Telegram Group & Telegram Channel
#ሐያቱ_ሷሐባ #አቡ_ዑበይዳህ__ኢብኑ #አል_ጀራሕ (ረ.ዐ) #ክፍል_1

“ማንኛውም ኡምማ (ሕዝብ) የራሱ አሚን (ታማኝ) አለው። የዚህ ኡምማ አሚን አቡ ዑበይዳህ ነው።” (ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ))

ግርማ ሞገስ ያለው፣ ረጂም እና በመጠኑ ሰውነቱ ሞላ ያለ ሰው ነበር። ብሩህ የሆነ ገጽታን የተላበሰ ሲሆን እሱን መመልከት የሚያስደስትና ከእሱ መዋልም መንፈስን የሚያድስ እንደነበር ተነግሮለታል። ጠባየ ሸጋ፣ አንደበተ ርቱዕ፣ ትዕግስተኛና ፍፁም ዓይን አፋርም ነበር። የነቢዩ (ﷺ) ኮምዩኒቲ (ማኅበረሰብ) ታማኝ ወይም “አሚን” በመባል ይታወቃል። ሙሉ ስሙ ዓሚር ኢብኑ ዐብደላህ አል ጀራሕ ነው። አቡ ዑበይዳህ በመባል ነው ይበልጥ የሚታወቀው። የነቢዩ (ﷺ) ባልደረባ (ሶሐባ) የነበሩ ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) በአንድ ወቅት ስለ አቡ ዑበይዳህ ሲናገሩ እንዲህ ብለው ነበር፦

“በቁረይሽ ጎሣ ውስጥ ሦስት ሰዎች አሉ፤ እነዚህ በግልጽነታቸውና በመልካም ጠባያቸው ከሌላው ሰው የተለየ የሚያደርጋቸው አያሌ ምግባር ነበራቸው። እውነትን እንጂ የማይናገሩ፣ በሚያዋሯቸውም ጊዜ ለነቀፌታና ለትችት የማይቸኩሉ ሰዎች ነበሩ። እነርሱም፦ “አቡበክር አስ ሲዲቅ፣ ዑሥማን ኢብኑ ዐፍፋን እና አቡ ዑበይዳህ ኢብኑ አል ጀራሕ (ረ.ዐ) ናቸው።”

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) ኢስላምን በቅድሚያ ከተበቀበሉት ሙስሊሞች መካከል አንዱ ነበር። ኢስላምን የተቀበለው አቡበክር (ረ.ዐ) ከተቀበሉ ከአንድ ቀን በኋላ ነበር። ለመስለሙ ምክንያት የሆኑትም አቡበክር (ረ.ዐ) ናቸው። አቡበክር (ረ.ዐ) አቡ ዑበይዳን፣ ዐብዱረሕማን ኢብኑ አውፍን፣ ዑሥማን ኢብኑ መዕዙንን እና አርቀም ኢብኑ አቡ አርቀምን ወደ ነቢዩ (ﷺ) በመውሰድ “ሸሃዳ” እንዲይዙ አደረጉ። እንግዲህ እነዚህ ሰዎች የኢስላም የመጀመሪያ ልጆች ናቸው።

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) በእነዚህ አስከፊ ወቅቶች ማለትም ሙስሊሞች በመካ ውስጥ ባሳለፉት የመከራና የሥቃይ ጊዜያት የነበረና ኢስላም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ የገጠመውን ዕድል የተጋፈጠ ነው። ከቀደምት ሙስሊሞች ጋር አብሮ ተሰዷል ነገር ግን በገጠሟቸው ፈተናዎችና መከራዎች ሁሉ በአላህ እና በመልዕክተኛው ያለው እምነት የማያወላውልና የማይበገር መሆኑን አስመስክሯል። በተለይም በበድር ዘመቻ ላይ ያሳየው ተጋድሎ ታላቁን ሥፍራ ይይዛል።

