Telegram Group & Telegram Channel
#የቀጠለ

[እነሆ እግዚአብሔርና ስሙ ከተሰለቹበት ከተማ ደረስሁ። የሰማይ አሞሮችና የባህር ነፍሳት ግን ጠግበዋል። የማያመሰግኑበትን በረከት አግኝተዋል። ከማይፀለይበት ገበታ ዙሪያ ተሰይመዋል። ምስጋና ስላልከፈሉ ገበታቸው ከመሙላት አትጎድልም፣ እነሆ የእግዚአብሔርና የህግጋቱ አውዶች ፈርሰዋል። ወንድ ከወንድ ይጋባል፣ በወደደ ጊዜ ሰው ከእንስሳት ቢገባ ከልካይ የለበትም። የማያመሰኳና ሸኾናው ክፍት የሆነ ሁሉ ይበላል። እግራቸው ወደ ክፉ ሁሉ ትሮጣለች፣ ግን አልተሰናከለችም። ገፅ 10]

["ሀገር ይዘው ህዝብ ይፈልጋሉ።  እንደ እስራኤሎች ህዝብ ይዘው ሀገር በፈለጉ እንዴት ደግ ነበር፤ እንደ አሜሪካኖች መስፈሪያ ያጣች የሰፋሪዎች ጀልባ ብንሆን እንዴት መልካም ነበር።" ገፅ 123]

ኢትዮጵያኖች የቱንም ያህል ችግር ቢያቆራምዳቸውና አሌክስ በገለፀው ልክ ሰው ለመብላት የበቁ ሰዎች ቢሆኑ እንኳን ሰውነትን ተውና እንስሳ ሁኑ ማለት የተሻለ አማራጭ መንገድ እንደመጠቆም የሚቆጠር አይመስለኝም። በርካታ ቀውስ አለብን፣ ረሃብተኞች ነን፤ ነገር ግን የመዳረሻ ሞዴሎቻችን አሜሪካና እስራኤል ሊሆኑ አይገባም። ለምን እግዜራችንን ነካህ ወይም ደግሞ ስራን አምልኩ አልከን የሚል ጥያቄ ማንሳቴ አይደለም። ጥያቄው የትኛውን ችግራችንን ለመቅረፍ ነው በመስቀል ቆፍረን ዶማን የምንሳለመው የሚለው ነው።

ችግራችን ስንፍና ብቻ ነው ወይ? መጥገብ አለመቻላችን ብቻ ነው ወዬ? የሰማይ ዝናብ መጠበቃችን፣ ለሶስት ሺህ ምናምን ዓመት በበበሬ ማረሳችን፣ ቅዳሴና ሰዓታት መቆማችን ነው ወይ ይሄን ሁሉ ቀውስ ያመጣብን? ማነው በድፍረት ችግራችን ይሄ ብቻ ነው ብሎ ሊነግረን የሚችለው? አሌክስ በትክክል የገባው ነገር ቢኖር ችግርና ቀውስ ውስጥ ስለመሆናችን ብቻ ነው። ከዚያ በዘለለ የችግራችንን መንሰኤ ስንፍናና አምልኮ፣ ከችግራችን የመውጫ መንገዱ ደግሞ ለስራ ባሪያ መሆንን ብቻ እንደመፍትሄ መቁጠር የትም ሊያደርሰን አይችልም። ነጩ መንገድ አላዋጣንም ብሎ ሙሉ በሙሉ ጥቁሩን መከተል ዞሮ ዞሮ ሚዛኑን መሳቱ አይቀርም።

በአንድ የኪነጥበብ መድረክ ላይ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ በኢህአዴግና በደርግ መካከል የመንገድ እንጂ የመዳረሻ ለውጥ እንደሌለ ለማሳየት የጠቀሰውን ማብራሪያ ላካፍላችሁ። "ደርግ ብሔሮችን ሁሉ ችላ ብሎ ኢትዮጵያን በማጉላት ላይ ያተኮረ ሃገረ መንግስት ገነባ። ውጤቱ የሚያምር አለመሆኑን ተተኪው ኢህአዴግ ተገነዘበ። ኢህአዴግም ከደርግ ትምህርት ወሰድኩኝ ብሎ ኢትዮጵያን ተወና ብሔሮችን ብቻ በማጉላት ላይ ያተኮረ መንግስትን ገነባ። ያመጣው ውጤት ግን ከደርግ የባሰ መሆኑን ሁሉም የገፈቱ ቀማሽ ሁሉ ይረዳዋል።"

እዚህ ጋር የጎደለው ነጭም ጥቁርም ያልሆነው ግራጫው መንገድ ነው። ነገሮችን ከምንም በላይ ማቻቻል (Balance ማድረግ) ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ ችግር የዶማና የመስቀል ዋጋን በመለዋወጥ ብቻ የሚፈታ እንዴት ሊሆን ይችላል? በልባችን አብሮ ያደገውን እግዜርን ስንተወው ሽልማታችን ምንድነው? እንደ አሜሪካውያን መሆን? ይሄ የሚያጓጓ መዳረሻ አይደለም በጭራሽ። ያጓጓል ብንል እንኳን የልባችንን እግዜር ከመተው ጋር ሊመጣጠን ፈፅሞ አይችልም።

ሌላኛው ትልቁ ጥያቄ መዳረሻችን ምንድነው የሚለው ይሆናል። የሰው ልጅ መለወጥ አለበት ካልን ምንድነው መምሰል ያለበት። አንበሳ? ዝሆን? ንስር? ጉንዳን? ንብ? ወዘተ? ...የሰው ልጅ ሄዶ ሄዶ ተለውጦ ሰው ብቻ ነው መምሰል ያለበት። ሰው ደግሞ ሆዱን ስለሞላ ብቻ ምሉዕ አይሆንም። ጎተራው ስላልጎደለ ብቻ ደስታውን በእጁ ሊጨብጥ አይችልም። ምክንያቱም ሰው አንበሳም፣ ጅብም ጉንዳንም አይደለም። ሰው፣ ሰው ብቻ ነው። የመንፈስ ረሃብ አለበት፣ ልቦናው መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚያስፈልገው ያምናል። እንደዛ ባይሆን ኖሮ በየጊዜው አማዞን ጫካ ውስጥ እንደ አዲስ Discover የሚደረጉ  የጎሳ አባላት ድንጋይ ወይም ዛፍ ሲያመልኩ ባልተገኙ ነበር። በቃ ህገ ልቦናቸው ወይም የማሰብ አድማሳቸው አንዳች Devine Intervention እንዳለ ሹክ ብሏቸዋል። በገባቸው ልክም Connection ለመፍጠር ይተጋሉ።

ይሄ ይሄ ሁሉ ቢዘነጋ እና 'የእግዜር ጣልቃ ገብነት አያስፈልግም' የሚለው ላይ ብንደርስ እንኳን አለማየሁ አውቆ ችላ ያለው ነገር እንዳለ ይሰማኛል። እንደ ጃፓን በጠንካራ የሞራል እሴት ያልበለፀገና እንደ ቻይና ጠንካራ የህግ አንቀፆችን ያልተለማመደ ማህበረሰብ ይዘህ አንዲት የቀረች ማስፈራሪያን (ፈሪሀ እግዚአብሔርን) ተው ለማለት መነሳሳት በራሱ ፍፁም ኃላፊነት የጎደለው አካሄድም ይመስለኛል።

ስንቱ ነው ለፅድቅ ይሆነኛል እያለ የተቸገረን (በመስቀል መቆፈር የማይችልን) ሰው ሆድ የሚሞላው። ስንቱስ ነው በሰማይ ይመጣብኛል ብሎ የሚያምነውን ቅጣት እያሰበ ብቻ በሰዎች ላይ ክፋትን ከመስራት የሚያቅማማው? ቆይ ለመሆኑ በዚህ የኑሮ ውድነት ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ተረጋግተው በሰላም መገበያየት የቻሉት ለምንድነው? አንዱ እያድፋፋ ሌላው እየላሰ ግን አብረን መኖር የቻልነው በምን ምክንያት ነው? በፈሪሀ እግዚአብሔር አይደለም ወይ? ታዲያ ምንም አማራጭ ሳናለማምደው ያለውን (አለው ተብሎ የሚታሰበውን) ብቸኛ የጋራ መስመር ልንበጥስበት የምንታገለው?

በነገራችን ላይ እንኳን የእስራኤልና የአሜሪካውያን ስብእና ይቅርና የጃፓናውያን አኗኗርም በራሱ ኢትዮጲያኖች ሊቀኑበት የሚገባ ለመሆኑ በቂ ጥናት ያስፈልጋል። ምክንያቱ ደግሞ ከልክ ያለፈ የስራ ፍቅራቸው፣ ግላዊነታቸውና አንዱ በአንዱ ህይወት ውስጥ ቦታ አለመኖሩ በርካታ ወጣቶችን በጭንቀት ራሳቸውን እንዲያጠፉ ምክንያት ሆኗል። ህይወት Balancing ትፈልጋለች የሚባለውም ለዚህ ነው። በአጠቃላይ አለማየሁ ገላጋይ ያነሳቸው አብዛኞቹ በአመክንዮ ያልተደገፉ Dictated ገለፃዎቹ አንባቢ ላይ የመጋባት አቅም የላቸውም።

በሽማግሌ መዳኘትን፣ የታመመ መጠየቅን፣ የዝምድና ተዋረዳችንን ሁሉ በገፀባህሪ በኩል ሆኖ የሚኮንንበት መንገድ Aggressive ነው። ያለንን ሁሉ ነጥቆ ሊሰጠን የሚሞክረው ነገር ደግሞ ሊቀማን ከሚታገለው አንፃር አጓጊ አይደለም። አለን ብለን የምናምነው ወርቅ፣ እንጨት እንደሆነ ይነግረናል። በምትኩ 'አልማዝ ነው እንካችሁ' የሚለን ግን ጭራሹኑ አመድ ነው። ገንፎን አጥላልቶ ለሙቅ የማጎብደድ አይነት።

ሳጠቃልለው፣ መጀመሪያ ላይ እንዳነሳሁት የሰው ልጅ በሙሉ ዘርፈ ብዙ ቀውስ ውስጥ ነው። እንደ እከሌ መሆን አለብን ብለን በኩራት የምንጠቅሰው ቡድን ወይም ሃገር የለም። ሃምሳ ጎበዝ ካለ ሃምሳ ሰነፍ አይጠፋም። የሆነ ቦታ ሰዎች ተሰባስበው ክፋ ነገርን ሲያደርጉ ብናይ ሰው ሁሉ ክፉ ነው ማለት ተገቢ አይደለም። ሌላ ቦታ ላይም ሰዎች ተሰብስበው መልካምና ቀና የሆነን ነገር ሲያደርጉ ብናይ ሰው ሁሉ መልካም ነው አንልም። በቃ ሰው መልካምም ክፉም ነው። ኢትዮጵያም መልካም ሰዎችን ብቻ ለአለም እንድታስተዋውቅ የተቀበለችው ቀብድ የለም። በዓለም ካሉት ጨካኝ ሰዎች መካከል ኢትዮጵያ ድርሻ አላት። ዓለም ካሏት መልካም ሰዎች ውስጥም ኢትዮጵውያን አሉበት።

#የሚቀጥል



tg-me.com/infokenamu/1860
Create:
Last Update:

#የቀጠለ

[እነሆ እግዚአብሔርና ስሙ ከተሰለቹበት ከተማ ደረስሁ። የሰማይ አሞሮችና የባህር ነፍሳት ግን ጠግበዋል። የማያመሰግኑበትን በረከት አግኝተዋል። ከማይፀለይበት ገበታ ዙሪያ ተሰይመዋል። ምስጋና ስላልከፈሉ ገበታቸው ከመሙላት አትጎድልም፣ እነሆ የእግዚአብሔርና የህግጋቱ አውዶች ፈርሰዋል። ወንድ ከወንድ ይጋባል፣ በወደደ ጊዜ ሰው ከእንስሳት ቢገባ ከልካይ የለበትም። የማያመሰኳና ሸኾናው ክፍት የሆነ ሁሉ ይበላል። እግራቸው ወደ ክፉ ሁሉ ትሮጣለች፣ ግን አልተሰናከለችም። ገፅ 10]

["ሀገር ይዘው ህዝብ ይፈልጋሉ።  እንደ እስራኤሎች ህዝብ ይዘው ሀገር በፈለጉ እንዴት ደግ ነበር፤ እንደ አሜሪካኖች መስፈሪያ ያጣች የሰፋሪዎች ጀልባ ብንሆን እንዴት መልካም ነበር።" ገፅ 123]

ኢትዮጵያኖች የቱንም ያህል ችግር ቢያቆራምዳቸውና አሌክስ በገለፀው ልክ ሰው ለመብላት የበቁ ሰዎች ቢሆኑ እንኳን ሰውነትን ተውና እንስሳ ሁኑ ማለት የተሻለ አማራጭ መንገድ እንደመጠቆም የሚቆጠር አይመስለኝም። በርካታ ቀውስ አለብን፣ ረሃብተኞች ነን፤ ነገር ግን የመዳረሻ ሞዴሎቻችን አሜሪካና እስራኤል ሊሆኑ አይገባም። ለምን እግዜራችንን ነካህ ወይም ደግሞ ስራን አምልኩ አልከን የሚል ጥያቄ ማንሳቴ አይደለም። ጥያቄው የትኛውን ችግራችንን ለመቅረፍ ነው በመስቀል ቆፍረን ዶማን የምንሳለመው የሚለው ነው።

ችግራችን ስንፍና ብቻ ነው ወይ? መጥገብ አለመቻላችን ብቻ ነው ወዬ? የሰማይ ዝናብ መጠበቃችን፣ ለሶስት ሺህ ምናምን ዓመት በበበሬ ማረሳችን፣ ቅዳሴና ሰዓታት መቆማችን ነው ወይ ይሄን ሁሉ ቀውስ ያመጣብን? ማነው በድፍረት ችግራችን ይሄ ብቻ ነው ብሎ ሊነግረን የሚችለው? አሌክስ በትክክል የገባው ነገር ቢኖር ችግርና ቀውስ ውስጥ ስለመሆናችን ብቻ ነው። ከዚያ በዘለለ የችግራችንን መንሰኤ ስንፍናና አምልኮ፣ ከችግራችን የመውጫ መንገዱ ደግሞ ለስራ ባሪያ መሆንን ብቻ እንደመፍትሄ መቁጠር የትም ሊያደርሰን አይችልም። ነጩ መንገድ አላዋጣንም ብሎ ሙሉ በሙሉ ጥቁሩን መከተል ዞሮ ዞሮ ሚዛኑን መሳቱ አይቀርም።

በአንድ የኪነጥበብ መድረክ ላይ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ በኢህአዴግና በደርግ መካከል የመንገድ እንጂ የመዳረሻ ለውጥ እንደሌለ ለማሳየት የጠቀሰውን ማብራሪያ ላካፍላችሁ። "ደርግ ብሔሮችን ሁሉ ችላ ብሎ ኢትዮጵያን በማጉላት ላይ ያተኮረ ሃገረ መንግስት ገነባ። ውጤቱ የሚያምር አለመሆኑን ተተኪው ኢህአዴግ ተገነዘበ። ኢህአዴግም ከደርግ ትምህርት ወሰድኩኝ ብሎ ኢትዮጵያን ተወና ብሔሮችን ብቻ በማጉላት ላይ ያተኮረ መንግስትን ገነባ። ያመጣው ውጤት ግን ከደርግ የባሰ መሆኑን ሁሉም የገፈቱ ቀማሽ ሁሉ ይረዳዋል።"

እዚህ ጋር የጎደለው ነጭም ጥቁርም ያልሆነው ግራጫው መንገድ ነው። ነገሮችን ከምንም በላይ ማቻቻል (Balance ማድረግ) ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ ችግር የዶማና የመስቀል ዋጋን በመለዋወጥ ብቻ የሚፈታ እንዴት ሊሆን ይችላል? በልባችን አብሮ ያደገውን እግዜርን ስንተወው ሽልማታችን ምንድነው? እንደ አሜሪካውያን መሆን? ይሄ የሚያጓጓ መዳረሻ አይደለም በጭራሽ። ያጓጓል ብንል እንኳን የልባችንን እግዜር ከመተው ጋር ሊመጣጠን ፈፅሞ አይችልም።

ሌላኛው ትልቁ ጥያቄ መዳረሻችን ምንድነው የሚለው ይሆናል። የሰው ልጅ መለወጥ አለበት ካልን ምንድነው መምሰል ያለበት። አንበሳ? ዝሆን? ንስር? ጉንዳን? ንብ? ወዘተ? ...የሰው ልጅ ሄዶ ሄዶ ተለውጦ ሰው ብቻ ነው መምሰል ያለበት። ሰው ደግሞ ሆዱን ስለሞላ ብቻ ምሉዕ አይሆንም። ጎተራው ስላልጎደለ ብቻ ደስታውን በእጁ ሊጨብጥ አይችልም። ምክንያቱም ሰው አንበሳም፣ ጅብም ጉንዳንም አይደለም። ሰው፣ ሰው ብቻ ነው። የመንፈስ ረሃብ አለበት፣ ልቦናው መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት እንደሚያስፈልገው ያምናል። እንደዛ ባይሆን ኖሮ በየጊዜው አማዞን ጫካ ውስጥ እንደ አዲስ Discover የሚደረጉ  የጎሳ አባላት ድንጋይ ወይም ዛፍ ሲያመልኩ ባልተገኙ ነበር። በቃ ህገ ልቦናቸው ወይም የማሰብ አድማሳቸው አንዳች Devine Intervention እንዳለ ሹክ ብሏቸዋል። በገባቸው ልክም Connection ለመፍጠር ይተጋሉ።

ይሄ ይሄ ሁሉ ቢዘነጋ እና 'የእግዜር ጣልቃ ገብነት አያስፈልግም' የሚለው ላይ ብንደርስ እንኳን አለማየሁ አውቆ ችላ ያለው ነገር እንዳለ ይሰማኛል። እንደ ጃፓን በጠንካራ የሞራል እሴት ያልበለፀገና እንደ ቻይና ጠንካራ የህግ አንቀፆችን ያልተለማመደ ማህበረሰብ ይዘህ አንዲት የቀረች ማስፈራሪያን (ፈሪሀ እግዚአብሔርን) ተው ለማለት መነሳሳት በራሱ ፍፁም ኃላፊነት የጎደለው አካሄድም ይመስለኛል።

ስንቱ ነው ለፅድቅ ይሆነኛል እያለ የተቸገረን (በመስቀል መቆፈር የማይችልን) ሰው ሆድ የሚሞላው። ስንቱስ ነው በሰማይ ይመጣብኛል ብሎ የሚያምነውን ቅጣት እያሰበ ብቻ በሰዎች ላይ ክፋትን ከመስራት የሚያቅማማው? ቆይ ለመሆኑ በዚህ የኑሮ ውድነት ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ተረጋግተው በሰላም መገበያየት የቻሉት ለምንድነው? አንዱ እያድፋፋ ሌላው እየላሰ ግን አብረን መኖር የቻልነው በምን ምክንያት ነው? በፈሪሀ እግዚአብሔር አይደለም ወይ? ታዲያ ምንም አማራጭ ሳናለማምደው ያለውን (አለው ተብሎ የሚታሰበውን) ብቸኛ የጋራ መስመር ልንበጥስበት የምንታገለው?

በነገራችን ላይ እንኳን የእስራኤልና የአሜሪካውያን ስብእና ይቅርና የጃፓናውያን አኗኗርም በራሱ ኢትዮጲያኖች ሊቀኑበት የሚገባ ለመሆኑ በቂ ጥናት ያስፈልጋል። ምክንያቱ ደግሞ ከልክ ያለፈ የስራ ፍቅራቸው፣ ግላዊነታቸውና አንዱ በአንዱ ህይወት ውስጥ ቦታ አለመኖሩ በርካታ ወጣቶችን በጭንቀት ራሳቸውን እንዲያጠፉ ምክንያት ሆኗል። ህይወት Balancing ትፈልጋለች የሚባለውም ለዚህ ነው። በአጠቃላይ አለማየሁ ገላጋይ ያነሳቸው አብዛኞቹ በአመክንዮ ያልተደገፉ Dictated ገለፃዎቹ አንባቢ ላይ የመጋባት አቅም የላቸውም።

በሽማግሌ መዳኘትን፣ የታመመ መጠየቅን፣ የዝምድና ተዋረዳችንን ሁሉ በገፀባህሪ በኩል ሆኖ የሚኮንንበት መንገድ Aggressive ነው። ያለንን ሁሉ ነጥቆ ሊሰጠን የሚሞክረው ነገር ደግሞ ሊቀማን ከሚታገለው አንፃር አጓጊ አይደለም። አለን ብለን የምናምነው ወርቅ፣ እንጨት እንደሆነ ይነግረናል። በምትኩ 'አልማዝ ነው እንካችሁ' የሚለን ግን ጭራሹኑ አመድ ነው። ገንፎን አጥላልቶ ለሙቅ የማጎብደድ አይነት።

ሳጠቃልለው፣ መጀመሪያ ላይ እንዳነሳሁት የሰው ልጅ በሙሉ ዘርፈ ብዙ ቀውስ ውስጥ ነው። እንደ እከሌ መሆን አለብን ብለን በኩራት የምንጠቅሰው ቡድን ወይም ሃገር የለም። ሃምሳ ጎበዝ ካለ ሃምሳ ሰነፍ አይጠፋም። የሆነ ቦታ ሰዎች ተሰባስበው ክፋ ነገርን ሲያደርጉ ብናይ ሰው ሁሉ ክፉ ነው ማለት ተገቢ አይደለም። ሌላ ቦታ ላይም ሰዎች ተሰብስበው መልካምና ቀና የሆነን ነገር ሲያደርጉ ብናይ ሰው ሁሉ መልካም ነው አንልም። በቃ ሰው መልካምም ክፉም ነው። ኢትዮጵያም መልካም ሰዎችን ብቻ ለአለም እንድታስተዋውቅ የተቀበለችው ቀብድ የለም። በዓለም ካሉት ጨካኝ ሰዎች መካከል ኢትዮጵያ ድርሻ አላት። ዓለም ካሏት መልካም ሰዎች ውስጥም ኢትዮጵውያን አሉበት።

#የሚቀጥል

BY ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/infokenamu/1860

View MORE
Open in Telegram


ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram has exploded as a hub for cybercriminals looking to buy, sell and share stolen data and hacking tools, new research shows, as the messaging app emerges as an alternative to the dark web.An investigation by cyber intelligence group Cyberint, together with the Financial Times, found a ballooning network of hackers sharing data leaks on the popular messaging platform, sometimes in channels with tens of thousands of subscribers, lured by its ease of use and light-touch moderation.ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል from us


Telegram ኢንፎክን የመጻሕፍት እና የመረጃ ማዕከል
FROM USA