Telegram Group & Telegram Channel
(መሥዋዕት ለማቅረብ) ወደ ቤተ መቅደስ ሔዷል፡፡ ከዚህም እርሱ አምላክ ነኝ እና በተአምራቴ የማዳን ሥራዬን ልፈጽም ሳይል ከኀጢአትና ከፈቃደ ሥጋ በስተቀር በሰው ሥርዓት ማደጉን፤ እንደዚሁም የትሕትና ጌታ መኾኑን እንማራለን፡፡ ዛሬም ምእመናን ልጅ ሲወልዱ ወንዶችን በዐርባ፤ ሴቶች ደግሞ በሰማንያ ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን በመውሰድ ክርስትና የሚያስነሡት በዚህ ሥርዓት መሠረት ነው፡፡

ከነቢዩ ስምዖን ታሪክም በመጀመሪያ እግዚአብሔር አምላክ የማይፈጽመውን የማይናገር፤ የተናገረውንም የማያስቀር የእውነት ባለቤት እንደ ኾነ፤ እንደዚሁም እኛ አይደረግም ያልነው ከባድ የሚመስለን ምሥጢር ጊዜውን ጠብቆ መፈጸሙ እንደማይቀር፤ በተጨማሪም እግዚአብሔር በጥበብ የሚገሥፅ፣ የሚያስተምር የፍቅር አምላክ እንደ ኾነ እንገነዘባለን፡፡ ከዚሁ ዅሉ ጋርም በሥርዓተ ጋብቻ እስኪወሰኑ ድረስ ወንድሞችም እኅቶችም ክብረ ንፅሕናቸውን ጠብቀው መቆየት እንዳለባቸው፤ ከጋብቻ በኋላ ከሁለቱ ጥንዶች አንዱ በሞት ቢለይ ፈቃደ ሥጋቸውን መግታትና ሰውነታቸውን መቈጣጠር የሚቻላቸው ከኾነ እስከ ምድራዊ ሕይወታቸው ፍጻሜ ራሳቸውን ጠብቀው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ ቢኖሩ በጸጋ ላይ ጸጋን፤ በበረከት ላይ በረከትን እንደሚታደሉ ከነቢዪት ሐና ታሪክ የምናገኘው ትምህርት ነው፡፡

በእርግጥ በሞት ወይም በዝሙት ምክንያት ከትዳር አጋሮቻችን ጋር የተለያየን ምእመናን ፈቃደ ሥጋችንን መቋቋም የማይቻለን ከኾነ በሥርዓተ ቍርባን በድጋሜ ጋብቻ መመሥረት እንደምንችል በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ተደንግጓል፡፡ እናም በሞት ለተለያዩ ጥንዶች ሁለተኛ ጋብቻ ባይከለከልም ሳያገቡ እንደ ነቢዪት ሐና ራሳቸውን ጠብቀው መኖር ለሚፈልጉ ግን አለማግባት ይቻላል፡፡ ራስን ጠብቆ መኖር በእግዚአብሔር ለተመረጡ ሰዎች እንጂ ለዅላችን አይቻለንምና፡፡ ‹‹… እያንዳንዱ እግዚአብሔር እንደ አደለው ጸጋ ይኑር፤ ግብሩ እንዲህ የኾነ አለና፡፡ ገብሩ ሌላ የኾነም አለና፡፡ ነገር ግን ያላገቡትንና አግብተው የፈቱትን እንደ እኔ ኾነው ቢኖሩ ይሻላቸዋል እላቸዋለሁ፡፡ በፍትወት ከመቃጠል ማግባት ይሻላልና …፤›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ /፩ኛ ቀሮ.፯፥፯-፱/፡፡

ነቢዪት ሐና በድንግልና ከመኖሯ እና ሁለተኛ ባል ካለማግባቷ ባሻገር ዓለማዊ ተድላና ደስታን ንቃ፣ ሰውነቷን ጠብቃ፣ ከምኵራብ ሳትወጣ ሰማንያ ዓመት ሙሉ እግዚአብሔርን ስታገለግል መኖሯ ከእርሷ የምንማረው ሌላኛው ቁም ነገር ነው፡፡ እኛም እንደ ነቢዪቷ ሙሉ ጊዜአችንን ለቤተ ክርስቲያን መስጠት ባይቻለን እንኳን ከሥጋዊው ሥራችን ጎን ለጎን ወደ ቤተ ክርስቲያን እየሔድን ትምህርተ ወንጌል ብንሰማ፣ ብንጸልይ፣ ብንሰግድ፣ ከምሥጢራት ብንሳተፍ፤ እንደዚሁም ለአቅማችን በሚመጥን ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ተልእኮ ብናገለግል የእግዚአብሔር ጸጋ በእኛ ላይ ይበዛል፤ እጥፍ ድርብም ይኾናል፡፡ ከዅሉም በላይ በምድራዊው ሕይወታችን የክርስቶስ ቤተ መቅደስ የኾነውን ሰውነታችንን ከኀጢአት ለይተን፣ ራሳችንን ለጽድቅ ሥራ አስገዝተን፣ በመንፈሳዊ ምግባር ጸንተን፣ ስንበድል ተጸጽተን (ንስሐ ገብተን)፣ ቅዱስ ሥጋውን በልተን፣ ክቡር ደሙን ጠጥተን ብንኖር የማያልፈውን መንግሥቱን ለመውረስ እንበቃለን፡፡

የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የነቢዩ ስምዖን እና የነቢዪት ሐና፣ የሌሎችም ቅዱሳን በረከት ይደርብን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው ☞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም



tg-me.com/orthodox1/13285
Create:
Last Update:

(መሥዋዕት ለማቅረብ) ወደ ቤተ መቅደስ ሔዷል፡፡ ከዚህም እርሱ አምላክ ነኝ እና በተአምራቴ የማዳን ሥራዬን ልፈጽም ሳይል ከኀጢአትና ከፈቃደ ሥጋ በስተቀር በሰው ሥርዓት ማደጉን፤ እንደዚሁም የትሕትና ጌታ መኾኑን እንማራለን፡፡ ዛሬም ምእመናን ልጅ ሲወልዱ ወንዶችን በዐርባ፤ ሴቶች ደግሞ በሰማንያ ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን በመውሰድ ክርስትና የሚያስነሡት በዚህ ሥርዓት መሠረት ነው፡፡

ከነቢዩ ስምዖን ታሪክም በመጀመሪያ እግዚአብሔር አምላክ የማይፈጽመውን የማይናገር፤ የተናገረውንም የማያስቀር የእውነት ባለቤት እንደ ኾነ፤ እንደዚሁም እኛ አይደረግም ያልነው ከባድ የሚመስለን ምሥጢር ጊዜውን ጠብቆ መፈጸሙ እንደማይቀር፤ በተጨማሪም እግዚአብሔር በጥበብ የሚገሥፅ፣ የሚያስተምር የፍቅር አምላክ እንደ ኾነ እንገነዘባለን፡፡ ከዚሁ ዅሉ ጋርም በሥርዓተ ጋብቻ እስኪወሰኑ ድረስ ወንድሞችም እኅቶችም ክብረ ንፅሕናቸውን ጠብቀው መቆየት እንዳለባቸው፤ ከጋብቻ በኋላ ከሁለቱ ጥንዶች አንዱ በሞት ቢለይ ፈቃደ ሥጋቸውን መግታትና ሰውነታቸውን መቈጣጠር የሚቻላቸው ከኾነ እስከ ምድራዊ ሕይወታቸው ፍጻሜ ራሳቸውን ጠብቀው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ ቢኖሩ በጸጋ ላይ ጸጋን፤ በበረከት ላይ በረከትን እንደሚታደሉ ከነቢዪት ሐና ታሪክ የምናገኘው ትምህርት ነው፡፡

