tg-me.com/ewnet_lehulum/2907
Last Update:
ራሱን አቃጠለ!
ስለ ጭቁኑ የፍልስጤም ሙስሊም ስለደረበትና ስለሚደርስበት መከራ ለመግለፅ ቃላቶች ራሱ አቅማቸው አይፈቅድላቸውም። የሕፃናት ጭፍጨፋ ከደቂቅ እስከ ትልቅ ያውም በአሰቃቂ ሁኔታ… ነገር ግን አይን ገላጭ ክስተት ሆኖ አለምን አንቅቷል። ኢማን በደም ስራቸው የሞላባቸውን ሙስሊሞች እስከ ጥግ አሳይተውን እኛም በእነርሱ ኮርተን ምንም አካላዊ ተሳትፎ ባለማድረጋችን በራሳችን አፍረናል። ያለን ብቸኛው ኃይል ዱዓችን ብቻ ሲቀር… ፍትህ ከአላህ ነው ከሠውም አይደለምና የአለም ኃያላን ሀገራቶች ሳይቀር ተሰባስበው ፍልስጤም ላይ አደሙባቸው። እስራኤልም በጦርና ወታደራዊ ኃይል በምዕራባውያንና አውሮፓውያን ስትረዳ ብትቆይም መቋቋም አቅቷት መሸሽን መረጠች። ከሕፃናት፣ ሴቶችና አዛውንቶች በቀር የመግደል ሕሊናም ሆነ አቅም በቀር ሌላ ምንም አልነበራትም። ከአለም ጫፍ እስከ ጫፍ ከደቡብ እስከ ሠሜን ከምዕራብ እስከ ምስራቅ ሙሉ በሙሉ ላስተዋሉ ሠዎች የፍሊስጤም ወኔና አልሸነፍ ባይነት ለሐቅ መጋደል የሕይወታቸውን ትልቁን ትምህርት ሠጣቸው። "የፍልስጤም ሙስሊሞች እንዲ በደስታ የሚሞቱለት እምነታቸውና ጥንካሬያቸው ምን ይሆን? በማለት በግርምት ተዋጡ።" ብርሐን ወደ ሆነውም ኢስላም አያሌዎች ቁርዓንን በማንበብ ወደ ኢስላም ጎረፉ። የፍልስጤምን ጉዳይ ቃላቶች ስለማይገልፁት ይህ የአሜሪካ የአየር ኃይል ውስጥ አባል የሆነ ሠው የፍልስጤምን ከመጠን በላይ ጭቆና በተግባር ለማውገዝ የሄደበት እርቀት ክስተቱን ገላጭ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። እየተቃጠለ እንኳን "Free Palestine" ሲል ይደመጣል። ልቡ ምን ያህል እንደታመመና የፍትህን መጓደል የተረዳ ሠው እንደነበረ ጠቋሚም ነው። ልብን ሠባሪ ሞት ሞተ፤ ግን ትልቅ መስዋዕትነትን የከፈለ ታሪካዊ ጀግና ሠው ነው።
አላህ ፍልስጤምን እና ሙስሊሞችን ይጠብቅ!
BY እውነት ለሁሉ [truth for all]
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/ewnet_lehulum/2907