tg-me.com/heppymuslim29/6514
Last Update:
ሽማግሌው ሲጠባበቁት የነበረው አውቶብስ ስለመጣላቸው ለመሳፈር ተጠግተዋል፡፡ እግራቸውን አንስተው ወደ ውስጥ ሲገቡ በአጋጣሚ የአንድ እግር ጫማቸው ተንሸራቶ ውጭ ይቀራል፡፡
መልሰው ጫማቸውን ማግኘት ሳይችሉ አውቶብሱ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡
በዚህ ጊዜ ሽማግሌው ምንም አይነት የብስጭት ቃላት ሳያሰሙ የቀሪ እግራቸውን ጫማ ያወልቁና በመስኮት በኩል አሾልከው ወደ ውጭ ይጥሉታል፡፡
የሽማግሌውን ድርጊት ውስጥ ሁኖ ይመለከት የነበረ ወጣት ተሳፋሪ ለሽማግሌው እንዲህ ሲል ጥያቄውን አቀረበላቸው፡፡
“አባት ሲያደርጉ የነበሩትን ነገር እያየሁ ነበር፡፡ ለምንድን ነው ቀሪውን ጫማ የወረወሩት?” አላቸው፡፡
ሽማግሌውም ወዲያውኑ እንዲህ ሲሉ መለሱለት
“ ይኸውልህ ልጄ ሾልኮ የቀረውን ጫማ ሊጠቀሙበት የሚችሉት ይሄኛውም አብሮ ሲኖር ነው፡፡ እናም ለማንኛውም ያገኘው አካል ጥቅም እንዲሰጠው ወይም ዋጋ እንዲኖረው ስል ነው ይሄኛውን ጨምሬ መወርወሬ” አሉት፡፡
“የማትጠቀምበት ነገር ሁሉ ያንተ አይደለም!”
@heppymuslim29
BY HAppy Mûslimah
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/heppymuslim29/6514