪዮ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ሚስዮን በተጨማሪ በኒዉዴልሂ የሚገኘው ኤምባሲም ተልዕኮ ተሰጥቶት መንቀሳቀስ ጀምሯል " ብለዋል።

NB. አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ወጣቶች ደህንነቱ ወዳልተጠበቀ ስፍራ እየሄዱ ያሉት ከስራ ቅጥር ጋር ተያያዥ በሆኑ የማተለያ ስልቶች በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል። የችግሩን ምንነት እና አስከፊነት ህብረተሰቡ እንዲያውቅ የማድረጉን ስራ ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/93783

View MORE
Open in Telegram


TIKVAH ETHIOPIA Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

For some time, Mr. Durov and a few dozen staffers had no fixed headquarters, but rather traveled the world, setting up shop in one city after another, he told the Journal in 2016. The company now has its operational base in Dubai, though it says it doesn’t keep servers there.Mr. Durov maintains a yearslong friendship from his VK days with actor and tech investor Jared Leto, with whom he shares an ascetic lifestyle that eschews meat and alcohol.

TIKVAH ETHIOPIA from cn


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM USA