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) ለሙስሊሙ ጦር ግንባር ቀደም ተዋጊ በመሆኑ በጠላት ላይ የሚያደርሰው ጥቃት ከፍተኛ ነበር። የቁረይሽ ፈረሰኞችም አቡ ዑበይዳህን በጣም ይጠነቀቁት፣ ይሸሹት፣ እና ፊት ለፊትም መጋፈጥን ይፈሩ ነበር። ነገር ግን አንድ አቡ ዑበይዳህን በሚሄድበት ቦታ ሁሉ የሚከታተለውና አደጋ ሊያደርስበት የሚሞክር ሰው ነበር። አቡ ዑበይዳህ ግን ሰውየው ጋር ላለመግጠም ጥረት ያደርጋል።

ሰውየውም ቅኝቱን ቀጠለ። አቡ ዑበይዳህም ይህን ሰው ላለመገናኘት ሞከረ። ነገር ግን ይኸው ባላንጣ መንገዱን ዘጋበት፡፡ ፊት ለፊት ተፋጠጡ። አሁን አቡ ዑበይዳህ ራሱን ሊገታና ጊዜም ሊወስድ አልፈለገም። በሰውየው ጭንቅላት ላይ ከባድ በትር አሳረፈበት። ሰውየውም መሬት ላይ ተዘረረ ፤ በቅጽበት ሕይወቱ አለፈች፡፡

ሟቹ ማን ይሆን? አዎ የአቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) አባት ነበር። የአንድ ፈጣሪ ሥርዓተ አምልኮን ለማንገሥና በብዙ አማክልት ማመንን ለማጥፋት በተደረገ ዘመቻ አባቱን በመግደሉ አይቆጭም። በዚሁ አጋጣሚ አቡ ዑበይዳህ የገደለው አባቱን ሳይሆን በአባቱ ውስጥ ያለውን የብዙ አማልክት እምነትና ሃይማኖት ነው።

ይህን ክስተት በሚመለከት ነበር አላህ የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ ያወረደው፦

لَّا تَجِدُ قَوْمًۭا يُؤْمِنُونَ بِٱللَّهِ وَٱلْيَوْمِ ٱلْءَاخِرِ يُوَآدُّونَ مَنْ حَآدَّ ٱللَّهَ وَرَسُولَهُۥ وَلَوْ كَانُوٓا۟ ءَابَآءَهُمْ أَوْ أَبْنَآءَهُمْ أَوْ إِخْوَ ٰنَهُمْ أَوْ عَشِيرَتَهُمْ ۚ أُو۟لَـٰٓئِكَ كَتَبَ فِى قُلُوبِهِمُ ٱلْإِيمَـٰنَ وَأَيَّدَهُم بِرُوحٍۢ مِّنْهُ ۖ وَيُدْخِلُهُمْ جَنَّـٰتٍۢ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَـٰرُ خَـٰلِدِينَ فِيهَا ۚ رَضِىَ ٱللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا۟ عَنْهُ ۚ أُو۟لَـٰٓئِكَ حِزْبُ ٱللَّهِ ۚ أَلَآ إِنَّ حِزْبَ ٱللَّهِ هُمُ ٱلْمُفْلِحُونَ ﴿٢٢﴾

“በአላህና በመጨረሻው ቀን የሚያምኑትን ሕዝቦች አላህንና መልክተኛውን የሚከራከሩትን ሰዎች፤ አባቶቻቸው፣ ወይም ልጆቻቸው፣ ወይም ወንድሞቻቸው፣ ወይም ዘመዶቻቸው ቢኾኑም እንኳ የሚወዳጁ ኾነው አታገኛቸውም፡፡ እነዚያ በልቦቻቸው ውስጥ እምነትን ጽፏል፡፡ ከእርሱም በኾነ መንፈስ ደግፏቸዋል፡፡ ከሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ ያገባቸዋል፡፡ አላህ ከእነርሱ ወዷል፡፡ ከእርሱም ወደዋል፡፡ እነዚያ የአላህ ሕዝቦች ናቸው፡፡ ንቁ! የአላህ ሕዝቦቸ እነርሱ ምኞታቸውን የሚያገኙ ናቸው፡፡“
(አል ሙጃደላህ፡ 22)

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) በአባቱ ላይ የወሰደው እርምጃ ያልታሰበና ያልተጠበቀም አልነበረም። በአላህ ከፍተኛ እምነት ያለው፣ ለኢስላም ቀናኢ የሆነ እንዲሁም ለነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ኡምማህ (ሕዝብ) የነበረው ትኩረት ከፍተኛ ሶሐባ በመሆኑ ነው።

ሙሐመድ ኢብኑ ጀዕፈር (ረ.ዐ) እንዳወሩት ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦

በአንድ ወቅት አንድ የክርስቲያን ልዑካን ቡድን ወደ ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይመጣል “አቡልቃሲም ሆይ! (ነቢዩን ማለታቸው ነው) በመካከላችን በሀብትና በንብረት ክፍፍል ምክንያት ስምምነት ላይ ልንደርስ አልቻልንምና እርስዎ የሚያምኑበትን ሰው በመሃከላችን እንዲፈርድ ቢልኩልን ፤ እኛ በእናንተ ሙስሊም ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ ክብርና እምነት አለንና መፍትሔውን ከእርሶ እንጠብቃለን” አሏቸው።

ነቢዩም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) “ወደ ማታ ላይ ተመልሳችሁ እንድትመጡ ጠንካራና ታማኝ የሆነን ሰው እሰጣችሁና ይዛችሁ ትሄዳላችሁ።” አሏቸው።

ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) የነቢዩን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) መልስ ከሰሙ በኋላ የተከሰተውን ሁኔታ ራሳቸው ይተርኩልናል፦ “ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የሚፈልጉትን ሰው መስፈርቱን አሟላለሁ በሚል ዝሁር ወቅት ላይ ቀደም ብዬ በመግባት ከነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አጠገብ ተቀመጥኩ። ነቢዩም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ስግደታቸውን እንደ ጨረሱ ወደቀኝና ግራ በመዞር ተመለከቱ፤ እኔም እንዲመለከቱኝ ከፍ ከፍ ማለት ጀመርኩ። ነገር ግን አሁንም መመልከታቸውን ቀጠሉ። ትኩረታቸውን ወደ አቡ ዑበይዳህ ኢብኑ አል ጀራሕ አደረጉ። ጠሩትና ‘ከእነዚህ ሰዎች ጋር ሂድ፤ ያልተስማሙበትም ጉዳይ አለና በትክክልና በእውነት ዳኛቸው።” አሉት፡፡ አቡ ዑበይዳህም ከሰዎቹ ጋር ቀጠሮ ያዘ።”

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) ታማኝ ብቻም አልነበሩም። በተሰጣቸው ማንኛውም የኃላፊነት ሥራ ሁሉ ጠንካራ እና አይበገሬ መሆናቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች አስመስክሯል።

ኢንሻአላህ ክፍል 2 ይቀጥላል

telegram/
https://www.tg-me.com/us/ISLAMIC CENTER/com.eslamic_center



tg-me.com/eslamic_center/542
Create:
Last Update:

#ሐያቱ_ሷሐባ #አቡ_ዑበይዳህ__ኢብኑ #አል_ጀራሕ (ረ.ዐ) #ክፍል_1

“ማንኛውም ኡምማ (ሕዝብ) የራሱ አሚን (ታማኝ) አለው። የዚህ ኡምማ አሚን አቡ ዑበይዳህ ነው።” (ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ))

ግርማ ሞገስ ያለው፣ ረጂም እና በመጠኑ ሰውነቱ ሞላ ያለ ሰው ነበር። ብሩህ የሆነ ገጽታን የተላበሰ ሲሆን እሱን መመልከት የሚያስደስትና ከእሱ መዋልም መንፈስን የሚያድስ እንደነበር ተነግሮለታል። ጠባየ ሸጋ፣ አንደበተ ርቱዕ፣ ትዕግስተኛና ፍፁም ዓይን አፋርም ነበር። የነቢዩ (ﷺ) ኮምዩኒቲ (ማኅበረሰብ) ታማኝ ወይም “አሚን” በመባል ይታወቃል። ሙሉ ስሙ ዓሚር ኢብኑ ዐብደላህ አል ጀራሕ ነው። አቡ ዑበይዳህ በመባል ነው ይበልጥ የሚታወቀው። የነቢዩ (ﷺ) ባልደረባ (ሶሐባ) የነበሩ ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) በአንድ ወቅት ስለ አቡ ዑበይዳህ ሲናገሩ እንዲህ ብለው ነበር፦

“በቁረይሽ ጎሣ ውስጥ ሦስት ሰዎች አሉ፤ እነዚህ በግልጽነታቸውና በመልካም ጠባያቸው ከሌላው ሰው የተለየ የሚያደርጋቸው አያሌ ምግባር ነበራቸው። እውነትን እንጂ የማይናገሩ፣ በሚያዋሯቸውም ጊዜ ለነቀፌታና ለትችት የማይቸኩሉ ሰዎች ነበሩ። እነርሱም፦ “አቡበክር አስ ሲዲቅ፣ ዑሥማን ኢብኑ ዐፍፋን እና አቡ ዑበይዳህ ኢብኑ አል ጀራሕ (ረ.ዐ) ናቸው።”

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) ኢስላምን በቅድሚያ ከተበቀበሉት ሙስሊሞች መካከል አንዱ ነበር። ኢስላምን የተቀበለው አቡበክር (ረ.ዐ) ከተቀበሉ ከአንድ ቀን በኋላ ነበር። ለመስለሙ ምክንያት የሆኑትም አቡበክር (ረ.ዐ) ናቸው። አቡበክር (ረ.ዐ) አቡ ዑበይዳን፣ ዐብዱረሕማን ኢብኑ አውፍን፣ ዑሥማን ኢብኑ መዕዙንን እና አርቀም ኢብኑ አቡ አርቀምን ወደ ነቢዩ (ﷺ) በመውሰድ “ሸሃዳ” እንዲይዙ አደረጉ። እንግዲህ እነዚህ ሰዎች የኢስላም የመጀመሪያ ልጆች ናቸው።

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) በእነዚህ አስከፊ ወቅቶች ማለትም ሙስሊሞች በመካ ውስጥ ባሳለፉት የመከራና የሥቃይ ጊዜያት የነበረና ኢስላም ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ የገጠመውን ዕድል የተጋፈጠ ነው። ከቀደምት ሙስሊሞች ጋር አብሮ ተሰዷል ነገር ግን በገጠሟቸው ፈተናዎችና መከራዎች ሁሉ በአላህ እና በመልዕክተኛው ያለው እምነት የማያወላውልና የማይበገር መሆኑን አስመስክሯል። በተለይም በበድር ዘመቻ ላይ ያሳየው ተጋድሎ ታላቁን ሥፍራ ይይዛል።

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) ለሙስሊሙ ጦር ግንባር ቀደም ተዋጊ በመሆኑ በጠላት ላይ የሚያደርሰው ጥቃት ከፍተኛ ነበር። የቁረይሽ ፈረሰኞችም አቡ ዑበይዳህን በጣም ይጠነቀቁት፣ ይሸሹት፣ እና ፊት ለፊትም መጋፈጥን ይፈሩ ነበር። ነገር ግን አንድ አቡ ዑበይዳህን በሚሄድበት ቦታ ሁሉ የሚከታተለውና አደጋ ሊያደርስበት የሚሞክር ሰው ነበር። አቡ ዑበይዳህ ግን ሰውየው ጋር ላለመግጠም ጥረት ያደርጋል።

ሰውየውም ቅኝቱን ቀጠለ። አቡ ዑበይዳህም ይህን ሰው ላለመገናኘት ሞከረ። ነገር ግን ይኸው ባላንጣ መንገዱን ዘጋበት፡፡ ፊት ለፊት ተፋጠጡ። አሁን አቡ ዑበይዳህ ራሱን ሊገታና ጊዜም ሊወስድ አልፈለገም። በሰውየው ጭንቅላት ላይ ከባድ በትር አሳረፈበት። ሰውየውም መሬት ላይ ተዘረረ ፤ በቅጽበት ሕይወቱ አለፈች፡፡

ሟቹ ማን ይሆን? አዎ የአቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) አባት ነበር። የአንድ ፈጣሪ ሥርዓተ አምልኮን ለማንገሥና በብዙ አማክልት ማመንን ለማጥፋት በተደረገ ዘመቻ አባቱን በመግደሉ አይቆጭም። በዚሁ አጋጣሚ አቡ ዑበይዳህ የገደለው አባቱን ሳይሆን በአባቱ ውስጥ ያለውን የብዙ አማልክት እምነትና ሃይማኖት ነው።

ይህን ክስተት በሚመለከት ነበር አላህ የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ ያወረደው፦

لَّا تَجِدُ قَوْمًۭا يُؤْمِنُونَ بِٱللَّهِ وَٱلْيَوْمِ ٱلْءَاخِرِ يُوَآدُّونَ مَنْ حَآدَّ ٱللَّهَ وَرَسُولَهُۥ وَلَوْ كَانُوٓا۟ ءَابَآءَهُمْ أَوْ أَبْنَآءَهُمْ أَوْ إِخْوَ ٰنَهُمْ أَوْ عَشِيرَتَهُمْ ۚ أُو۟لَـٰٓئِكَ كَتَبَ فِى قُلُوبِهِمُ ٱلْإِيمَـٰنَ وَأَيَّدَهُم بِرُوحٍۢ مِّنْهُ ۖ وَيُدْخِلُهُمْ جَنَّـٰتٍۢ تَجْرِى مِن تَحْتِهَا ٱلْأَنْهَـٰرُ خَـٰلِدِينَ فِيهَا ۚ رَضِىَ ٱللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا۟ عَنْهُ ۚ أُو۟لَـٰٓئِكَ حِزْبُ ٱللَّهِ ۚ أَلَآ إِنَّ حِزْبَ ٱللَّهِ هُمُ ٱلْمُفْلِحُونَ ﴿٢٢﴾

“በአላህና በመጨረሻው ቀን የሚያምኑትን ሕዝቦች አላህንና መልክተኛውን የሚከራከሩትን ሰዎች፤ አባቶቻቸው፣ ወይም ልጆቻቸው፣ ወይም ወንድሞቻቸው፣ ወይም ዘመዶቻቸው ቢኾኑም እንኳ የሚወዳጁ ኾነው አታገኛቸውም፡፡ እነዚያ በልቦቻቸው ውስጥ እምነትን ጽፏል፡፡ ከእርሱም በኾነ መንፈስ ደግፏቸዋል፡፡ ከሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲኾኑ ያገባቸዋል፡፡ አላህ ከእነርሱ ወዷል፡፡ ከእርሱም ወደዋል፡፡ እነዚያ የአላህ ሕዝቦች ናቸው፡፡ ንቁ! የአላህ ሕዝቦቸ እነርሱ ምኞታቸውን የሚያገኙ ናቸው፡፡“
(አል ሙጃደላህ፡ 22)

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) በአባቱ ላይ የወሰደው እርምጃ ያልታሰበና ያልተጠበቀም አልነበረም። በአላህ ከፍተኛ እምነት ያለው፣ ለኢስላም ቀናኢ የሆነ እንዲሁም ለነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ኡምማህ (ሕዝብ) የነበረው ትኩረት ከፍተኛ ሶሐባ በመሆኑ ነው።

ሙሐመድ ኢብኑ ጀዕፈር (ረ.ዐ) እንዳወሩት ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦

በአንድ ወቅት አንድ የክርስቲያን ልዑካን ቡድን ወደ ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይመጣል “አቡልቃሲም ሆይ! (ነቢዩን ማለታቸው ነው) በመካከላችን በሀብትና በንብረት ክፍፍል ምክንያት ስምምነት ላይ ልንደርስ አልቻልንምና እርስዎ የሚያምኑበትን ሰው በመሃከላችን እንዲፈርድ ቢልኩልን ፤ እኛ በእናንተ ሙስሊም ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ ክብርና እምነት አለንና መፍትሔውን ከእርሶ እንጠብቃለን” አሏቸው።

ነቢዩም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) “ወደ ማታ ላይ ተመልሳችሁ እንድትመጡ ጠንካራና ታማኝ የሆነን ሰው እሰጣችሁና ይዛችሁ ትሄዳላችሁ።” አሏቸው።

ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) የነቢዩን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) መልስ ከሰሙ በኋላ የተከሰተውን ሁኔታ ራሳቸው ይተርኩልናል፦ “ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የሚፈልጉትን ሰው መስፈርቱን አሟላለሁ በሚል ዝሁር ወቅት ላይ ቀደም ብዬ በመግባት ከነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አጠገብ ተቀመጥኩ። ነቢዩም (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ስግደታቸውን እንደ ጨረሱ ወደቀኝና ግራ በመዞር ተመለከቱ፤ እኔም እንዲመለከቱኝ ከፍ ከፍ ማለት ጀመርኩ። ነገር ግን አሁንም መመልከታቸውን ቀጠሉ። ትኩረታቸውን ወደ አቡ ዑበይዳህ ኢብኑ አል ጀራሕ አደረጉ። ጠሩትና ‘ከእነዚህ ሰዎች ጋር ሂድ፤ ያልተስማሙበትም ጉዳይ አለና በትክክልና በእውነት ዳኛቸው።” አሉት፡፡ አቡ ዑበይዳህም ከሰዎቹ ጋር ቀጠሮ ያዘ።”

አቡ ዑበይዳህ (ረ.ዐ) ታማኝ ብቻም አልነበሩም። በተሰጣቸው ማንኛውም የኃላፊነት ሥራ ሁሉ ጠንካራ እና አይበገሬ መሆናቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች አስመስክሯል።

ኢንሻአላህ ክፍል 2 ይቀጥላል

telegram/
https://www.tg-me.com/us/ISLAMIC CENTER/com.eslamic_center

BY ISLAMIC-CENTER




Share with your friend now:
tg-me.com/eslamic_center/542

View MORE
Open in Telegram


ISLAMIC CENTER Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Tata Power whose core business is to generate, transmit and distribute electricity has made no money to investors in the last one decade. That is a big blunder considering it is one of the largest power generation companies in the country. One of the reasons is the company's huge debt levels which stood at ₹43,559 crore at the end of March 2021 compared to the company’s market capitalisation of ₹44,447 crore.

How Does Bitcoin Work?

Bitcoin is built on a distributed digital record called a blockchain. As the name implies, blockchain is a linked body of data, made up of units called blocks that contain information about each and every transaction, including date and time, total value, buyer and seller, and a unique identifying code for each exchange. Entries are strung together in chronological order, creating a digital chain of blocks. “Once a block is added to the blockchain, it becomes accessible to anyone who wishes to view it, acting as a public ledger of cryptocurrency transactions,” says Stacey Harris, consultant for Pelicoin, a network of cryptocurrency ATMs. Blockchain is decentralized, which means it’s not controlled by any one organization. “It’s like a Google Doc that anyone can work on,” says Buchi Okoro, CEO and co-founder of African cryptocurrency exchange Quidax. “Nobody owns it, but anyone who has a link can contribute to it. And as different people update it, your copy also gets updated.”

ISLAMIC CENTER from us


Telegram ISLAMIC-CENTER
FROM USA