Telegram Group & Telegram Channel
እንደምን አላችሁ?
የነቢያት ጾም ሰንበታት የራሳቸው ስያሜዎች እንደ ዐቢይ ጾም ያላቸው ሲሆን የነገው ሰንበት ከጌታችን ፱ቱ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው ስያሜውም ስብከት ይባላል! 

ለነገው ቅዳሴ እንዲያግዝ የዕለቱ ግጻዌ ከነ ዝማሬው ከelam የቴሌግራም ገጽ  በክቡር አባታችን አባ ኃይለ ሚካኤል የተዘጋጀ  እናጋራችኋለን፤

መልካም በዓል


መዝሙር ዘስብከት ከታኅሣሥ ፯ - ፲፫

(በ፪/ዩ) ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኮሳት ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ወልዶ መድኅነ ንሰብክ
ትርጕም፦
ቅድመ ዓለም የነበረ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን፤ የሰማዕታት አክሊል፣ ካህናትን የሚሾም፣ የመነኮሳት ተስፋ የሆነ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን።

የዕለቱ ምንባባት፦

ዕብ ፩፥፩ - ፍ፤
፪ጴጥ ፫፥፩ - ፲፤
ግብ ፫፥፲፯ - ፍ፤
የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ ፩፥፵፬ - ፍ፤
ቅዳሴ፦ ዘእግዚእነ

የዕለቱ ምስባክ፦
ፈኑ እዴከ እምአርያም፤
አድኅነኒ ወባልሐኒ እማይ ብዙኅ፤
ወእምእዴሆሙ ለደቂቀ ነኪር። መዝ ፻፵፫፥፯፤

ትርጉም፦

እጅህን ከአርያም ላክ፤
ከብዙ ውኃም አድነኝ፤
ከባዕድ ልጆችም አድነኝ።

ምሥጢር፦
ረድኤትህን ከአርያም ላክ አንድም ልጅህን በሥጋ ላክ፤
ከብዙ ጦር/ሠራዊት አድነኝ አንድም ከፍትወታት እኩያት ከኃጣውእ ርኩሳት ከፍዳ ከመከራ ነፍስ ፈጽመህ አድነኝ።
ከነናምሩድ ከነሳኦል ልጆች እጅ አድነኝ አንድም ከዲያብሎስ ወገኖች ሥልጣን አድነኝ።
ክንድ ከአካል ተገኝቶ ከአካል ሳይለይ ይኖራል፤ እሱም ከአብ ተገኝቶ ከአብ ሳይለይ ይኖራልና። ቦ የሰው ኃይሉ በክንዱ እንዲታወቅ የአብም ኃይሉ በወልድ ታውቋልና። ቦ ክንድ ከአካል ሳይለይ የወደቀ አንሥቶ ይመለሳል፤ እሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አንድነት ሳይለይ የወደቀ አዳምን አንሥቶ ተመልሷልና። ቦ በክንድ የራቀ ያቀርቡበታል የቀረበ ያርቁበታል፤ የራቀ አዳምን አቅርቦበታል የቀረበ ዲያብሎስን አርቆበታልና። ቦ በክንድ አሥረው ያጠብቁበታል ወርውረው ያርቁበታል፤ ዲያብሎስን በእሳት ዛንጅር ይዞ በነፋስ አውታር አሥሮ ከሰው ሕይወት አርቆበታልና። ቦ በክንድ የታሠረ ይፈቱበታል የተፈታ ያሥሩበታል፤ የታሠረ አዳምን ፈትቶበታል የተፈታ ዲያብሎስን አሥሮበታልና። ኋላም ሑሩ እምኔየ ብሎ ያርቅበታል ንዑ ኀቤየ ብሎ ያቀርብበታልና እጅህን ላክ አለ።
መልእክት፦
ዛፍ ከሥሩ ሳይነቀል ጫፉ መሬት ነክቶ ይመለሳል የአምላክ ሰው የመሆን ምሥጢርም እንዲሁ ነው። ምሥጢሩ የዚህን ያህል ጥልቅና ረቂቅ ከሆነ በምሥጢረ ሥጋዌ ዙሪያ አምላክ እንዴት ሰው እንደሆነ ሰውም እንዴት አምላክ እንደሆነ ተመራምሬ እደርሳለሁ ማለት የውቅያኖስን ውኃ በእንቁላል ቅርፊት ቀድቶ ለመጨረስ እንደመሞከር ነው።

©



tg-me.com/orthodox1/12830
Create:
Last Update:

እንደምን አላችሁ?
የነቢያት ጾም ሰንበታት የራሳቸው ስያሜዎች እንደ ዐቢይ ጾም ያላቸው ሲሆን የነገው ሰንበት ከጌታችን ፱ቱ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው ስያሜውም ስብከት ይባላል! 