በእርግጥ በሞት ወይም በዝሙት ምክንያት ከትዳር አጋሮቻችን ጋር የተለያየን ምእመናን ፈቃደ ሥጋችንን መቋቋም የማይቻለን ከኾነ በሥርዓተ ቍርባን በድጋሜ ጋብቻ መመሥረት እንደምንችል በቀኖና ቤተ ክርስቲያን ተደንግጓል፡፡ እናም በሞት ለተለያዩ ጥንዶች ሁለተኛ ጋብቻ ባይከለከልም ሳያገቡ እንደ ነቢዪት ሐና ራሳቸውን ጠብቀው መኖር ለሚፈልጉ ግን አለማግባት ይቻላል፡፡ ራስን ጠብቆ መኖር በእግዚአብሔር ለተመረጡ ሰዎች እንጂ ለዅላችን አይቻለንምና፡፡ ‹‹… እያንዳንዱ እግዚአብሔር እንደ አደለው ጸጋ ይኑር፤ ግብሩ እንዲህ የኾነ አለና፡፡ ገብሩ ሌላ የኾነም አለና፡፡ ነገር ግን ያላገቡትንና አግብተው የፈቱትን እንደ እኔ ኾነው ቢኖሩ ይሻላቸዋል እላቸዋለሁ፡፡ በፍትወት ከመቃጠል ማግባት ይሻላልና …፤›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ /፩ኛ ቀሮ.፯፥፯-፱/፡፡

ነቢዪት ሐና በድንግልና ከመኖሯ እና ሁለተኛ ባል ካለማግባቷ ባሻገር ዓለማዊ ተድላና ደስታን ንቃ፣ ሰውነቷን ጠብቃ፣ ከምኵራብ ሳትወጣ ሰማንያ ዓመት ሙሉ እግዚአብሔርን ስታገለግል መኖሯ ከእርሷ የምንማረው ሌላኛው ቁም ነገር ነው፡፡ እኛም እንደ ነቢዪቷ ሙሉ ጊዜአችንን ለቤተ ክርስቲያን መስጠት ባይቻለን እንኳን ከሥጋዊው ሥራችን ጎን ለጎን ወደ ቤተ ክርስቲያን እየሔድን ትምህርተ ወንጌል ብንሰማ፣ ብንጸልይ፣ ብንሰግድ፣ ከምሥጢራት ብንሳተፍ፤ እንደዚሁም ለአቅማችን በሚመጥን ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ተልእኮ ብናገለግል የእግዚአብሔር ጸጋ በእኛ ላይ ይበዛል፤ እጥፍ ድርብም ይኾናል፡፡ ከዅሉም በላይ በምድራዊው ሕይወታችን የክርስቶስ ቤተ መቅደስ የኾነውን ሰውነታችንን ከኀጢአት ለይተን፣ ራሳችንን ለጽድቅ ሥራ አስገዝተን፣ በመንፈሳዊ ምግባር ጸንተን፣ ስንበድል ተጸጽተን (ንስሐ ገብተን)፣ ቅዱስ ሥጋውን በልተን፣ ክቡር ደሙን ጠጥተን ብንኖር የማያልፈውን መንግሥቱን ለመውረስ እንበቃለን፡፡

የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ የነቢዩ ስምዖን እና የነቢዪት ሐና፣ የሌሎችም ቅዱሳን በረከት ይደርብን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው ☞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13285

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

How to Invest in Bitcoin?

Like a stock, you can buy and hold Bitcoin as an investment. You can even now do so in special retirement accounts called Bitcoin IRAs. No matter where you choose to hold your Bitcoin, people’s philosophies on how to invest it vary: Some buy and hold long term, some buy and aim to sell after a price rally, and others bet on its price decreasing. Bitcoin’s price over time has experienced big price swings, going as low as $5,165 and as high as $28,990 in 2020 alone. “I think in some places, people might be using Bitcoin to pay for things, but the truth is that it’s an asset that looks like it’s going to be increasing in value relatively quickly for some time,” Marquez says. “So why would you sell something that’s going to be worth so much more next year than it is today? The majority of people that hold it are long-term investors.”

To pay the bills, Mr. Durov is issuing investors $1 billion to $1.5 billion of company debt, with the promise of discounted equity if the company eventually goes public, the people briefed on the plans said. He has also announced plans to start selling ads in public Telegram channels as soon as later this year, as well as offering other premium services for businesses and users.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from fr


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA