Telegram Group & Telegram Channel
‹‹የብዕር ጥበብ›› አስተዋይ ወጣት ለኢትዮጵያ አንድነት በሚል ርዕስ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኪነ ጥበብ ፕሮግራም ተካሄደ
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል ‹‹የብዕር ጥበብ›› አስተዋይ ወጣት ለኢትዮጵያ አንድነት በሚል ርዕስ ሚያዝያ 8/2014 ዓ/ም የኪነ ጥበብ ፕሮግራም አካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ ጋዜጠኛና ደራሲ ዘነበ ወላ፣ ደራሲ መሐመድ አሊ (ቡርሃን አዲስ) እና የጋሞ አባቶች በተጋባዥ እንግድነት ተገኝተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በሰው ልጆች የእድገት ሂደት ወጣትነት ከፍተኛ የፈጠራ፣ የጥበብና የማኅበራዊ እሴት ሥራዎች አቅም የሚያድግበትና የሚፈፀምበት የሕይወት ምዕራፍ መሆኑን ተናግረው ወጣቱን በጥበብና በግብረ ገብ መገንባት ለአንድ ሀገር ሰላም፣ ሀገራዊ አንድነትና ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል፡፡ በተለይ በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን እየተፈጠሩ ያሉት ክስተቶች የኢትዮጵያን አንድነት እና የሕዝቡን ዘመናት የተሻገረ አብሮነትና ወንድማማችነት እንዳይጎጉ በማንበብና ጥበብን በማሳደግ የሚገኝ የአስተሳሰብ ብስለት ወጣቱ ንቁና በአላስፈላጊ ቡድኖች በቀላሉ የማይመራ እንዲሆን እንደሚረዳው ፕሬዝደንቱ ገልጸዋል፡፡ መሰል የሥነ ጽሑፍ ዝግጅቶችም ወጣቱ እርስ በእርሱ፣ የተሻለ ልምድ ካላቸውና ከማኅበረሰቡ ልምዶችንና አስተውሎቶችን በመጋራት የሚማማርበት ነው ብለዋል፡፡

ጋዜጠኛና ደራሲ ዘነበ ወላ ለተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በርካታ ኢንደስትሪዎችን የሚያንቃሳቅስና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር የሀገራችን ትልቅ በረከት መሆኑን ጠቅሶ ይህን እውን ለማድረግ በጽናትና በአንድነት በመቆም በጉልበትና በዕውቀት ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው ተናግሯል፡፡

ደራሲ ዘነበ ሥነ ጽሑፍ የሚያበረክተውን ፋይዳ ሲገልጽ በዓባይ ውኃ ላይ ግብጾች 2,200 መጻሕፍት፣ ከ10,000 በላይ ምሳሌያዊ ንግግሮችና 1,500 ጥናታዊ ጽሑፎች አሏቸው ብሏል፡፡ ተማሪዎች ተመርቀው ወደ ሥራ ዓለም ሲቀላቀሉ በየተሰማሩበት ዘርፍ ሁሉ በአስተዋይነት፣ በጥበብና የማንበብ ልምድን በማዳበር ለሀገራቸውም ሆነ ለዓለም የየራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

ደራሲ መሐመድ አሊ (ቡርሃን አዲስ) በበኩሉ ሃይማኖት፣ ባህልና ቤተሰብ ሀገራት ለረዥም ዓመታት ጠንካራ ሆነው የቆዩባቸው ዕሴቶች መሆናቸውን ተናግሮ በአሁኑ ሰዓት ግን በተለይ በተማረው ማኅበረሰብ አካባቢ እነዚህ እሴቶች የኋላቀርነት መገለጫ ተደርገው እየታዩ ነው ብሏል፡፡ እሴቶቹ የማኅበረሰብ ሞራልና ምግባርን የሚጠብቁ፣ ለሌሎች መኖርና ኃላፊነት መውሰድን የሚያስተምሩ እንዲሁም ማኅበረሰቡ ራሱን ሉዓላዊ አድርጎ እንዲቆይ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡

የተዛነፈ አመለካከትና ዕይታ ያለው ማኅበረሰብ የተቃና ሀገር ሊኖረው አይችልም ያለው ደራሲ መሐመድ መሰል ዝግጅቶች በወጣቶች መሰናዳታቸው ሀገርን የሚረከብና አንድነቷን የሚያስጠብቅ ትውልድ እንዳለ ተስፋ የሚሰጥ እንዲሁም ወጣቶች ስለ ሀገራቸው ያገባናል እንዲሉና ከልዩነታችን ይልቅ አንድ የሚያደርገንን ነገር በማጉላት ለመጪው ትውልድ መልካም ተሞክሮዎችን ማስተላለፍ እንድንችል የሚረዳን ነው ብሏል፡፡
የጋሞ አባቶች ተወካይ አቶ ሰዲቃ ስሜ ወጣቶች በሃይማኖት፣ በዘር፣ በቀለምና በብሔር ከመጋጨት ይልቅ ከጥላቻ ንግግሮች በመቆጠብ ሀገራዊ አንድነትን ለመገንባት እንዲሠሩና የጀመሩትን መልካም ተሞክሮ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል ሰብሳቢ ተማሪ ኢብራሂም ካሴ እንደገለጸው ፕሮግራሙ በዋናነት ወጣቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደ መሆኑ ተማሪዎች ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ሀገራዊና ሌሎች ይዘቶች ያላቸው አስተሳሰቦች ላይ ትኩረት በማድረግ አስተዋይ ወጣት እንዲሆኑ ያለመ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት መድረኮች መዘጋጀታቸው ተማሪዎች እንደ አካዳሚክ ትምህርታቸው ሁሉ በንባብ ዕውቀታቸውን በማዳበር አስተሳሰባቸውን ይገነባል ብሏል፡፡

በዕለቱ ግጥሞች፣ ቴአትር፣ ሥነ ጽሑፍ እና በከተማው ኪነት ባንድ የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችና ባህላዊ ጭፈራዎች ቀርበዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

#INFOKEN_BOOKS_AND_INFORMATION_CENTER
Join us @infokenamu



tg-me.com/infokenamu/1824
Create:
Last Update:

‹‹የብዕር ጥበብ›› አስተዋይ ወጣት ለኢትዮጵያ አንድነት በሚል ርዕስ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኪነ ጥበብ ፕሮግራም ተካሄደ
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል ‹‹የብዕር ጥበብ›› አስተዋይ ወጣት ለኢትዮጵያ አንድነት በሚል ርዕስ ሚያዝያ 8/2014 ዓ/ም የኪነ ጥበብ ፕሮግራም አካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ ጋዜጠኛና ደራሲ ዘነበ ወላ፣ ደራሲ መሐመድ አሊ (ቡርሃን አዲስ) እና የጋሞ አባቶች በተጋባዥ እንግድነት ተገኝተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በሰው ልጆች የእድገት ሂደት ወጣትነት ከፍተኛ የፈጠራ፣ የጥበብና የማኅበራዊ እሴት ሥራዎች አቅም የሚያድግበትና የሚፈፀምበት የሕይወት ምዕራፍ መሆኑን ተናግረው ወጣቱን በጥበብና በግብረ ገብ መገንባት ለአንድ ሀገር ሰላም፣ ሀገራዊ አንድነትና ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል፡፡ በተለይ በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን እየተፈጠሩ ያሉት ክስተቶች የኢትዮጵያን አንድነት እና የሕዝቡን ዘመናት የተሻገረ አብሮነትና ወንድማማችነት እንዳይጎጉ በማንበብና ጥበብን በማሳደግ የሚገኝ የአስተሳሰብ ብስለት ወጣቱ ንቁና በአላስፈላጊ ቡድኖች በቀላሉ የማይመራ እንዲሆን እንደሚረዳው ፕሬዝደንቱ ገልጸዋል፡፡ መሰል የሥነ ጽሑፍ ዝግጅቶችም ወጣቱ እርስ በእርሱ፣ የተሻለ ልምድ ካላቸውና ከማኅበረሰቡ ልምዶችንና አስተውሎቶችን በመጋራት የሚማማርበት ነው ብለዋል፡፡

ጋዜጠኛና ደራሲ ዘነበ ወላ ለተማሪዎች ባስተላለፈው መልዕክት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በርካታ ኢንደስትሪዎችን የሚያንቃሳቅስና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር የሀገራችን ትልቅ በረከት መሆኑን ጠቅሶ ይህን እውን ለማድረግ በጽናትና በአንድነት በመቆም በጉልበትና በዕውቀት ሁሉም የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው ተናግሯል፡፡

ደራሲ ዘነበ ሥነ ጽሑፍ የሚያበረክተውን ፋይዳ ሲገልጽ በዓባይ ውኃ ላይ ግብጾች 2,200 መጻሕፍት፣ ከ10,000 በላይ ምሳሌያዊ ንግግሮችና 1,500 ጥናታዊ ጽሑፎች አሏቸው ብሏል፡፡ ተማሪዎች ተመርቀው ወደ ሥራ ዓለም ሲቀላቀሉ በየተሰማሩበት ዘርፍ ሁሉ በአስተዋይነት፣ በጥበብና የማንበብ ልምድን በማዳበር ለሀገራቸውም ሆነ ለዓለም የየራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

ደራሲ መሐመድ አሊ (ቡርሃን አዲስ) በበኩሉ ሃይማኖት፣ ባህልና ቤተሰብ ሀገራት ለረዥም ዓመታት ጠንካራ ሆነው የቆዩባቸው ዕሴቶች መሆናቸውን ተናግሮ በአሁኑ ሰዓት ግን በተለይ በተማረው ማኅበረሰብ አካባቢ እነዚህ እሴቶች የኋላቀርነት መገለጫ ተደርገው እየታዩ ነው ብሏል፡፡ እሴቶቹ የማኅበረሰብ ሞራልና ምግባርን የሚጠብቁ፣ ለሌሎች መኖርና ኃላፊነት መውሰድን የሚያስተምሩ እንዲሁም ማኅበረሰቡ ራሱን ሉዓላዊ አድርጎ እንዲቆይ የሚያስችሉ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡

የተዛነፈ አመለካከትና ዕይታ ያለው ማኅበረሰብ የተቃና ሀገር ሊኖረው አይችልም ያለው ደራሲ መሐመድ መሰል ዝግጅቶች በወጣቶች መሰናዳታቸው ሀገርን የሚረከብና አንድነቷን የሚያስጠብቅ ትውልድ እንዳለ ተስፋ የሚሰጥ እንዲሁም ወጣቶች ስለ ሀገራቸው ያገባናል እንዲሉና ከልዩነታችን ይልቅ አንድ የሚያደርገንን ነገር በማጉላት ለመጪው ትውልድ መልካም ተሞክሮዎችን ማስተላለፍ እንድንችል የሚረዳን ነው ብሏል፡፡
የጋሞ አባቶች ተወካይ አቶ ሰዲቃ ስሜ ወጣቶች በሃይማኖት፣ በዘር፣ በቀለምና በብሔር ከመጋጨት ይልቅ ከጥላቻ ንግግሮች በመቆጠብ ሀገራዊ አንድነትን ለመገንባት እንዲሠሩና የጀመሩትን መልካም ተሞክሮ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል ሰብሳቢ ተማሪ ኢብራሂም ካሴ እንደገለጸው ፕሮግራሙ በዋናነት ወጣቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደ መሆኑ ተማሪዎች ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ሀገራዊና ሌሎች ይዘቶች ያላቸው አስተሳሰቦች ላይ ትኩረት በማድረግ አስተዋይ ወጣት እንዲሆኑ ያለመ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት መድረኮች መዘጋጀታቸው ተማሪዎች እንደ አካዳሚክ ትምህርታቸው ሁሉ በንባብ ዕውቀታቸውን በማዳበር አስተሳሰባቸውን ይገነባል ብሏል፡፡

በዕለቱ ግጥሞች፣ ቴአትር፣ ሥነ ጽሑፍ እና በከተማው ኪነት ባንድ የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችና ባህላዊ ጭፈራዎች ቀርበዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

#INFOKEN_BOOKS_AND_INFORMATION_CENTER
Join us @infokenamu

BY ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/infokenamu/1824

View MORE
Open in Telegram


ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram announces Search Filters

With the help of the Search Filters option, users can now filter search results by type. They can do that by using the new tabs: Media, Links, Files and others. Searches can be done based on the particular time period like by typing in the date or even “Yesterday”. If users type in the name of a person, group, channel or bot, an extra filter will be applied to the searches.

Tata Power whose core business is to generate, transmit and distribute electricity has made no money to investors in the last one decade. That is a big blunder considering it is one of the largest power generation companies in the country. One of the reasons is the company's huge debt levels which stood at ₹43,559 crore at the end of March 2021 compared to the company’s market capitalisation of ₹44,447 crore.

ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል from us


Telegram ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል
FROM USA