ለነገው ቅዳሴ እንዲያግዝ የዕለቱ ግጻዌ ከነ ዝማሬው ከelam የቴሌግራም ገጽ  በክቡር አባታችን አባ ኃይለ ሚካኤል የተዘጋጀ  እናጋራችኋለን፤

መልካም በዓል


መዝሙር ዘስብከት ከታኅሣሥ ፯ - ፲፫

(በ፪/ዩ) ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኮሳት ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ወልዶ መድኅነ ንሰብክ
ትርጕም፦
ቅድመ ዓለም የነበረ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን፤ የሰማዕታት አክሊል፣ ካህናትን የሚሾም፣ የመነኮሳት ተስፋ የሆነ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን።

የዕለቱ ምንባባት፦

ዕብ ፩፥፩ - ፍ፤
፪ጴጥ ፫፥፩ - ፲፤
ግብ ፫፥፲፯ - ፍ፤
የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ ፩፥፵፬ - ፍ፤
ቅዳሴ፦ ዘእግዚእነ

የዕለቱ ምስባክ፦
ፈኑ እዴከ እምአርያም፤
አድኅነኒ ወባልሐኒ እማይ ብዙኅ፤
ወእምእዴሆሙ ለደቂቀ ነኪር። መዝ ፻፵፫፥፯፤

ትርጉም፦

እጅህን ከአርያም ላክ፤
ከብዙ ውኃም አድነኝ፤
ከባዕድ ልጆችም አድነኝ።

ምሥጢር፦
ረድኤትህን ከአርያም ላክ አንድም ልጅህን በሥጋ ላክ፤
ከብዙ ጦር/ሠራዊት አድነኝ አንድም ከፍትወታት እኩያት ከኃጣውእ ርኩሳት ከፍዳ ከመከራ ነፍስ ፈጽመህ አድነኝ።
ከነናምሩድ ከነሳኦል ልጆች እጅ አድነኝ አንድም ከዲያብሎስ ወገኖች ሥልጣን አድነኝ።
ክንድ ከአካል ተገኝቶ ከአካል ሳይለይ ይኖራል፤ እሱም ከአብ ተገኝቶ ከአብ ሳይለይ ይኖራልና። ቦ የሰው ኃይሉ በክንዱ እንዲታወቅ የአብም ኃይሉ በወልድ ታውቋልና። ቦ ክንድ ከአካል ሳይለይ የወደቀ አንሥቶ ይመለሳል፤ እሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አንድነት ሳይለይ የወደቀ አዳምን አንሥቶ ተመልሷልና። ቦ በክንድ የራቀ ያቀርቡበታል የቀረበ ያርቁበታል፤ የራቀ አዳምን አቅርቦበታል የቀረበ ዲያብሎስን አርቆበታልና። ቦ በክንድ አሥረው ያጠብቁበታል ወርውረው ያርቁበታል፤ ዲያብሎስን በእሳት ዛንጅር ይዞ በነፋስ አውታር አሥሮ ከሰው ሕይወት አርቆበታልና። ቦ በክንድ የታሠረ ይፈቱበታል የተፈታ ያሥሩበታል፤ የታሠረ አዳምን ፈትቶበታል የተፈታ ዲያብሎስን አሥሮበታልና። ኋላም ሑሩ እምኔየ ብሎ ያርቅበታል ንዑ ኀቤየ ብሎ ያቀርብበታልና እጅህን ላክ አለ።
መልእክት፦
ዛፍ ከሥሩ ሳይነቀል ጫፉ መሬት ነክቶ ይመለሳል የአምላክ ሰው የመሆን ምሥጢርም እንዲሁ ነው። ምሥጢሩ የዚህን ያህል ጥልቅና ረቂቅ ከሆነ በምሥጢረ ሥጋዌ ዙሪያ አምላክ እንዴት ሰው እንደሆነ ሰውም እንዴት አምላክ እንደሆነ ተመራምሬ እደርሳለሁ ማለት የውቅያኖስን ውኃ በእንቁላል ቅርፊት ቀድቶ ለመጨረስ እንደመሞከር ነው።

©

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/12830

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The Singapore stock market has alternated between positive and negative finishes through the last five trading days since the end of the two-day winning streak in which it had added more than a dozen points or 0.4 percent. The Straits Times Index now sits just above the 3,060-point plateau and it's likely to see a narrow trading range on Monday.

Traders also expressed uncertainty about the situation with China Evergrande, as the indebted property company has not provided clarification about a key interest payment.In economic news, the Commerce Department reported an unexpected increase in U.S. new home sales in August.Crude oil prices climbed Friday and front-month WTI oil futures contracts saw gains for a fifth straight week amid tighter supplies. West Texas Intermediate Crude oil futures for November rose $0.68 or 0.9 percent at 73.98 a barrel. WTI Crude futures gained 2.8 percent for the week.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from de


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA