Telegram Group & Telegram Channel
ጥበቃ.......

"እንዴት የሚያምር ቀን ነው"። በሚል ሀይለቃል ነበር ቀኔን የጀመርኩት። በጣም ደስ ብሎኝ ነበር በጠዋት የነቃሁት። ምክኒያቱም ለ 5 አመታት ሳልሰለች የጠበቅኩት ፍቅረኛዬ ይመጣል ። ለ አመታት ያሳለፍኳቸውን የጥበቃ ጊዚያቆች ሳስብ አንዳንዴ በፅናቴ እገረማለሁ። ከአሁን አሁን ይደውላል ጥበቃ፣ ከዛሬ ነገ ታገቢኛለሽ ብሎ ይጠይቀኛል ጥበቃ፣ ድንገት መጥቶ ሰርፕራይዝ ያደርገኛል ጥበቃ፣ ተኝቼ በህልሜ እስካየው ጥበቃ፣.................ብቻ ብዙ ብዙ ጥበቃ ለወትሮው እንደዚህ ትዕግስተኛ አልነበርኩም የያዘ ይዞኝ እንጅ........




ዛሬ ግን ይሄ ጥበቃየ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያበቃበት ቀን ነው። በቃ እፎይ የምልበት ቀን። ለዛም ነው በጠዋት ተነስቼ ቆንጆ ሆኜ የመጨረሻ ጥበቃየን ለመጠበቅ እየተዘጋጀሁ ያለሁት ። የሚወደውን ቆንጆ ሀምራዊ ቀሚስ አድርጌ፣ ፀጉሬን በግራ በኩል ከፍዬ ቆንጆ አድርጌ አስይዤዋለሁ። ጫማዬ ጥቁር ትንሽ ተለቅ ያለ ሄል ያለው ቆንጆ ጫማ ነው። ቦርሳዬ ዋው እሱ ድሮ የላከልኝ በጣም ምወደው ጥቁር ነጫጭ ፈርጥ ያለው ነው። በጊዜው ውድ የሚባለውን ሽቶ በላዬ ላይ አርከፍክፌ መስታወት ፊት ቆምኩ። መልኬ እንደዛሬ ቆንጆ ሆኖ ታይቶኝ አያውቅም። ብቻ ወጣሁ..............



ቦታው ጋ ደርሼ ሲመጣ ምን እንደምለው ፣ ከዛ በኋላ የምናደርጋቸውን ነገሮች፣ የሚኖረንን ሕይወት እያሰብኩ በደስታ አለም ውስጥ ራሴን አሰመጥኩት። ጠበቅኩ.....ጠበቅኩ...... ጥበቃው ሊሰለቸኝ ሲጀምር..... ለ አምስት አመት የጠበቅኩ ሴት አንድ ቀን መታገስማ አያቅተኝም ከዚህ በኋላኮ ላርፍ ነው ተመስገን እያልኩ ብቻየን እስቃለሁ። ብዙ ሰዓታት አለፉ ስልኩ አይሰራም........ሲመጣ መንገድ ላይ የሆነ ነገር ገጥሞት እንደሆነ ደመደምኩ። ነፍሴ ተጨነቀች...... ሳላገኘው ምን ሆኖብኝ ይሆን? ብቻ ውስጤ ፈራ....... ግን መጠበቅ አላቆምኩም ።ካለፉት አምስት አመታት ጥበቃ ይልቅ የዛሬው ጥበቃ እንደ ሺ አመት ረዘመብኝ። ............
ጥበቃው ቀጠለ። አንድ መልዕክት ስልኬ ጋር እስኪገባ ድረስ። እንዲህ ይል ነበር......


" የኔ ማር አትጠብቂኝ ለዘላለም አልመጣም!!!!"

የዛ ሁሉ አመት ጥበቃ በአንድ አረፍተነገር አከተመ!!!! "አልመጣም" መልዕክቱን ደጋግሜ አየሁት ውስጤ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ሲል ብቻ ተሰማኝ። አልጮህኩም፤ አላለቀስኩም። ምን እንደተሰማኝም አላውቅም ብቻ ግን ተሰበርኩ። ክንፏ እንደተመታ ወፍ ሙሽሽ አልኩ። ለካስ በጣም ሲታዘን እንባም ይደርቃል፣ ለመጮህም ቃላት ያልቃል።


ግን አንድ ነገር ልክ ነበርኩ። እንዳልኩት ዛሬ የመጨረሻ የጥበቃ ቀኔ ሆነ።ከዛሬ በኋላ አልጠብቅም!!!!




ከተቀመጥኩበት ተነስቼ በተሰበረ ልቤ ወደቤቴ መንገዴን ቀጠልኩ።

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot



tg-me.com/nibab_lehiwot/158
Create:
Last Update:

ጥበቃ.......

"እንዴት የሚያምር ቀን ነው"። በሚል ሀይለቃል ነበር ቀኔን የጀመርኩት። በጣም ደስ ብሎኝ ነበር በጠዋት የነቃሁት። ምክኒያቱም ለ 5 አመታት ሳልሰለች የጠበቅኩት ፍቅረኛዬ ይመጣል ። ለ አመታት ያሳለፍኳቸውን የጥበቃ ጊዚያቆች ሳስብ አንዳንዴ በፅናቴ እገረማለሁ። ከአሁን አሁን ይደውላል ጥበቃ፣ ከዛሬ ነገ ታገቢኛለሽ ብሎ ይጠይቀኛል ጥበቃ፣ ድንገት መጥቶ ሰርፕራይዝ ያደርገኛል ጥበቃ፣ ተኝቼ በህልሜ እስካየው ጥበቃ፣.................ብቻ ብዙ ብዙ ጥበቃ ለወትሮው እንደዚህ ትዕግስተኛ አልነበርኩም የያዘ ይዞኝ እንጅ........




ዛሬ ግን ይሄ ጥበቃየ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያበቃበት ቀን ነው። በቃ እፎይ የምልበት ቀን። ለዛም ነው በጠዋት ተነስቼ ቆንጆ ሆኜ የመጨረሻ ጥበቃየን ለመጠበቅ እየተዘጋጀሁ ያለሁት ። የሚወደውን ቆንጆ ሀምራዊ ቀሚስ አድርጌ፣ ፀጉሬን በግራ በኩል ከፍዬ ቆንጆ አድርጌ አስይዤዋለሁ። ጫማዬ ጥቁር ትንሽ ተለቅ ያለ ሄል ያለው ቆንጆ ጫማ ነው። ቦርሳዬ ዋው እሱ ድሮ የላከልኝ በጣም ምወደው ጥቁር ነጫጭ ፈርጥ ያለው ነው። በጊዜው ውድ የሚባለውን ሽቶ በላዬ ላይ አርከፍክፌ መስታወት ፊት ቆምኩ። መልኬ እንደዛሬ ቆንጆ ሆኖ ታይቶኝ አያውቅም። ብቻ ወጣሁ..............



ቦታው ጋ ደርሼ ሲመጣ ምን እንደምለው ፣ ከዛ በኋላ የምናደርጋቸውን ነገሮች፣ የሚኖረንን ሕይወት እያሰብኩ በደስታ አለም ውስጥ ራሴን አሰመጥኩት። ጠበቅኩ.....ጠበቅኩ...... ጥበቃው ሊሰለቸኝ ሲጀምር..... ለ አምስት አመት የጠበቅኩ ሴት አንድ ቀን መታገስማ አያቅተኝም ከዚህ በኋላኮ ላርፍ ነው ተመስገን እያልኩ ብቻየን እስቃለሁ። ብዙ ሰዓታት አለፉ ስልኩ አይሰራም........ሲመጣ መንገድ ላይ የሆነ ነገር ገጥሞት እንደሆነ ደመደምኩ። ነፍሴ ተጨነቀች...... ሳላገኘው ምን ሆኖብኝ ይሆን? ብቻ ውስጤ ፈራ....... ግን መጠበቅ አላቆምኩም ።ካለፉት አምስት አመታት ጥበቃ ይልቅ የዛሬው ጥበቃ እንደ ሺ አመት ረዘመብኝ። ............
ጥበቃው ቀጠለ። አንድ መልዕክት ስልኬ ጋር እስኪገባ ድረስ። እንዲህ ይል ነበር......


" የኔ ማር አትጠብቂኝ ለዘላለም አልመጣም!!!!"

የዛ ሁሉ አመት ጥበቃ በአንድ አረፍተነገር አከተመ!!!! "አልመጣም" መልዕክቱን ደጋግሜ አየሁት ውስጤ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ሲል ብቻ ተሰማኝ። አልጮህኩም፤ አላለቀስኩም። ምን እንደተሰማኝም አላውቅም ብቻ ግን ተሰበርኩ። ክንፏ እንደተመታ ወፍ ሙሽሽ አልኩ። ለካስ በጣም ሲታዘን እንባም ይደርቃል፣ ለመጮህም ቃላት ያልቃል።


ግን አንድ ነገር ልክ ነበርኩ። እንዳልኩት ዛሬ የመጨረሻ የጥበቃ ቀኔ ሆነ።ከዛሬ በኋላ አልጠብቅም!!!!




ከተቀመጥኩበት ተነስቼ በተሰበረ ልቤ ወደቤቴ መንገዴን ቀጠልኩ።

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot

BY ሕይወትን - በገፅ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/158

View MORE
Open in Telegram


ሕይወትን በገፅ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

NEWS: Telegram supports Facetime video calls NOW!

Secure video calling is in high demand. As an alternative to Zoom, many people are using end-to-end encrypted apps such as WhatsApp, FaceTime or Signal to speak to friends and family face-to-face since coronavirus lockdowns started to take place across the world. There’s another option—secure communications app Telegram just added video calling to its feature set, available on both iOS and Android. The new feature is also super secure—like Signal and WhatsApp and unlike Zoom (yet), video calls will be end-to-end encrypted.

Telegram Be The Next Best SPAC

I have no inside knowledge of a potential stock listing of the popular anti-Whatsapp messaging app, Telegram. But I know this much, judging by most people I talk to, especially crypto investors, if Telegram ever went public, people would gobble it up. I know I would. I’m waiting for it. So is Sergei Sergienko, who claims he owns $800,000 of Telegram’s pre-initial coin offering (ICO) tokens. “If Telegram does a SPAC IPO, there would be demand for this issue. It would probably outstrip the interest we saw during the ICO. Why? Because as of right now Telegram looks like a liberal application that can accept anyone - right after WhatsApp and others have turn on the censorship,” he says.

ሕይወትን በገፅ from hk


Telegram ሕይወትን - በገፅ
FROM USA