Telegram Group & Telegram Channel
#ጾም_በክርስትና_ሕይወት

በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን
1.የጾም ትርጉም
2.ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
3.የጾም ጥቅሞች
4.በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡
ከላይ ከ1-4 ተራ ቊጥር የተገለጹትን እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡

1ኛ/ የጾም ትርጉም
ጾም፡- ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ማለት ሲሆን ከሥጋ፣ ከቅቤና፣ ከእንቁላል ደግሞ እንድንጾምባቸው የተወሰኑ የአጽዋማት ሳምንታት እስኪጠናቀቁ የምንከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 15/
ከዚህም ጋር ጾም ማለት፡- ዓይን ክፉ ከማየት ጆሮ ክፉ ከመስማት፣ አንደበት ክፉ ከመናገር፣ እጅ ክፉ ከመሥራት በአጠቃላይ ሰውነት የኃጢአት ሥራ ከመሥራት የሚገታበት፣ የሚከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ቅዱስ ያሬድ/

ጾም፡- ሁለት ዓይነት ነው ይኸውም
ሀ. የአዋጅ ጾም ነው፡- ይህም በስውር ሳይሆን ሁሉ አውቆት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ይህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አለው፡፡ “በጽዮን መለከትን ንፉ ጾምንም ቀድሱ ጉባኤውንም አውጁ” /ኢዩ. 2፡15/
ሰባቱ አጽዋማት የአዋጅ ጾሞች ናቸው፡፡ እነዚህም እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1. የነቢያት ጾም
2. የገሀድ ጾም
3. የነነዌ ጾም
4. ዐቢይ ጾም
5. የሐዋርያት ጾም
6. ጾመ ድኅነት /ረቡዕና ዓርብ/
7.ጾመ ፍልሰታ
ለ. የግል ጾም ነው፡- የግል ጾም ስንል አንድ ሰው በሠራው ኃጢአት ምክንያት ለንስሓ አባቱ ተናግሮ የሚሰጠው የንስሓ ጾም ሲሆን እንዲሁም አንድ ሰው ስለደረሰበትና በእርሱ ላይ ስለሆነ ነገር ስለሚፈልገው ጉዳይ እግዚአብሔር ተገቢውን መልስ እንዲሰጠው የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት ልጁ በታመመ ጊዜ ጹሟል፡፡ /2ኛ.ሳሙ. 12፡16/
ነገር ግን በግል ጾም ጊዜ ጾሙ ይፋ ስላልሆነ ራስን መሰወር እንደሚያስፈልግ ታዟል፡፡
ይህንንም አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “ስትጾሙም እንደ ግብዞች አትጠውልጉ ለሰዎች ሊታዩ እንደ ጾመኛ ፊታቸውን ያጠወልጋሉና አንተ ግን ስትጾም ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ በስውር የሚያይህ አባትህ በግልጥ ይከፍልሃል” /ማቴ. 6፡16-18/ ይህ ቅዱስ ቃል ስለግል ጾም የተነገረ ነው፡፡ በዚህ መሠረት የግል ጾምን ከጿሚው ሰው እና ከእግዚአብሔር ውጭ ማንም ማወቅ የለበትም፡፡

2ኛ/ ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
ጾም፡- ያስፈለገበት ምክንያት ልጓመ ሥጋ ስለሆነ ነው፡፡ ሰው ሁልጊዜ የጣመ የላመ ምግብ የማይለየውና እንደልቡ እየበላ እየጠጣ ሳይጾም የሚኖር ከሆነ ለኃጢአት ይጋለጣል፡፡ ይህም በፍትሐ ነገሥት ተጽፏል፡፡ “ከመ ያድክም ኃይለ ፍትወት” (ኃይለ ፍትወትን፣ ሥጋዊ ፍትወትን ያደክም ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም በምንጾምበት ጊዜ ረሀብን፣ ችግርን እናውቃለን፡፡ “ከመ ያእምር ጸዋሚ ሕማመ ረኀብ ወይምሐሮሙ ለርኁባን” (ጿሚ ሰው የረኀብን ችግር ያውቅ ዘንድና ለተራቡ ይራራ ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም “ችግርን የቀመሰ ችግርን ያውቃል” እንዲሉ አባቶቻችን፡፡

3ኛ/ የጾም ጥቅሞች
የጾም ጥቅሞች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1.በጾም መንግሥተ ሰማያትን እንወርሳለን፡፡
ይህንንም የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለጽድቅ ብለው የሚራቡና የሚጠሙ ንዑዳን ክቡራን ናቸው እነርሱ ይጠግባሉና” /ማቴ. 5፡6/ ሲል ተናግሯል፡፡
2.በጾም በአገር ላይ የታዘዘው መቅሠፍት ይርቃል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾሙ፡፡ ለእነርሱ የታዘዘው እሳት የዛፉን ጫፍ ጫፍ አቃጥሎ ተመልሷል፡፡ /ትን ዮናስ ም. 3 በሙሉ/

3.በጾም ሰይጣን ድል ይሆናል፡፡
“እንዲህ ዓይነት አብሮ አደግ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም” /ማቴ. 17፡21/ ሲል ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌል የተናገረው ቃል ሰይጣን በጾም ድል እንደሚሆን የሚገልጽ ነው፡፡
4.ጾም ከፈተና፣ ከመከራ ያድናል፡፡
ነቢዩ ዳንኤል በጾም ከአፈ አናብስት (ከአንበሶች አፍ) ድኗል፡፡ /ትን. ዳን. ም. 6 በሙሉ/ ሶስና በጾም ከሐሰት ምስክሮች ድናለች፡፡ /መጽ. ሶስና ም. 1 ሙሉ/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ከፈተና፣ ከመከራ ድነዋል፡፡
5.ጾም ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት በመሆኑ ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በገድላቸው እንደተጻፈው ዕድሜልካቸውን በጾም ነው የኖሩት የእናታቸውን ጡት እንኳን አልጠቡም፡፡ በዚህ ዓለም የኖሩት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ዓመት ነው፡፡ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም የዕድሜ ባለጸጎች ሆነዋል፡፡
6.በጾም ምስጢር ይገለጻል፡፡
አይሁድ አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ቆነጻጽለው ባጠፏቸው ጊዜ ዕዝራ ሱቱኤል አዝኖ አርባ ቀን ጾመ ከዚህ በኋላ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ሰማያዊ መጠጥ በብርሃን ጽዋ (ጽዋዓ እሳት) ለዕዝራ አጠጣው ዕዝራም ምስጢር ተገልጾለት አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ጽፏል፡፡ /መጽ. ዕዝ. ሱቱ. 13፡36-41/ ሌሎችም ደጋግ ሰዎች በጾም ምስጢር ተገልጾላቸዋል፡፡
7.በጾም ኃጢአት ይሠረያል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾመው ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ /ትን. ዮናስ ም. 3 በሙሉ/ ሌሎችም ሰዎች በጾም ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ ይህንንም ታላቁ ሊቅ መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ያሬድ በዜማ ድርሰቱ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “በጾም ወበጸሎት ይሠረይ ኃጢአት” (በጾምና በጸሎት ኃጢአት ይሠረያል)
8.በጾም ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ይቻላል፡፡
ሊቀ ነቢያት ሙሴ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል በቃል ተነጋግሯል፡፡ /ዘዳግም. 9፡9-14/
ነቢዩ ኤልያስም በጾም ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሯል፡፡ /1ኛ. መጽ. ነገ. 17፡2/
9.በጾም ልመናችን ይፈጸማል፡፡
እስራኤል በጾም የለመኑትን አግኝተዋል፡፡ /1ኛ ሳሙ. 7፡6-14/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ልመናቸው ተፈጽሞላቸዋል፡፡
የጾም ጥቅሞች ከላይ ከ1-9 ተራ ቊጥር የተገለጹ ሲሆን ከላይ በርእሱ እንደተገለጸው ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት ሲሆን በአንጻሩ አለመጾም ደግሞ የኃጢአት ሁሉ መሠረት ነው፡፡ ምክንያቱም ሰው ካልጾመ ለብዙ ኃጢአት ይጋለጣል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰዎች የተሰጠው የጾም ትእዛዝ ነው፡፡ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን፡- ይህን ዕፀ በለስ አትብሉ ሲል ከዕፀ በለሱ ተከልከሉ ጹሙ ማለቱ ነው፡፡ እነርሱ ግን አትብሉ የተባሉትን በሉ ከገነት ወጡ ተጎዱ አለመጾም ያስጎዳል፡፡ በዚህ መሠረት ኃጢአት በመብል ምክንያት ወደዓለም ገባ፡፡

4ኛ/ በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጾም፡- ከትርጉሙ እንደተረዳነው ከእህል ከውኃ ከመከልከሉ ጋር ከክፉ ነገር ከኃጢአት መራቅ ስለሆነ ጾማችን ከክፉ ነገር በመራቅ፣ በቅን ልቡና፣ በንጹሕ ልብ መሆን አለበት፡፡ እንዲሁም ነቢዩ ኢሳይያስ “በምትጾምበት ጊዜ እንጀራህን ለተራበ ብትቆርስ ብርሃንህ እንደንጋት ይበራል የዚያን ጊዜ ትጠራለህ እግዚአብሔርም ይሰማሃል ትጮሀለህ እርሱም እነሆ ይልሃል” /ኢሳ. 58፡6-9/ ባለው መሠረት በጾም ጊዜ የጧት ቁርሳችን ለድሆች ከተሰጠ ሰማያዊ ዋጋ እናገኛለን፡፡



tg-me.com/orthodox1/13232
Create:
Last Update:

#ጾም_በክርስትና_ሕይወት

በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን
1.የጾም ትርጉም
2.ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
3.የጾም ጥቅሞች
4.በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡
ከላይ ከ1-4 ተራ ቊጥር የተገለጹትን እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡

1ኛ/ የጾም ትርጉም
ጾም፡- ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ማለት ሲሆን ከሥጋ፣ ከቅቤና፣ ከእንቁላል ደግሞ እንድንጾምባቸው የተወሰኑ የአጽዋማት ሳምንታት እስኪጠናቀቁ የምንከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 15/
ከዚህም ጋር ጾም ማለት፡- ዓይን ክፉ ከማየት ጆሮ ክፉ ከመስማት፣ አንደበት ክፉ ከመናገር፣ እጅ ክፉ ከመሥራት በአጠቃላይ ሰውነት የኃጢአት ሥራ ከመሥራት የሚገታበት፣ የሚከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ቅዱስ ያሬድ/

ጾም፡- ሁለት ዓይነት ነው ይኸውም
ሀ. የአዋጅ ጾም ነው፡- ይህም በስውር ሳይሆን ሁሉ አውቆት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ይህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አለው፡፡ “በጽዮን መለከትን ንፉ ጾምንም ቀድሱ ጉባኤውንም አውጁ” /ኢዩ. 2፡15/
ሰባቱ አጽዋማት የአዋጅ ጾሞች ናቸው፡፡ እነዚህም እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1. የነቢያት ጾም
2. የገሀድ ጾም
3. የነነዌ ጾም
4. ዐቢይ ጾም
5. የሐዋርያት ጾም
6. ጾመ ድኅነት /ረቡዕና ዓርብ/
7.ጾመ ፍልሰታ
ለ. የግል ጾም ነው፡- የግል ጾም ስንል አንድ ሰው በሠራው ኃጢአት ምክንያት ለንስሓ አባቱ ተናግሮ የሚሰጠው የንስሓ ጾም ሲሆን እንዲሁም አንድ ሰው ስለደረሰበትና በእርሱ ላይ ስለሆነ ነገር ስለሚፈልገው ጉዳይ እግዚአብሔር ተገቢውን መልስ እንዲሰጠው የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት ልጁ በታመመ ጊዜ ጹሟል፡፡ /2ኛ.ሳሙ. 12፡16/
ነገር ግን በግል ጾም ጊዜ ጾሙ ይፋ ስላልሆነ ራስን መሰወር እንደሚያስፈልግ ታዟል፡፡
ይህንንም አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “ስትጾሙም እንደ ግብዞች አትጠውልጉ ለሰዎች ሊታዩ እንደ ጾመኛ ፊታቸውን ያጠወልጋሉና አንተ ግን ስትጾም ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ በስውር የሚያይህ አባትህ በግልጥ ይከፍልሃል” /ማቴ. 6፡16-18/ ይህ ቅዱስ ቃል ስለግል ጾም የተነገረ ነው፡፡ በዚህ መሠረት የግል ጾምን ከጿሚው ሰው እና ከእግዚአብሔር ውጭ ማንም ማወቅ የለበትም፡፡

2ኛ/ ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
ጾም፡- ያስፈለገበት ምክንያት ልጓመ ሥጋ ስለሆነ ነው፡፡ ሰው ሁልጊዜ የጣመ የላመ ምግብ የማይለየውና እንደልቡ እየበላ እየጠጣ ሳይጾም የሚኖር ከሆነ ለኃጢአት ይጋለጣል፡፡ ይህም በፍትሐ ነገሥት ተጽፏል፡፡ “ከመ ያድክም ኃይለ ፍትወት” (ኃይለ ፍትወትን፣ ሥጋዊ ፍትወትን ያደክም ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም በምንጾምበት ጊዜ ረሀብን፣ ችግርን እናውቃለን፡፡ “ከመ ያእምር ጸዋሚ ሕማመ ረኀብ ወይምሐሮሙ ለርኁባን” (ጿሚ ሰው የረኀብን ችግር ያውቅ ዘንድና ለተራቡ ይራራ ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም “ችግርን የቀመሰ ችግርን ያውቃል” እንዲሉ አባቶቻችን፡፡

3ኛ/ የጾም ጥቅሞች
የጾም ጥቅሞች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1.በጾም መንግሥተ ሰማያትን እንወርሳለን፡፡
ይህንንም የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለጽድቅ ብለው የሚራቡና የሚጠሙ ንዑዳን ክቡራን ናቸው እነርሱ ይጠግባሉና” /ማቴ. 5፡6/ ሲል ተናግሯል፡፡
2.በጾም በአገር ላይ የታዘዘው መቅሠፍት ይርቃል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾሙ፡፡ ለእነርሱ የታዘዘው እሳት የዛፉን ጫፍ ጫፍ አቃጥሎ ተመልሷል፡፡ /ትን ዮናስ ም. 3 በሙሉ/

3.በጾም ሰይጣን ድል ይሆናል፡፡
“እንዲህ ዓይነት አብሮ አደግ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም” /ማቴ. 17፡21/ ሲል ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌል የተናገረው ቃል ሰይጣን በጾም ድል እንደሚሆን የሚገልጽ ነው፡፡
4.ጾም ከፈተና፣ ከመከራ ያድናል፡፡
ነቢዩ ዳንኤል በጾም ከአፈ አናብስት (ከአንበሶች አፍ) ድኗል፡፡ /ትን. ዳን. ም. 6 በሙሉ/ ሶስና በጾም ከሐሰት ምስክሮች ድናለች፡፡ /መጽ. ሶስና ም. 1 ሙሉ/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ከፈተና፣ ከመከራ ድነዋል፡፡
5.ጾም ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት በመሆኑ ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በገድላቸው እንደተጻፈው ዕድሜልካቸውን በጾም ነው የኖሩት የእናታቸውን ጡት እንኳን አልጠቡም፡፡ በዚህ ዓለም የኖሩት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ዓመት ነው፡፡ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም የዕድሜ ባለጸጎች ሆነዋል፡፡
6.በጾም ምስጢር ይገለጻል፡፡
አይሁድ አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ቆነጻጽለው ባጠፏቸው ጊዜ ዕዝራ ሱቱኤል አዝኖ አርባ ቀን ጾመ ከዚህ በኋላ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ሰማያዊ መጠጥ በብርሃን ጽዋ (ጽዋዓ እሳት) ለዕዝራ አጠጣው ዕዝራም ምስጢር ተገልጾለት አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ጽፏል፡፡ /መጽ. ዕዝ. ሱቱ. 13፡36-41/ ሌሎችም ደጋግ ሰዎች በጾም ምስጢር ተገልጾላቸዋል፡፡
7.በጾም ኃጢአት ይሠረያል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾመው ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ /ትን. ዮናስ ም. 3 በሙሉ/ ሌሎችም ሰዎች በጾም ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ ይህንንም ታላቁ ሊቅ መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ያሬድ በዜማ ድርሰቱ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “በጾም ወበጸሎት ይሠረይ ኃጢአት” (በጾምና በጸሎት ኃጢአት ይሠረያል)
8.በጾም ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ይቻላል፡፡
ሊቀ ነቢያት ሙሴ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል በቃል ተነጋግሯል፡፡ /ዘዳግም. 9፡9-14/
ነቢዩ ኤልያስም በጾም ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሯል፡፡ /1ኛ. መጽ. ነገ. 17፡2/
9.በጾም ልመናችን ይፈጸማል፡፡
እስራኤል በጾም የለመኑትን አግኝተዋል፡፡ /1ኛ ሳሙ. 7፡6-14/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ልመናቸው ተፈጽሞላቸዋል፡፡
የጾም ጥቅሞች ከላይ ከ1-9 ተራ ቊጥር የተገለጹ ሲሆን ከላይ በርእሱ እንደተገለጸው ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት ሲሆን በአንጻሩ አለመጾም ደግሞ የኃጢአት ሁሉ መሠረት ነው፡፡ ምክንያቱም ሰው ካልጾመ ለብዙ ኃጢአት ይጋለጣል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰዎች የተሰጠው የጾም ትእዛዝ ነው፡፡ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን፡- ይህን ዕፀ በለስ አትብሉ ሲል ከዕፀ በለሱ ተከልከሉ ጹሙ ማለቱ ነው፡፡ እነርሱ ግን አትብሉ የተባሉትን በሉ ከገነት ወጡ ተጎዱ አለመጾም ያስጎዳል፡፡ በዚህ መሠረት ኃጢአት በመብል ምክንያት ወደዓለም ገባ፡፡

4ኛ/ በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጾም፡- ከትርጉሙ እንደተረዳነው ከእህል ከውኃ ከመከልከሉ ጋር ከክፉ ነገር ከኃጢአት መራቅ ስለሆነ ጾማችን ከክፉ ነገር በመራቅ፣ በቅን ልቡና፣ በንጹሕ ልብ መሆን አለበት፡፡ እንዲሁም ነቢዩ ኢሳይያስ “በምትጾምበት ጊዜ እንጀራህን ለተራበ ብትቆርስ ብርሃንህ እንደንጋት ይበራል የዚያን ጊዜ ትጠራለህ እግዚአብሔርም ይሰማሃል ትጮሀለህ እርሱም እነሆ ይልሃል” /ኢሳ. 58፡6-9/ ባለው መሠረት በጾም ጊዜ የጧት ቁርሳችን ለድሆች ከተሰጠ ሰማያዊ ዋጋ እናገኛለን፡፡

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13232

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram and Signal Havens for Right-Wing Extremists

Since the violent storming of Capitol Hill and subsequent ban of former U.S. President Donald Trump from Facebook and Twitter, the removal of Parler from Amazon’s servers, and the de-platforming of incendiary right-wing content, messaging services Telegram and Signal have seen a deluge of new users. In January alone, Telegram reported 90 million new accounts. Its founder, Pavel Durov, described this as “the largest digital migration in human history.” Signal reportedly doubled its user base to 40 million people and became the most downloaded app in 70 countries. The two services rely on encryption to protect the privacy of user communication, which has made them popular with protesters seeking to conceal their identities against repressive governments in places like Belarus, Hong Kong, and Iran. But the same encryption technology has also made them a favored communication tool for criminals and terrorist groups, including al Qaeda and the Islamic State.

Pinterest (PINS) Stock Sinks As Market Gains

Pinterest (PINS) closed at $71.75 in the latest trading session, marking a -0.18% move from the prior day. This change lagged the S&P 500's daily gain of 0.1%. Meanwhile, the Dow gained 0.9%, and the Nasdaq, a tech-heavy index, lost 0.59%. Heading into today, shares of the digital pinboard and shopping tool company had lost 17.41% over the past month, lagging the Computer and Technology sector's loss of 5.38% and the S&P 500's gain of 0.71% in that time. Investors will be hoping for strength from PINS as it approaches its next earnings release. The company is expected to report EPS of $0.07, up 170% from the prior-year quarter. Our most recent consensus estimate is calling for quarterly revenue of $467.87 million, up 72.05% from the year-ago period.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from it


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA