Telegram Group & Telegram Channel
🔆ከራሱ ጋር የተስማማ ከተፈጥሮው ሁሉ ጋር ይስማማል!
(Live in harmony with nature)

📍ተፈጥሮ የሰው አካል ነው፤ ሰውም የተፈጥሮ ውህድ ነው፡፡ ሰው ከተፈጥሮ ውጭ መሆን አይችልም፡፡ ከተፈጥሮው ውጪ ልሁን የሚል ሰው ካለ መጀመሪያ የሚጋጨው ከራሱ ጋር ነው፡፡ ሁለተኛም ከልዕለ የተፈጥሮ ሃይል ጋር ይላተማል፡፡ ብዙ ሰው ከሰው ጋር ተስማምቶ መኖርን ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን ከራሱና ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ መኖርን አይደፍርም፡፡ ተፈጥሮው በማይፈቅደው መንገድ የሚተራመሰው ይበዛል፡፡ ያልሆነውን ለመሆን የሚፍጨረጨር የትየለሌ ነው፡፡ ሰው ከተፈጥሮው ከራቀና ከሰውነቱ ካፈነገጠ አደጋ ላይ ነው፡፡ አንድም አዕምሮው ማሰብ አቁማል፤ ሁለትም ጤንነቱ አጠራጣሪ ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት ነው፡፡

📍ጥንታዊው ሮማዊው ፈላስፋ ሴኔካ ለሚወደው ጓደኛው ለሉሲሊየስ በፃፈው ደብዳቤ ላይ፡- ‹‹ከተፈጥሮ ጋር ተስማምተህ ከኖርክ በጭራሽ ደሃ አትሆንም፡፡ ነገር ግን እንደሌሎች ሃሳብ መኖር ከፈቀድክ ግን መቼም ቢሆን ሀብታም አትሆንም›› ብሎት ነበር፡፡ ሴኔካ ሀብትን ከቁስ ጋር አያይዞ አይደለም ይሄን የተናገረው፡፡ እሱ ሃብት የሚለው የመንፈስ ሀብትን ነው፡፡ ይሄ ደግሞ ከተፈጥሮ ጋር በመግባባት የሚገኝ ነው፡፡ ተፈጥሮን ማወቅ፣ መረዳትና ከተፈጥሮው ጋር ተጣጥሞና ተስማምቶ መኖር ሰውን በመንፈሳዊ ሃብት እንዲበለፅግ ያደርገዋል፡፡ ብዙዎቻችን በመንፈሳችን ያጣን የነጣን ደሃ የሆንነው አንድም ተፈጥሮውን ለመረዳት ባለመጣራችን ነው፤ ሁለትም ሰውነታችንን ከተፈጥሮው ጋር እያቃረንን ስለምንኖር ነው፡፡

💡ብዙ ሰው በራሱ ሃሳብ ሳይሆን በሌሎች ሃሳብ ነው ኑሮውን የሚገፋው፡፡ ሰው ስለእሱ በሚሰጠው ፍረጃና አስተያየት እየተመራ ህይወቱን ሲኦል የሚያደርግ እልፍ ነው፡፡ በርግጥ የሁሉም ሰው አስተያየት ሰውን ገደል ይከታል ማለት አይደለም፡፡ የዛኑ ያህል የተሰጠን አስተያየት ሁሉ የመጨረሻው እውነትም አይደለም፡፡ በሁለቱ መካከል ማሰብና መመርመር የሚባል ነገር አለ፡፡ የትኛውንም መጤ ሃሳብ በአዕምሮ ወንፊትነት ማጣራት ግድ ይላል፡፡ ሳያኝኩ እንደሚውጡ ሳያስቡ የሰውን ሃሳብና አስተያየት የሚተገብሩ ራሳቸውን አደጋ ውስጥ ይከታሉ ለማለት ነው፡፡

💎ታዋቂውን የግሪኩን ፈላስፋ ዲዮጋንን አንዱ እንዲህ ብሎ ጠየቀው፡- ‹‹በሕይወትና በሞት መሐል ልዩነቱ ምንድነው?›› ዲዮጋንም፡- ‹‹ምንም ልዩነት የለውም›› አለው፡፡ ‹‹ታዲያ አንተ ለምን በሕይወት ትኖራለህ? ራስህን አታጠፋም ነበር?›› ሲለው፤ ዲዮጋንም፡- ‹‹እሱም ቢሆን ምንም ልዩነት የለውም!›› አለው ይባላል፡፡ ዲዮጋን ሞትንም ሕይወትንም አንድ ያደረገው ሁለቱም የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ስለሆኑ ነው፡፡ ሞት ያለሕይወት፤ ህይወትም ያለሞት አልተፈጠረምና፡፡ ህይወትን ተቀብለህ ሞትን መተው አትችልም፡፡ ብዙዎች ከማያመልጡት ወጥመድ መሸሽ ይፈልጋሉ፡፡ ሞት የህይወትህ አካል ነው፡፡ የትም ብትሄድ አታመልጠውም፡፡ ይልቁንስ ህይወትንም ሞትንም ጠልቀህ ከተገነዘብክ አኗኗርህንና አኳኋንህን፤ መካከሉን ሕይወትህን እንድታስተካክል ይረዳሃል፡፡

📍የብዙዎቻችን አወዳደቅ ራሳችንን አለመሆናችን ነው፡፡ የእኛ የህይወት መስመር ከሌላው ጋር የሚወዳደር አይደለም፡፡ ብዙዎቻችን ከራሳችን ተፈጥሮ ጋር ተራርቀን ስላለን ደረጃችንን የምንወስነው በሌሎች መለኪያ ነው፡፡ ዋናውና ስሜትን የሚጎዳው አወዳደቅ ደግሞ በትናንት ውድቀታችን ዛሬአችንን ስናወሳስበው ነው፡፡ ሁለቱም አወዳደቆች ከተፈጥሯችን ጋር በመጋጨት የሚመጡ ናቸው፡፡

💎ወዳጄ ሆይ... ከተፈጥሮው ጋር ተስማምተህ ኑር፡፡ ከራስህ አትራቅ፡፡ የአንተነትህን ተመን ራስህ አውጣ፡፡ ደስታም ይሁን ሀዘን ያለው አዕምሮህ ውስጥ ነውና በሌሎች መለኪያ ሕይወትህን አታወዳድር፡፡ ደረጃህን በራስህ ወስን፡፡ ሌሎች ምንም ብትሆን አቃቂር ከማውጣት አይቦዝኑም፡፡ ሌሎች እንዲያመሰግኑህ ብለህ ራስህን አትጣል፡፡

📍ለህሊናህ ታመን፡፡ ውስጥህን አድምጥ! ተፈጥሮህን እወቀው፤ እውነትን ተከተል፡፡ አንተነትህን አናግረው፡፡ መንፈስህን አበልጽገው፡፡ ዕለት ዕለት ከራስህ ጋር ትነጋገር ዘንድ ልመድ! ሞት የሕይወትህ ክፋይ መሆኑን አትዘንጋ፡፡ መሄድህ ላይቀር ጥሩ ነገር ሰርተህ እለፍ! ከተፈጥሮውና ከተፈጥሮህ ተማር! ቀድመህ ከራስህ ጋር ተስማማ፤ ሌላው ቀሊል ነው!!

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot



tg-me.com/EthioHumanity/7134
Create:
Last Update:

🔆ከራሱ ጋር የተስማማ ከተፈጥሮው ሁሉ ጋር ይስማማል!
(Live in harmony with nature)

📍ተፈጥሮ የሰው አካል ነው፤ ሰውም የተፈጥሮ ውህድ ነው፡፡ ሰው ከተፈጥሮ ውጭ መሆን አይችልም፡፡ ከተፈጥሮው ውጪ ልሁን የሚል ሰው ካለ መጀመሪያ የሚጋጨው ከራሱ ጋር ነው፡፡ ሁለተኛም ከልዕለ የተፈጥሮ ሃይል ጋር ይላተማል፡፡ ብዙ ሰው ከሰው ጋር ተስማምቶ መኖርን ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን ከራሱና ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ መኖርን አይደፍርም፡፡ ተፈጥሮው በማይፈቅደው መንገድ የሚተራመሰው ይበዛል፡፡ ያልሆነውን ለመሆን የሚፍጨረጨር የትየለሌ ነው፡፡ ሰው ከተፈጥሮው ከራቀና ከሰውነቱ ካፈነገጠ አደጋ ላይ ነው፡፡ አንድም አዕምሮው ማሰብ አቁማል፤ ሁለትም ጤንነቱ አጠራጣሪ ደረጃ ላይ ደርሷል ማለት ነው፡፡

📍ጥንታዊው ሮማዊው ፈላስፋ ሴኔካ ለሚወደው ጓደኛው ለሉሲሊየስ በፃፈው ደብዳቤ ላይ፡- ‹‹ከተፈጥሮ ጋር ተስማምተህ ከኖርክ በጭራሽ ደሃ አትሆንም፡፡ ነገር ግን እንደሌሎች ሃሳብ መኖር ከፈቀድክ ግን መቼም ቢሆን ሀብታም አትሆንም›› ብሎት ነበር፡፡ ሴኔካ ሀብትን ከቁስ ጋር አያይዞ አይደለም ይሄን የተናገረው፡፡ እሱ ሃብት የሚለው የመንፈስ ሀብትን ነው፡፡ ይሄ ደግሞ ከተፈጥሮ ጋር በመግባባት የሚገኝ ነው፡፡ ተፈጥሮን ማወቅ፣ መረዳትና ከተፈጥሮው ጋር ተጣጥሞና ተስማምቶ መኖር ሰውን በመንፈሳዊ ሃብት እንዲበለፅግ ያደርገዋል፡፡ ብዙዎቻችን በመንፈሳችን ያጣን የነጣን ደሃ የሆንነው አንድም ተፈጥሮውን ለመረዳት ባለመጣራችን ነው፤ ሁለትም ሰውነታችንን ከተፈጥሮው ጋር እያቃረንን ስለምንኖር ነው፡፡

💡ብዙ ሰው በራሱ ሃሳብ ሳይሆን በሌሎች ሃሳብ ነው ኑሮውን የሚገፋው፡፡ ሰው ስለእሱ በሚሰጠው ፍረጃና አስተያየት እየተመራ ህይወቱን ሲኦል የሚያደርግ እልፍ ነው፡፡ በርግጥ የሁሉም ሰው አስተያየት ሰውን ገደል ይከታል ማለት አይደለም፡፡ የዛኑ ያህል የተሰጠን አስተያየት ሁሉ የመጨረሻው እውነትም አይደለም፡፡ በሁለቱ መካከል ማሰብና መመርመር የሚባል ነገር አለ፡፡ የትኛውንም መጤ ሃሳብ በአዕምሮ ወንፊትነት ማጣራት ግድ ይላል፡፡ ሳያኝኩ እንደሚውጡ ሳያስቡ የሰውን ሃሳብና አስተያየት የሚተገብሩ ራሳቸውን አደጋ ውስጥ ይከታሉ ለማለት ነው፡፡

💎ታዋቂውን የግሪኩን ፈላስፋ ዲዮጋንን አንዱ እንዲህ ብሎ ጠየቀው፡- ‹‹በሕይወትና በሞት መሐል ልዩነቱ ምንድነው?›› ዲዮጋንም፡- ‹‹ምንም ልዩነት የለውም›› አለው፡፡ ‹‹ታዲያ አንተ ለምን በሕይወት ትኖራለህ? ራስህን አታጠፋም ነበር?›› ሲለው፤ ዲዮጋንም፡- ‹‹እሱም ቢሆን ምንም ልዩነት የለውም!›› አለው ይባላል፡፡ ዲዮጋን ሞትንም ሕይወትንም አንድ ያደረገው ሁለቱም የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ስለሆኑ ነው፡፡ ሞት ያለሕይወት፤ ህይወትም ያለሞት አልተፈጠረምና፡፡ ህይወትን ተቀብለህ ሞትን መተው አትችልም፡፡ ብዙዎች ከማያመልጡት ወጥመድ መሸሽ ይፈልጋሉ፡፡ ሞት የህይወትህ አካል ነው፡፡ የትም ብትሄድ አታመልጠውም፡፡ ይልቁንስ ህይወትንም ሞትንም ጠልቀህ ከተገነዘብክ አኗኗርህንና አኳኋንህን፤ መካከሉን ሕይወትህን እንድታስተካክል ይረዳሃል፡፡

📍የብዙዎቻችን አወዳደቅ ራሳችንን አለመሆናችን ነው፡፡ የእኛ የህይወት መስመር ከሌላው ጋር የሚወዳደር አይደለም፡፡ ብዙዎቻችን ከራሳችን ተፈጥሮ ጋር ተራርቀን ስላለን ደረጃችንን የምንወስነው በሌሎች መለኪያ ነው፡፡ ዋናውና ስሜትን የሚጎዳው አወዳደቅ ደግሞ በትናንት ውድቀታችን ዛሬአችንን ስናወሳስበው ነው፡፡ ሁለቱም አወዳደቆች ከተፈጥሯችን ጋር በመጋጨት የሚመጡ ናቸው፡፡

💎ወዳጄ ሆይ... ከተፈጥሮው ጋር ተስማምተህ ኑር፡፡ ከራስህ አትራቅ፡፡ የአንተነትህን ተመን ራስህ አውጣ፡፡ ደስታም ይሁን ሀዘን ያለው አዕምሮህ ውስጥ ነውና በሌሎች መለኪያ ሕይወትህን አታወዳድር፡፡ ደረጃህን በራስህ ወስን፡፡ ሌሎች ምንም ብትሆን አቃቂር ከማውጣት አይቦዝኑም፡፡ ሌሎች እንዲያመሰግኑህ ብለህ ራስህን አትጣል፡፡

📍ለህሊናህ ታመን፡፡ ውስጥህን አድምጥ! ተፈጥሮህን እወቀው፤ እውነትን ተከተል፡፡ አንተነትህን አናግረው፡፡ መንፈስህን አበልጽገው፡፡ ዕለት ዕለት ከራስህ ጋር ትነጋገር ዘንድ ልመድ! ሞት የሕይወትህ ክፋይ መሆኑን አትዘንጋ፡፡ መሄድህ ላይቀር ጥሩ ነገር ሰርተህ እለፍ! ከተፈጥሮውና ከተፈጥሮህ ተማር! ቀድመህ ከራስህ ጋር ተስማማ፤ ሌላው ቀሊል ነው!!

ውብ አሁን❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot

BY ስብዕናችን #Humanity


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/EthioHumanity/7134

View MORE
Open in Telegram


ስብዕናችን Humanity Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram has exploded as a hub for cybercriminals looking to buy, sell and share stolen data and hacking tools, new research shows, as the messaging app emerges as an alternative to the dark web.An investigation by cyber intelligence group Cyberint, together with the Financial Times, found a ballooning network of hackers sharing data leaks on the popular messaging platform, sometimes in channels with tens of thousands of subscribers, lured by its ease of use and light-touch moderation.ስብዕናችን Humanity from id


Telegram ስብዕናችን #Humanity
FROM USA