እኔ እና አንተ.......
በዘመን በቅለን ከአንድ ውሃ ፈልቀን፣
በአንዲት ጨረቃ በፀሀይ ምለን፣
እንዳንለያይ ቃል የተጋባን፣
ዘመን ያፈራን አንድ አይነት ነበርን ፤
እኔ እና አንተ
እንደ ውቅያኖስ ሰፍተን የጠለቅን፣
እንደ ክዋክብት ከእልፍ የበዛን፣
እንደ አሸዋ ከቁጥር የላቅን፣
በአንድ ወቅት የነበርን አበቦች ነበርን፣
እኔ እና አንተ
በመኖራችን የተኗኗርን፣
በደስታችን ሀሴት ያደረግን፣
የተለያየን አንድ አይነት ነበርን፣
እኔ እና አንተ
የአለምን ውበት ጠልቀን የቀመስን፣
የነፍስ እስትንፋስ አብረን እፍ ያልን ፣
ከእውነት ጋራ በክንፍ የበረርን፣
ዘመን ያፈራን ውብ ፍሬ ነበርን።
ግን
እኔ እና አንተ አንድ አይነት እንጅ አንድ ስላልሆንን፣
ተሰበረና እህል ውሃችን፣
ደፈረሰብን ባንድ ያፈለቀን ንፁህ ውሃችን፣
ብርሀን ነፈገች ያማማለችን ውብ ጨረቃችን፣
ጥልቁ አሰመጠን ውቅያኖሳችን፤
ድንገት ጠፉብን ክዋክብቶቻችን፣
ጠወለጉብን አበቦቻችን፣
መደሰታችን ለሀዘን ሆነብን፣
ተለያየና እህል ውሃችን፣
ተበታተንን አንድ አይነት እንጅ አንድ ስላልሆንን ።😉
✍bee
በዘመን በቅለን ከአንድ ውሃ ፈልቀን፣
በአንዲት ጨረቃ በፀሀይ ምለን፣
እንዳንለያይ ቃል የተጋባን፣
ዘመን ያፈራን አንድ አይነት ነበርን ፤
እኔ እና አንተ
እንደ ውቅያኖስ ሰፍተን የጠለቅን፣
እንደ ክዋክብት ከእልፍ የበዛን፣
እንደ አሸዋ ከቁጥር የላቅን፣
በአንድ ወቅት የነበርን አበቦች ነበርን፣
እኔ እና አንተ
በመኖራችን የተኗኗርን፣
በደስታችን ሀሴት ያደረግን፣
የተለያየን አንድ አይነት ነበርን፣
እኔ እና አንተ
የአለምን ውበት ጠልቀን የቀመስን፣
የነፍስ እስትንፋስ አብረን እፍ ያልን ፣
ከእውነት ጋራ በክንፍ የበረርን፣
ዘመን ያፈራን ውብ ፍሬ ነበርን።
ግን
እኔ እና አንተ አንድ አይነት እንጅ አንድ ስላልሆንን፣
ተሰበረና እህል ውሃችን፣
ደፈረሰብን ባንድ ያፈለቀን ንፁህ ውሃችን፣
ብርሀን ነፈገች ያማማለችን ውብ ጨረቃችን፣
ጥልቁ አሰመጠን ውቅያኖሳችን፤
ድንገት ጠፉብን ክዋክብቶቻችን፣
ጠወለጉብን አበቦቻችን፣
መደሰታችን ለሀዘን ሆነብን፣
ተለያየና እህል ውሃችን፣
ተበታተንን አንድ አይነት እንጅ አንድ ስላልሆንን ።😉
✍bee
የእኔ ታሪክ ምዕራፍ -2
ክፍል -12
ቪ እባክሽ እሽ በይኝ .....አትወጅኝም እንዴ አሌፍ እንደተንበረከከ መለመኑን ቀጥሏል። ቪቪያን በእሽ እና እምቢ ውስጥ ግራ ገብቷት ቆማለች። በአባቷ እና በአሌፍ መሃል .....ድንገት አብራው መሆን እንደምትችል የነገራት ትዝ አላት........ እና ልትናገር ከንፈሮቿን ማንቀሳቀስ ስትጀምር ....እ....ማቲ መጥቶ አቋረጣቸው። ቪቪ አባባ አሌፍ ካልመጣ አላወራም ብሏል በጣም እየደከመ ነው እባክሽ እንፍጠን ስለምታወሩት ነገር በኋላ አውሩ አላት ፍጥን ፍጥን እያለ። አሌፍ ተነስ እንሂድ አለችው ከተንበረከከበት እጁን ጎትታ እያስነሳችው። (አሌፍ በዛ ቅፅበት ማቲያስን ጠላው።) ሶስቱም ተያይዘው ወደ ሆስፒታል ጉዞ ጀመሩ።
ሆስፒታል ሲደርሱ አሌፍ ብቻ ወደውስጥ ገብቶ ሌሎቹ ውጭ ጠበቁት። አባባ ደህና ኖት አለ የፊቱ መገርጣት እያስደነገጠው። ደ......ደህና ነኝ ልጄ... ለ ...ምን ነበር ልታናግረኝ የፈለግከው? ኧረ እሱ ቀስ ብሎ ይደርሳል መጀመሪያ ጤና ይበልጣልኮ
ልጄ ለሽማግሌ ነገ የሚባል ጊዜ የለውም አሁን ን...ገረኝ የሕዝቅኤል ድምፅ ቁርጥ ቁርጥ ይላል። እ ስለ ቪቪያን እና ስለ እኔ ላናግርክ ነበር ። ብዙ አሳሳቢ አይደለም ቀስ ብሎ ይደርሳል አለ አንገቱን እያቀረቀረ። እምምምም እስኪ ለ እናትህ ደውልና አገናኘኝ አለ ሕዝቅኤል ውስጡ እየተጨነቀ። አሌፍ የሕዝቅኤል ሁኔታ ግራ ቢያጋባውም መጥፎ ነገር እንደማያደርግ በሙሉ ልቡ ስለሚያምነው እና ከምንም በላይ ስለሚያከብረው እሽ ብሎ ያዘዘውን አደረገ። ራቢያ አሶስት ጥሪ በኋላ ስልኩን አነሳችው ።እማየ አላት እንደሁሌው ሰሚሬ እንዴት ዋልክ ልጄ ዛሬ ሳናወራ ዋልንኮ ደህና ነህ አለች በስስት አነጋገር። ደህና ነኝ እማ ትንሽ ስላልተመቸኝ ነው የ ቪቪያን አባት ሊያናግርሽ ይፈልጋል አዋሪው ብሎ ስልኩን ሰጣው። ራቢያ ሰውየውን ባታውቀውም ደነገጠች እሷም የቪቪያንን እና የ ልጇን አንድ ላይ መሆን አጥብቀው ከሚቃወሙት ውስጥ ናት። ሰውየው ምን ሊለኝ ይሆን አለች በውስጧ። ሰ...ሰላም ለ አንቺ....አለ ሕዝቅኤል የልብ ምቱ እየፈጠነ። ራቢያ በቁሟ ደረቀች። ሔሎ ሔሎ...ራ .....ሊጨርሰው አለና መልሶ ዋጠው። ሕዝቄ......በህይወት አለህ? እንባ ተናነቃት..... እንደምንም ራሷን እየታገለች.....አንተ ነህ ሕዝቄ.....እውነት አንተ ነህ? አወ እኔ ነኝ ደህና እንደሆንሽ ተስፋ አደርጋለሁ። "ልጆቻችንም ሊጋቡ ነው እንኳን ደስ አለሽ ወይዘሮ ራቢያ" ቅስሙ ስብር ብሎ ነበር ይሄንን የተናገራት ምን ለማለት እንደፈለገ በደምብ ገብቷታል። የእርሷም ውስጥ ስብር አለ .... ምናለ ያኔ ባስተዋውቀው ኖሮ ወይ ራቢያ በቃ ችግር አያጣሽም አይደል ወይ ጣጣ ቻው አቶ ሕዝቅኤል ብላ ስልኩን ዘጋች።
ለስንት አመታት ሙሉ ድምፁን ያጠፋው ሕዝቅኤልን ከብዙ ጊዜ ጥበቃ እና ሀዘን በኋላ እንደሞተ ደምድማ ሀዘኗን አምና ተቀብላው ነበር። ድንገት ግን ሕዝቅኤል መጣ ያውም የሴት ልጅ አባት ሆኖ ለዛውም ደሞ ልጆቻቸው ጭራሽ ሊጋቡ ነው። ራቢያ ራሷን መቆጣጠር አቅቷት ወንበሩን ተደግፋ ማልቀስ ጀመረች። ለምን ? ለምን ይሄ ሁሉ.......
ትተዋወቃላችሁ እንዴ አለ አሌፍ ንግግራቸው ገርሞት .....አወ አሁን አወቅኳት ልጆች እያለን አንድ ላይ ነበር የተማርነው በጣም ጎበዝ ነበረች ይገርምሃል አለው። አሌፍ ግን ደስ የማይል ስሜት ተሰማው እናቱ ከዚህ በላይ ትልቅ ደረጃ መድረስ የምትችል ጠንካራ ሴት እንደሆነች ያውቃል......ባትወልድ ኖሮ!!!!
ሕዝቅኤል ሊሞት እንደሆነ እየተሰማው ስለሆነ ምንም ጊዜ ማጥፋት አልፈለገም።ከዚህ በኋላ ዝም በማለት የማሳልፈው ጊዜ የለኝም አለ በውስጡ።
አሌፍ አባትህ ግን ስለ አንተ ምንም ነገር ነግሮህ አያውቅም?
አልገባኝም ምን አይነት ነገር አለ ግራ እየተጋባ .....
ታሪካቸውን አባትህ እና እናትህ እንዴት እንደተገናኙ አንተ እንዴት እንደ ተወለድክ ?
አይ አባቴ ለዛ ጊዜ አልነበረውም ባይሆን እናቴ ግን ነግራኛለች። አለ...
እንዴት ነበር የተወለድከው?
ይቀጥላል............
@nibab_lehiwot
ክፍል -12
ቪ እባክሽ እሽ በይኝ .....አትወጅኝም እንዴ አሌፍ እንደተንበረከከ መለመኑን ቀጥሏል። ቪቪያን በእሽ እና እምቢ ውስጥ ግራ ገብቷት ቆማለች። በአባቷ እና በአሌፍ መሃል .....ድንገት አብራው መሆን እንደምትችል የነገራት ትዝ አላት........ እና ልትናገር ከንፈሮቿን ማንቀሳቀስ ስትጀምር ....እ....ማቲ መጥቶ አቋረጣቸው። ቪቪ አባባ አሌፍ ካልመጣ አላወራም ብሏል በጣም እየደከመ ነው እባክሽ እንፍጠን ስለምታወሩት ነገር በኋላ አውሩ አላት ፍጥን ፍጥን እያለ። አሌፍ ተነስ እንሂድ አለችው ከተንበረከከበት እጁን ጎትታ እያስነሳችው። (አሌፍ በዛ ቅፅበት ማቲያስን ጠላው።) ሶስቱም ተያይዘው ወደ ሆስፒታል ጉዞ ጀመሩ።
ሆስፒታል ሲደርሱ አሌፍ ብቻ ወደውስጥ ገብቶ ሌሎቹ ውጭ ጠበቁት። አባባ ደህና ኖት አለ የፊቱ መገርጣት እያስደነገጠው። ደ......ደህና ነኝ ልጄ... ለ ...ምን ነበር ልታናግረኝ የፈለግከው? ኧረ እሱ ቀስ ብሎ ይደርሳል መጀመሪያ ጤና ይበልጣልኮ
ልጄ ለሽማግሌ ነገ የሚባል ጊዜ የለውም አሁን ን...ገረኝ የሕዝቅኤል ድምፅ ቁርጥ ቁርጥ ይላል። እ ስለ ቪቪያን እና ስለ እኔ ላናግርክ ነበር ። ብዙ አሳሳቢ አይደለም ቀስ ብሎ ይደርሳል አለ አንገቱን እያቀረቀረ። እምምምም እስኪ ለ እናትህ ደውልና አገናኘኝ አለ ሕዝቅኤል ውስጡ እየተጨነቀ። አሌፍ የሕዝቅኤል ሁኔታ ግራ ቢያጋባውም መጥፎ ነገር እንደማያደርግ በሙሉ ልቡ ስለሚያምነው እና ከምንም በላይ ስለሚያከብረው እሽ ብሎ ያዘዘውን አደረገ። ራቢያ አሶስት ጥሪ በኋላ ስልኩን አነሳችው ።እማየ አላት እንደሁሌው ሰሚሬ እንዴት ዋልክ ልጄ ዛሬ ሳናወራ ዋልንኮ ደህና ነህ አለች በስስት አነጋገር። ደህና ነኝ እማ ትንሽ ስላልተመቸኝ ነው የ ቪቪያን አባት ሊያናግርሽ ይፈልጋል አዋሪው ብሎ ስልኩን ሰጣው። ራቢያ ሰውየውን ባታውቀውም ደነገጠች እሷም የቪቪያንን እና የ ልጇን አንድ ላይ መሆን አጥብቀው ከሚቃወሙት ውስጥ ናት። ሰውየው ምን ሊለኝ ይሆን አለች በውስጧ። ሰ...ሰላም ለ አንቺ....አለ ሕዝቅኤል የልብ ምቱ እየፈጠነ። ራቢያ በቁሟ ደረቀች። ሔሎ ሔሎ...ራ .....ሊጨርሰው አለና መልሶ ዋጠው። ሕዝቄ......በህይወት አለህ? እንባ ተናነቃት..... እንደምንም ራሷን እየታገለች.....አንተ ነህ ሕዝቄ.....እውነት አንተ ነህ? አወ እኔ ነኝ ደህና እንደሆንሽ ተስፋ አደርጋለሁ። "ልጆቻችንም ሊጋቡ ነው እንኳን ደስ አለሽ ወይዘሮ ራቢያ" ቅስሙ ስብር ብሎ ነበር ይሄንን የተናገራት ምን ለማለት እንደፈለገ በደምብ ገብቷታል። የእርሷም ውስጥ ስብር አለ .... ምናለ ያኔ ባስተዋውቀው ኖሮ ወይ ራቢያ በቃ ችግር አያጣሽም አይደል ወይ ጣጣ ቻው አቶ ሕዝቅኤል ብላ ስልኩን ዘጋች።
ለስንት አመታት ሙሉ ድምፁን ያጠፋው ሕዝቅኤልን ከብዙ ጊዜ ጥበቃ እና ሀዘን በኋላ እንደሞተ ደምድማ ሀዘኗን አምና ተቀብላው ነበር። ድንገት ግን ሕዝቅኤል መጣ ያውም የሴት ልጅ አባት ሆኖ ለዛውም ደሞ ልጆቻቸው ጭራሽ ሊጋቡ ነው። ራቢያ ራሷን መቆጣጠር አቅቷት ወንበሩን ተደግፋ ማልቀስ ጀመረች። ለምን ? ለምን ይሄ ሁሉ.......
ትተዋወቃላችሁ እንዴ አለ አሌፍ ንግግራቸው ገርሞት .....አወ አሁን አወቅኳት ልጆች እያለን አንድ ላይ ነበር የተማርነው በጣም ጎበዝ ነበረች ይገርምሃል አለው። አሌፍ ግን ደስ የማይል ስሜት ተሰማው እናቱ ከዚህ በላይ ትልቅ ደረጃ መድረስ የምትችል ጠንካራ ሴት እንደሆነች ያውቃል......ባትወልድ ኖሮ!!!!
ሕዝቅኤል ሊሞት እንደሆነ እየተሰማው ስለሆነ ምንም ጊዜ ማጥፋት አልፈለገም።ከዚህ በኋላ ዝም በማለት የማሳልፈው ጊዜ የለኝም አለ በውስጡ።
አሌፍ አባትህ ግን ስለ አንተ ምንም ነገር ነግሮህ አያውቅም?
አልገባኝም ምን አይነት ነገር አለ ግራ እየተጋባ .....
ታሪካቸውን አባትህ እና እናትህ እንዴት እንደተገናኙ አንተ እንዴት እንደ ተወለድክ ?
አይ አባቴ ለዛ ጊዜ አልነበረውም ባይሆን እናቴ ግን ነግራኛለች። አለ...
እንዴት ነበር የተወለድከው?
ይቀጥላል............
@nibab_lehiwot
ጌታ ምን ላድርግልህ ቢለኝ ልቤን አሳይልኝ ነበር የምለው ልቤ ውስጥ ብገልጠው ያመኛል ብዬ የሸሸግኩት እልፍ ደብዳቤ ነበረ
ጌታዬ ሌላ ምን ላድርግልህ ቢለኝ ተንበርክኬ እሷን ስለሰጠኸኝ አመሰግናለሁ ያልኩትን የምስጋና ፀሎት አሳይልኝ እለው ነበር
አሁንም ሌላ ምን ላድርግልህ ቢለኝ እሷ ያልነበረች ግዜ አረማመዴን እና ልቤ ውስጥ የተንከላወሰውን ሃሳብ አሳይልኝ እለው ነበር
እሱ ግን ምን ላደርግልህ ብሎ አይጠይቀኝም ...እኔ አድርግልኝ ብዬ ልጠይቀው ሳሰፈስፍ ስጣደፍ
ልጃቸው ሊሞትባቸው አኑርልኝ የሚሉ ፀላይ፣ ልጄ ሳያድግ አትግደለኝ የሚል አባት ፀሎት ፣ ፍትህ የሚሹ ብዚ ነብሶች ፣ ርሃብ ጠፍሮ ይዟቸው አንድ ጉርሻ ብትቸረኝ የሚሉትን
እውነታቸውን በገነዘብ የተቀሙ እልፍ ደካሞችንአምላክን በተማፅኖ የሚኖሩትን ሰዎች ወረፋ አስቀድማቸዋለሁ
የኔ ጥያቄ ቅንጦት ይሆን? እላለሁ
ምን አልባት ልባችን ላይ ያለው መሻት ቢመዘን እኩል ይሆን? ይሆናል ማን ያውቃል ?
የኔ ጥያቄ ከሌላው ጋር ሲስተያይ ቅንጦት ይመስለኛል ብዬ አስብና መሻቴን ገታለሁ🙃
✍Miraዥ
ጌታዬ ሌላ ምን ላድርግልህ ቢለኝ ተንበርክኬ እሷን ስለሰጠኸኝ አመሰግናለሁ ያልኩትን የምስጋና ፀሎት አሳይልኝ እለው ነበር
አሁንም ሌላ ምን ላድርግልህ ቢለኝ እሷ ያልነበረች ግዜ አረማመዴን እና ልቤ ውስጥ የተንከላወሰውን ሃሳብ አሳይልኝ እለው ነበር
እሱ ግን ምን ላደርግልህ ብሎ አይጠይቀኝም ...እኔ አድርግልኝ ብዬ ልጠይቀው ሳሰፈስፍ ስጣደፍ
ልጃቸው ሊሞትባቸው አኑርልኝ የሚሉ ፀላይ፣ ልጄ ሳያድግ አትግደለኝ የሚል አባት ፀሎት ፣ ፍትህ የሚሹ ብዚ ነብሶች ፣ ርሃብ ጠፍሮ ይዟቸው አንድ ጉርሻ ብትቸረኝ የሚሉትን
እውነታቸውን በገነዘብ የተቀሙ እልፍ ደካሞችንአምላክን በተማፅኖ የሚኖሩትን ሰዎች ወረፋ አስቀድማቸዋለሁ
የኔ ጥያቄ ቅንጦት ይሆን? እላለሁ
ምን አልባት ልባችን ላይ ያለው መሻት ቢመዘን እኩል ይሆን? ይሆናል ማን ያውቃል ?
የኔ ጥያቄ ከሌላው ጋር ሲስተያይ ቅንጦት ይመስለኛል ብዬ አስብና መሻቴን ገታለሁ🙃
✍Miraዥ
የእኔ ታሪክ (ምዕራፍ-2)
ክፍል-14
አወ እኔ ነኝ የራቢያ የድሮ ፍቅረኛ የአንተም አባት .....
ማለት አልገባኝም አባባ በሽታው ነው ወይስ በትክክል ጤነኛ ኖት ? አሌፍ ግራ ገብቶታል...የሚይዝ የሚጨብጠውን አጣ ....በዛ ሰዓት ውሸቱን እንደሆነ ማመን ብቻ ነበር የፈለገው ወደ ራቢያ በድጋሚ ደወለ...... ራቢያ ፈራችው የሆነ ነገር እንደተፈጠረ ልቧ ነግሯታል .......ልጄ.. አለች ፈራ ተባ እያለች
እማዬ አባቴ ማን ነው ???? ቀጥተኛ መልስ ነው ምፈልገው ምንም እንዳታስተባብይ....ቶሎ በይ.....ራቢያ በቁሟ ራደች። እ...ቆይ አንዴ..... እሱ......እማዬ ዝም በይ!!!! አሌፍ በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ጮኸባት። አባቴ አቶ ሕዝቅኤል ነው አይደለ??? መልሽልኝ እንጅ አወ ወይም አይደለም በይኝ ወላሒ ለአዚም ካልሆነ ደግመሽ አይኔን አታይው!! የአሌፍ ጩኸት ሕዝቅኤልን ራሱ በትንሹ አስፈራው። ራቢያ አማራጭ ስላልነበራት "አወ" አለች። ረጋ ባለ ድምፅ አሌፍ የሚያደርገውን አጣ.....እማየ አሁንስ አንቺን መቋቋም በቃኝ!! አልቻልኩም ስልኩን ጆሮዋ ላይ ዘግቶ የወንድ ልጅ እንባ መታየት የለበትም የሚለውን አባባል እዛው ሻረው። ሕዝቅኤል ለማፅናናት እጁን ሰደደ። እንዳትነካኝ!!! እሱም ላይ ጮኸ እኔ አንድ አባት ብቻ ነው ያለኝ እሱም ሞቷል በቃ!! ማናችሁንም አልፈልግም አላምናችሁም ሁላችሁም ውሸታሞች ናችሁ.....አሌፍ ብሶቱን አንድ ላይ ዘረገፈው።
ቪቪያን ሲጯጯሁ በመስኮት በኩል ስታያቸው ስለነበረ በሩን ከፍታው ገባች። አሌፍ እያለቀሰ ነበር....ምንድን ነው አሌፍ አለች አንዴ አባቷን አንዴ እሱን እየተመለከተች።
ሕዝቅኤል በደከመ ድምፁ ሊያፅናናው ቢሞክርም አሌፍ ጭራሽ መረጋጋት እየተሳነው መጣ ። ቪቪያን ወደሱ ስትጠጋ እንዳትነኪኝ እህቴ እያለ ሳቅ እና ለቅሶ ባዘለ ድምፅ ጮኸ!!!
ምንድን ነው አባዬ ቪቪያን አፈጠጠችበት። በቃችሁ ዝም በሉ!!! ሕዝቅኤልም የቁጣ ጩኸቱን ለቀቀው ።(ሜሮን እና ኤልሳ ከውጭ ዶክተሮች እንዳይመጡ እየተጠባበቁ ነው። ማቲያስ ደግሞ ያልታወቀ ስልክ ተደውሎለት ሊያናግር እንደወጣ አልተመለሰም)
በሕዝቅኤል ቁጣ ክፍሉ ፀጥ አለ ያሁሉ ጩኸት በአንድ ጊዜ ጠፋ። ተቀመጡ ሁለታችሁም .....ቪቪያን እና አሌፍ የታዘዙትን አደረጉ። አንቺ ዝም በይ ምንም ድምፅ አልፈልግም። አንተ ደሞ ሙሉ ታሪክህን ስማና የምታደርገውን ታደርጋለህ....ትልቅ ሰው ነህ ከምንም ነገር ከልክየ አላድንህም። ከቁጣው የተነሳ ብቻ ሳይሆን ሊናገር ያሰበውን ነገር ቀድሞ የታወቃት ይመስል የቪቪያን እጆች መንቀጥቀጥ ጀምረዋል።
ሕዝቅኤል ለቪቪያን የነገራትን ሙሉ ታሪክ ለ አሌፍ አንድ በአንድ ነገረው። አወ በንግግሩ ቪቪያን አሌፍ ወንድሟ እንደሆነ አወቀች። ልቧ ስብርብር አለ፣ ክንፏን እንደተመታች ወፍ እዛው ባለችበት ተልፈሰፈሰች። እንደዛ ልታገኘው ስትጓጓለት የነበረችው ወንድሟ፣ እንደዛ አቅፎ እንደ ታናሽ እህቱ ፀጉሯን እንዲነካካት የምትመኘው ሰው የምታፈቅረው አሌፍ ነው። ገና ዛሬ ወንድሜ ባይሆንስ ለዘለዓለም ሳላገኘው ብቀር ብላ ተመኘች።
አሌፍ ሙሉ ታሪኩን ከሰማ በኋላ ምን አደረግን? ቆይ በምን ጥፋታችን ነው እንደዚህ የምታሰቃዩን? ምን አይነት ህይወት ነው የሰጣችሁን?? እህቴን እንዳፈቅር ኧረ ጭራሽ ባላውቅማ አግብቻት እንድኖር? ለምን???አሌፍ ከልቡ አምርሮ ሕዝቅኤልን መናገር ጀመረ።
ሕዝቅኤል እስኪጨርስ ዝም አለው። ቪቪያን ተናገሪ እንጅ ለምን ዝም ትያለሽ እያለ በእጁ ይገፋፋታል።ፈርተሽ ነው? የአሌፍ እንባ እንደ ጎርፍ ይወርዳል። ቪቪያን ግን ደንዝዛለች አትናገርም፣ አታለቅስም፣ ፀጥ ፍዝዝ፣ ብቻ።
ለ እኛስ ቀላል ነው? ብለህ ታስባለህ ኧ እስኪ ራቢያን ተመልከታት። ለ አንተ ብላ አይደለም በጊዜው የማትወደውን ሰው ያገባችው? ኧ አንተን ማስወጣት እና በሰላም ከቤተሰቧ ጋር መኖር አቅቷት ይመስልሃል? መልስልኝ?? አየህ ከክብሯ ፣ ከቤተሰቧ፣ ከማህበረሰቡ አንተን ስላስበለጠች እንጅ እንደ አንድ ተራ ሰው በ 2 እና 3 ሺ ብር አሽቀንጥራ ጥላህ እስካሁን ህልሟን አሳክታ እየኖረች ነበር። ይሄን እንዴት ማሰብ ያቅትሃል ስቃይዋ አይታይህም? ላንተ ስትል የተሸከመችው መከራ አይታይህም ወይ? ልታዝንላት ነበርኮ የሚገባው ....ምን ልትል እንዳሰብክ ይገባኛል" እኔ ፈልጌ አልመጣሁም" ልትል ነው አይደለ እንግዲያውስ እኔም ልንገርህ እኛም ፈልገን አልነበረም ያመጣንህ ድንገት ሳናስበው በተሰራ የአንድ ቀን ስህተት ነበር። ራቢያኮ አንተን ለመግደል ብዙ ምክኒያቶች ነበሯት። ጭራሽ እንደተፈጠርክ ለ እኔ ሳትነግረኝ ብቻዋን ስቃዩን ተሸከመችው። ለ አንተ ብቻ ሳይሆን እንደነገርኩህ ለ እኔም ታስብ ነበር። እስኪ አንድ ቀን በአንተ መወለድ ስታማርር ሰምተሃት ታውቃለህ? ወደኋላ ጎተትከኝ ብላህ ታውቃለች?? ሳትፈለግ የመጣህ ስህተት ....ብላህ ታውቃለች ወይ ንገረኝ?
አሌፍ አንገቱን ደፍቶ ፀጥ አለ።(ራቢያ ለ 50ኛ ጊዜ እየደወለች ነው።)
ታዲያ እኔስ አላሳዝንም ይሄ ሁሉ ሚስጥር ተደብቆብኝ ኖርኩ። ጭራሽ እህቴን አፈቀርኳት ከዛ ድንገት መጥታችሁ እህትህ ነች አላችሁኝ። ከዛስ....ቆይ አግብቻትስ ቢሆን...
ለሱ ነውኮ ፈጣሪን አመስግን የምልህ ቢያንስ የእኛን ታሪክ አልደገማችሁም። ለበጎ ነው ያገናኛችሁ ብለህ ተቀበል። አሌፍ ልጄ ከልጅነትህ ጀምሮ ባውቅህ እና ብንከባከብህ ምንኛ ደስ ባለኝ ነበር።ግን አልተፈቀደልንም ምን ማድረግ እንችል ነበር ሁላችንም የራሳችን ሕመም አለብን።
ይሔንን ሁሉ ለአሌፍ ሲያወራ ቪቪያንን ረስቷት ነበር። ወደሷ ዞሮ እርግብ ነይ ወደዚህ አላት ደመነፍሷን ሔዳ ታቀፈችው።
አሌፍም ተነስቶ ሔዶ ታቀፈው። ሕዝቅኤል በጣም ደነገጠ፣ ደስታም ተጨመረበት። እንደዚህ ይፈጠራል ብሎ በጭራስ አስቦት አያውቅም ነበር። ሁለቱን ልጆቹን በቀኝ እና በግራው አቅፎ የደስታ እንባን አነባ። ከብዙ አመታት በኋላ የተጣላውን ፈጣሪውን ቀና ብሎ በእንባ አይኑ አመሰገነው። ልጆቼ እርስ በርስ ተጠባበቁ። አለ በየተራ ግንባራቸውን እየሳመ።ከዚያም አይኖቹንም ሸፈነ። ያቀፏቸው እጆች ከትከሻቸው ሲንሸራተቱ ቪቪያን እና አሌፍ ቀና አሉ።
ይቀጥል ይሆናል........
@nibab_lehiwot
ክፍል-14
አወ እኔ ነኝ የራቢያ የድሮ ፍቅረኛ የአንተም አባት .....
ማለት አልገባኝም አባባ በሽታው ነው ወይስ በትክክል ጤነኛ ኖት ? አሌፍ ግራ ገብቶታል...የሚይዝ የሚጨብጠውን አጣ ....በዛ ሰዓት ውሸቱን እንደሆነ ማመን ብቻ ነበር የፈለገው ወደ ራቢያ በድጋሚ ደወለ...... ራቢያ ፈራችው የሆነ ነገር እንደተፈጠረ ልቧ ነግሯታል .......ልጄ.. አለች ፈራ ተባ እያለች
እማዬ አባቴ ማን ነው ???? ቀጥተኛ መልስ ነው ምፈልገው ምንም እንዳታስተባብይ....ቶሎ በይ.....ራቢያ በቁሟ ራደች። እ...ቆይ አንዴ..... እሱ......እማዬ ዝም በይ!!!! አሌፍ በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ጮኸባት። አባቴ አቶ ሕዝቅኤል ነው አይደለ??? መልሽልኝ እንጅ አወ ወይም አይደለም በይኝ ወላሒ ለአዚም ካልሆነ ደግመሽ አይኔን አታይው!! የአሌፍ ጩኸት ሕዝቅኤልን ራሱ በትንሹ አስፈራው። ራቢያ አማራጭ ስላልነበራት "አወ" አለች። ረጋ ባለ ድምፅ አሌፍ የሚያደርገውን አጣ.....እማየ አሁንስ አንቺን መቋቋም በቃኝ!! አልቻልኩም ስልኩን ጆሮዋ ላይ ዘግቶ የወንድ ልጅ እንባ መታየት የለበትም የሚለውን አባባል እዛው ሻረው። ሕዝቅኤል ለማፅናናት እጁን ሰደደ። እንዳትነካኝ!!! እሱም ላይ ጮኸ እኔ አንድ አባት ብቻ ነው ያለኝ እሱም ሞቷል በቃ!! ማናችሁንም አልፈልግም አላምናችሁም ሁላችሁም ውሸታሞች ናችሁ.....አሌፍ ብሶቱን አንድ ላይ ዘረገፈው።
ቪቪያን ሲጯጯሁ በመስኮት በኩል ስታያቸው ስለነበረ በሩን ከፍታው ገባች። አሌፍ እያለቀሰ ነበር....ምንድን ነው አሌፍ አለች አንዴ አባቷን አንዴ እሱን እየተመለከተች።
ሕዝቅኤል በደከመ ድምፁ ሊያፅናናው ቢሞክርም አሌፍ ጭራሽ መረጋጋት እየተሳነው መጣ ። ቪቪያን ወደሱ ስትጠጋ እንዳትነኪኝ እህቴ እያለ ሳቅ እና ለቅሶ ባዘለ ድምፅ ጮኸ!!!
ምንድን ነው አባዬ ቪቪያን አፈጠጠችበት። በቃችሁ ዝም በሉ!!! ሕዝቅኤልም የቁጣ ጩኸቱን ለቀቀው ።(ሜሮን እና ኤልሳ ከውጭ ዶክተሮች እንዳይመጡ እየተጠባበቁ ነው። ማቲያስ ደግሞ ያልታወቀ ስልክ ተደውሎለት ሊያናግር እንደወጣ አልተመለሰም)
በሕዝቅኤል ቁጣ ክፍሉ ፀጥ አለ ያሁሉ ጩኸት በአንድ ጊዜ ጠፋ። ተቀመጡ ሁለታችሁም .....ቪቪያን እና አሌፍ የታዘዙትን አደረጉ። አንቺ ዝም በይ ምንም ድምፅ አልፈልግም። አንተ ደሞ ሙሉ ታሪክህን ስማና የምታደርገውን ታደርጋለህ....ትልቅ ሰው ነህ ከምንም ነገር ከልክየ አላድንህም። ከቁጣው የተነሳ ብቻ ሳይሆን ሊናገር ያሰበውን ነገር ቀድሞ የታወቃት ይመስል የቪቪያን እጆች መንቀጥቀጥ ጀምረዋል።
ሕዝቅኤል ለቪቪያን የነገራትን ሙሉ ታሪክ ለ አሌፍ አንድ በአንድ ነገረው። አወ በንግግሩ ቪቪያን አሌፍ ወንድሟ እንደሆነ አወቀች። ልቧ ስብርብር አለ፣ ክንፏን እንደተመታች ወፍ እዛው ባለችበት ተልፈሰፈሰች። እንደዛ ልታገኘው ስትጓጓለት የነበረችው ወንድሟ፣ እንደዛ አቅፎ እንደ ታናሽ እህቱ ፀጉሯን እንዲነካካት የምትመኘው ሰው የምታፈቅረው አሌፍ ነው። ገና ዛሬ ወንድሜ ባይሆንስ ለዘለዓለም ሳላገኘው ብቀር ብላ ተመኘች።
አሌፍ ሙሉ ታሪኩን ከሰማ በኋላ ምን አደረግን? ቆይ በምን ጥፋታችን ነው እንደዚህ የምታሰቃዩን? ምን አይነት ህይወት ነው የሰጣችሁን?? እህቴን እንዳፈቅር ኧረ ጭራሽ ባላውቅማ አግብቻት እንድኖር? ለምን???አሌፍ ከልቡ አምርሮ ሕዝቅኤልን መናገር ጀመረ።
ሕዝቅኤል እስኪጨርስ ዝም አለው። ቪቪያን ተናገሪ እንጅ ለምን ዝም ትያለሽ እያለ በእጁ ይገፋፋታል።ፈርተሽ ነው? የአሌፍ እንባ እንደ ጎርፍ ይወርዳል። ቪቪያን ግን ደንዝዛለች አትናገርም፣ አታለቅስም፣ ፀጥ ፍዝዝ፣ ብቻ።
ለ እኛስ ቀላል ነው? ብለህ ታስባለህ ኧ እስኪ ራቢያን ተመልከታት። ለ አንተ ብላ አይደለም በጊዜው የማትወደውን ሰው ያገባችው? ኧ አንተን ማስወጣት እና በሰላም ከቤተሰቧ ጋር መኖር አቅቷት ይመስልሃል? መልስልኝ?? አየህ ከክብሯ ፣ ከቤተሰቧ፣ ከማህበረሰቡ አንተን ስላስበለጠች እንጅ እንደ አንድ ተራ ሰው በ 2 እና 3 ሺ ብር አሽቀንጥራ ጥላህ እስካሁን ህልሟን አሳክታ እየኖረች ነበር። ይሄን እንዴት ማሰብ ያቅትሃል ስቃይዋ አይታይህም? ላንተ ስትል የተሸከመችው መከራ አይታይህም ወይ? ልታዝንላት ነበርኮ የሚገባው ....ምን ልትል እንዳሰብክ ይገባኛል" እኔ ፈልጌ አልመጣሁም" ልትል ነው አይደለ እንግዲያውስ እኔም ልንገርህ እኛም ፈልገን አልነበረም ያመጣንህ ድንገት ሳናስበው በተሰራ የአንድ ቀን ስህተት ነበር። ራቢያኮ አንተን ለመግደል ብዙ ምክኒያቶች ነበሯት። ጭራሽ እንደተፈጠርክ ለ እኔ ሳትነግረኝ ብቻዋን ስቃዩን ተሸከመችው። ለ አንተ ብቻ ሳይሆን እንደነገርኩህ ለ እኔም ታስብ ነበር። እስኪ አንድ ቀን በአንተ መወለድ ስታማርር ሰምተሃት ታውቃለህ? ወደኋላ ጎተትከኝ ብላህ ታውቃለች?? ሳትፈለግ የመጣህ ስህተት ....ብላህ ታውቃለች ወይ ንገረኝ?
አሌፍ አንገቱን ደፍቶ ፀጥ አለ።(ራቢያ ለ 50ኛ ጊዜ እየደወለች ነው።)
ታዲያ እኔስ አላሳዝንም ይሄ ሁሉ ሚስጥር ተደብቆብኝ ኖርኩ። ጭራሽ እህቴን አፈቀርኳት ከዛ ድንገት መጥታችሁ እህትህ ነች አላችሁኝ። ከዛስ....ቆይ አግብቻትስ ቢሆን...
ለሱ ነውኮ ፈጣሪን አመስግን የምልህ ቢያንስ የእኛን ታሪክ አልደገማችሁም። ለበጎ ነው ያገናኛችሁ ብለህ ተቀበል። አሌፍ ልጄ ከልጅነትህ ጀምሮ ባውቅህ እና ብንከባከብህ ምንኛ ደስ ባለኝ ነበር።ግን አልተፈቀደልንም ምን ማድረግ እንችል ነበር ሁላችንም የራሳችን ሕመም አለብን።
ይሔንን ሁሉ ለአሌፍ ሲያወራ ቪቪያንን ረስቷት ነበር። ወደሷ ዞሮ እርግብ ነይ ወደዚህ አላት ደመነፍሷን ሔዳ ታቀፈችው።
አሌፍም ተነስቶ ሔዶ ታቀፈው። ሕዝቅኤል በጣም ደነገጠ፣ ደስታም ተጨመረበት። እንደዚህ ይፈጠራል ብሎ በጭራስ አስቦት አያውቅም ነበር። ሁለቱን ልጆቹን በቀኝ እና በግራው አቅፎ የደስታ እንባን አነባ። ከብዙ አመታት በኋላ የተጣላውን ፈጣሪውን ቀና ብሎ በእንባ አይኑ አመሰገነው። ልጆቼ እርስ በርስ ተጠባበቁ። አለ በየተራ ግንባራቸውን እየሳመ።ከዚያም አይኖቹንም ሸፈነ። ያቀፏቸው እጆች ከትከሻቸው ሲንሸራተቱ ቪቪያን እና አሌፍ ቀና አሉ።
ይቀጥል ይሆናል........
@nibab_lehiwot
"ሀይቅ ዳር ተሰብስበው እንቁራሪቶች አብዝተው ስለጮኹ ሀይቁ የ እንቁራሪቶች ነው ማለት አይደለም፤ለ ክብራቸው ሲሉ ዝም ያሉ ብዙ ዓሳዎች ሀይቁ ውስጥ አሉ!"
✍ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድሕን
✍ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድሕን
ሰላም እንዴት ቆያችሁ? በ ነገሮች መደራረብ ምክኒያት ለትንሽ ጊዜያት ምንም አይነት post አይኖርም በትዕግስት እንድትጠብቁን አደራ እላለሁ😔
ጠየቅኳት.......
ሰወች ሁል ጊዜ ይጨነቃሉ ስለነገም ያስባሉ ያዝናሉ፣አንቺ ግን ለምን ..........
በእርጋታ የተሞላ አጭር መልስ
"ለራሴ ስለምኖር".......
✍bee
ሰወች ሁል ጊዜ ይጨነቃሉ ስለነገም ያስባሉ ያዝናሉ፣አንቺ ግን ለምን ..........
በእርጋታ የተሞላ አጭር መልስ
"ለራሴ ስለምኖር".......
✍bee
የእኔ ጥያቄ....
መልስ እፈልጋለሁ.....
ፍቅር መንገድን አስትቶ በጭፍን የሚነዳ መሰናክል
ወይስ
መፅሐፍ እንደሚለው "የህይወት መዓዛ" ?
wait is love really exists🤔
መልስ እፈልጋለሁ.....
ፍቅር መንገድን አስትቶ በጭፍን የሚነዳ መሰናክል
ወይስ
መፅሐፍ እንደሚለው "የህይወት መዓዛ" ?
wait is love really exists🤔
“ሁለት እናት ወፎች ነበሩ እና አንደኛዋ ወፍ በጠዋት ተነስታ አስፓልቱ ላይ ያለውን ጥሬ በሙሉ ለቅማ ለራሷም በላች ለልጆቻም አበላች። አርፍዳ የተነሳችዋ ሌላኛዋ እናት ወፍ ግን ለሰዓታት በጽናት ብትፈልግ አንዳች ጥሬ አላገችም። ከዚህ ታሪክ ምን ትረዳላችሁ።”
ኒቼ፦ ''የመጀመርያዋ እናት ወፍ ስግብግብ መሆኗን''
ማርክስ፦ ''የሰው ልጅ በኑሮ ውድነት ምክንያት ቅንጣት ያህል ምግብ መጣል ማቆሙን።''
ሾፐንአወር፦ ''ወፍ ሆኜ አላውቅም፤ ለምን እራሷን አንጠይቃትም!''
ሲዮራን፦ ''ምትመገበው ያጣችው ወፍ በልጆቿና በጎጆዋ ውስጥ ዝማሬ የለሽ ድብርት እንደምታስተናግድ።''
አርስቶትል ፦ ''በጠዋት መነሳት የስኬት ቁልፍ እንደሆነ''
ዲዮጋን፦ ''ምግብ በቀላሉ በጎዳና ላይ እንደሚገኝ''
ሶቅራጠስ፦ ''ወፎች ጥሬ እንደሚበሉ''
እኔ:- ወፉአ ያረፈደችው አምሽታ ስለተኛች ነው::ለምን አመሸች? ሰለልጆችዋ ስታስብ::😇
እናተስ ምን ትላላችሁ🤔
✍Aiden
@nibab_lehiwot
ኒቼ፦ ''የመጀመርያዋ እናት ወፍ ስግብግብ መሆኗን''
ማርክስ፦ ''የሰው ልጅ በኑሮ ውድነት ምክንያት ቅንጣት ያህል ምግብ መጣል ማቆሙን።''
ሾፐንአወር፦ ''ወፍ ሆኜ አላውቅም፤ ለምን እራሷን አንጠይቃትም!''
ሲዮራን፦ ''ምትመገበው ያጣችው ወፍ በልጆቿና በጎጆዋ ውስጥ ዝማሬ የለሽ ድብርት እንደምታስተናግድ።''
አርስቶትል ፦ ''በጠዋት መነሳት የስኬት ቁልፍ እንደሆነ''
ዲዮጋን፦ ''ምግብ በቀላሉ በጎዳና ላይ እንደሚገኝ''
ሶቅራጠስ፦ ''ወፎች ጥሬ እንደሚበሉ''
እኔ:- ወፉአ ያረፈደችው አምሽታ ስለተኛች ነው::ለምን አመሸች? ሰለልጆችዋ ስታስብ::😇
እናተስ ምን ትላላችሁ🤔
✍Aiden
@nibab_lehiwot