Telegram Group & Telegram Channel
አንድ ሰው ብዙ ሰው ነው፡፡ ብዙ ሰው ግን አንድ ሰው ሊሆን አይችልም፡፡

የአንድ ሰው ብዙነት ከዕድሜው የሚያገኛቸው ብዝሃ ማንነቱ ነው፡፡ አንድ ሰው በልጅነቱ የልጅነት አስተሳሰብና ማንነት አለው፤ በወጣትነቱም የወጣትነቱን ሰውነትና የትኩስነት ማንነቱን ይይዛል፡፡ ያው አንዱ ሰው ሲጎለምስም የጉልምስና ሰውነትን ያንፀባርቃል፡፡ በአዛውንትነት ዕድሜውም በተረጋጋው ማንነቱ ሰውነቱን ያበጃጃል፡፡ በስተመጨረሻም በዘመነ እርጅናው ትናንቱን እየወቀሰና እያሞገሰ፣ ዛሬ ላይ መካሪና ዘካሪ እየሆነና ወዳለፈው ጊዜ በሃሳብ ፈረስ እየጋለበ፣ ትዝታውንም እያቀነቀነ ወዳማይቀረው ይሄዳል፡፡

እነዚህ ሁሉ የተለያዩ ማንነቶች በአንድ ግለሰብ ህይወት ላይ ወጥተው የሚገቡ፤ ገብተው የሚወጡ ማንነቶች ናቸው፡፡

አምላክ የሰው ልጅ ተፈጥሮን አንድ ጊዜ ቢሰራውም ሰው ግን ማንነቱን ብዙ ጊዜ ያበጃጃዋል፡፡ እንደእውቀቱ መጠን፤ እንደአስተሳሰቡ ደረጃ፣ እንደሕይወት ገጠመኙ፣ እንደአኗኗር ሁኔታው፣ እንደአስተዳደግ ዘዬው ራሱን ይለዋውጣል፤ አዕምሮውን ያድሳል፤ ሃሳቡን ያገላብጣል፡፡

ከተፈጥሯዊው የእድሜ ጉዞው በተለየም ሰው ዕውቀትን ሲጨምር፣ አስተሳሰቡን ሲያድስ፣ ኑሮውን ሲቀይር አዲስ የአኗኗር ዘይቤን ሲከተል አዲስ ሰውነትን ይጎናፀፋል፡፡ ያው አንዱ ሰው ብዙ የተለያዩ ማንነቶችን ለራሱ ይጋብዛል፡፡ ታዲያ አንድ ሰው ስንት ነው? ብዙ ነዋ!

አንድ ጥንታዊ ፈላስፋ ያነሳው ግሩም ጥያቄ ነበር፡፡ ጥያቄውም፡-

‹‹እኔ ራሴ አንድ ሰው ሆኜ አላውቅም፡፡ ምክንያቱም አስቀድሞ እንደህፃን፣ ቀጥሎም እንደወጣት፣ ከዚያም እንደጎልማሳ፣ በመጨረሻም እንደሽማግሌ ኖሬአለሁ፡፡ ከሞት በኋላ ሕይወት ቢኖር እንኳን ዘላለማዊውን ሕይወት እንደማን ሆኜ ነው የምኖረው? እኔ የሕይወት ተሞክሮ ውጤት ነኝ፡፡ ስለሆነም ሁለትና ሶስት ወይም ከዚያ በላይ የሰው ባሕሪያትን በውስጤ ይዤ በምድር ላይ ከኖርኩ በኋላ ብሞት በምኖረው ሕይወት የመገለጫዬ ባህርይ ማን ሊሆን ነው?›› ሲል ይጠይቃል፡፡

ጥያቄው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡

ሰው ከሞት በኋላ የማንነት መገለጫው ማን እንደሆነና በየትኛውስ ማንነቱ ሊፈረጅ እንደሚገባ ማወቅ አጓጊ ነው፡፡ እንደእኔ ግን ሰው ከሞት በፊት በመጨረሻ ሕይወቱ የያዘው ማንነቱ በዕድሜው ሙሉ ያያቸውና የተለዋወጠባቸው ማንነቶች ድምር ውጤት በመሆኑ የሚፈረጀውም፣ የሚከሰሰውም፣ የሚደነቀውም ሆነ የሚከበረው በኋለኛው የህይወት ማንነቱ ነው፡፡ ምክንያቱም የመጨረሻው ሕይወቱ የዕድሜው ሁሉ መጠቅለያ ማንነት ነው፡፡

ሰው በዕድሜው ካያቸው የራሱ የተለያዩ ማንነቶች የሚወሰደውን ወስዶ፣ የሚጣለውን ጥሎ መልካሙን ማንነት መያዝ የእሱ ድርሻ ነውና፡፡ ከራስ መማርን የመሰለ ምን ወሳኝ ትምህርት አለ?! ምንም!

እድሜ ካልተማርንበት ቁጥር ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ ቁጥር ብቻ ደግሞ ዋጋ የለውም፡፡ ዋጋ ያለው ሕይወት እውን የሚሆነው የሰው ልጅ ዕድሜ በበጎ ስራ ሲቆጠርና ሲተመን ብቻ ነው፡፡ በዚች አስገራሚ ዓለም ሽማግሌ ሆነው እንደ ልጅ የሚኖሩ፤ ልጅ ሆነው እንደአዋቂ የሆኑ መኖራቸው ሃቅ ነውና፡፡

ከሞት መለስ በሕይወት እያለ የሰው ልጅ መጠየቅም፣ መኮነንም፣ መደነቅም ሆነ መከበር ካለበት በአሁናዊው ማንነቱ ነው፡፡ ዛሬ ማንነቱን በበጎ አስተሳሰብ የዋጀ ሰው ትናንት ባጠፋው መወቀስ የለበትም፡፡ የትናንቱ ጥፋት በትናንት ማንነቱ ነው ሊፈረጅ የሚገባው፡፡ ዛሬ አዲስ ሰው ነውና!

የአመክንዮ ሕግም በትናንት ማንነቱ የዛሬውን አዲስ ማንነቱን የሚደመድሙ ሰዎች ልክ እንዳልሆኑ ይናገራል፡፡ ይሄንንም Miss-representation Fallacy ሲል ይገልፀዋል፡፡ ዛሬ አዲስ ሰው ነውና የትናንቱን ሽሯል፡፡ የትናንት አሮጌ አስተሳሰቡን በአዲስ አስተሳሰብ አድሷል፡፡ የትናንት አላዋቂነቱን በዛሬ ዕውቀቱ ቀይሯል፡፡ ትናንት ያልገባው ዛሬ ገብቶታልና፡፡

ታላቁ የነፃነት ታጋይ የነበሩት ኔልሰን ማንዴላ እንዲህ ይሉናል፡-

‹‹በስኬቴ አትዳኙኝ፡፡ ይልቁንስ ምን ያህል ጊዜ ወድቄ ምን ያህል ጊዜ መልሼ እንደተነሳሁ አይታቹህ ፍረዱኝ ›› ይላሉ፡፡

አዎ! የአወዳደቅህ ሳይሆን የአነሳስህ ሁኔታ ያንተን ማንነት አጥርቶ ያሳያል፡፡ የወደቁ ሳይሆን ከውድቀታቸው የተነሱ አዕምሯቸው ሰፊ ስለመሆኑ ክርክር አያሻውም፡፡

በጠባቡ አስተሳሰባቸው ወድቀው በሰፊ አስተሳሰባቸው ሕይወታቸውን ያሰፉና ከውድቀታቸው የተነሱ ትንሳኤ ብሩሃን የሆኑ ሊደነቁ ይገባል፡፡ ምክንያቱም በመውደቅ መነሳታቸው መካከል ያገኙት ትምህርት እንዴት ከውድቀት መነሳት እንደሚቻል አዲስ ዕውቀት አስጨብጧቸዋል፡፡ ተስፋ ቆርጠው ወድቀው አለመቅረታቸው የሚያሳየው የአስተሳሰባቸው ጮራ ምን ያህል የበራ እንደነበረ የሚያሳይ ነውና፡፡

አዎ! ዛሬ ዛሬ ብዙዎቻችን በተለያዩ ውድቀቶችና አወዳደቆች ተፍገምግመናል፡፡ የሚያሳፍረውና የሚያስፈራው ነገር ከውድቀታችን ለመነሳት ፍላጎቱም ሆነ ቁርጠኝነቱ የሌለን መሆኑ ነው፡፡

👉 አንዳንዶች በዘረኝነት ወድቀዋል፣ 👉 ጥቂቶች በትእቢት በአፍጢማቸው ተተክለዋል፡፡
👉 ቀላል ቁጥር የሌላቸው አወቅን ብለው ደንቁረዋል፤ ሰፋን ብለው ጠብበዋል፡፡
👉 ሰለጠንን ያሉት እቡያን ሰይጥነዋል፡፡
👉 ከዕድሜአቸው ያልተማሩ፤ ከብዝሃ ማንነታቸው ቀለም ያልቆጠሩ፣ መልካሙን ያልኮረጁ ቆመ-ቀሮች ቤት ይቁጠራቸው፡፡
👉 ከብዝሃ ማንነታቸው ያልተማሩ በአንዱ ማንነታቸው የሙጥኝ ያሉ አዲስ ሃሳብ ያስደነግጣቸዋል፤ ለውጥ ይቀፋቸዋል፤ አዲስ ማንነት ያስፈራቸዋል፡፡

አዎ! አንድ ሰው ብዙ ነው፡፡ ብዙነቱን ግን እውን የሚያደርገው በሰፊው አስተሳሰቡ ሲሰፋ ነው፡፡

ከተፈራረቁበት ማንነቶቹ ጠቃሚውን ማንነት ፈልቅቆ የሚያወጣ ብልህ ሰው ከብዙነቱ እልፍ ትምህርት ቀስሟል፡፡ ቅስሙን የሚሰብር ሳይሆን ቅስሙን በአዲስ አስተሳሰብ የሚጠግን ጀግና ካለፈው ሕይወቱ ብዙ የተማረ ነው፡፡ ከውድቀቱ የሚማር መላልሶ መነሳት አይቸግረውምና፡፡

ወዳጄ ሆይ…

👉 አንተ አንድ ሰው አይደለህምና እንደብዙ ሰው አስብ!

👉 መውደቅን አትፍራ! ነገር ግን እንዴት ከወደቅበት ቦታ መነሳት እንደምትችል አዕምሮህን አሰራ፡፡

👉 መውደቅ በማንም ላይ የሚደርስ ነው፡፡ ከዛ ይልቅ ወድቆ መቅረት ነው አሳፋሪው ነገር፡፡

ቸር መነሳት! ቸር ትንሳኤ! ቸር ብዝሃነት!

✍️ እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)

ይህን ፅሁፍ አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ #like #repost #copylink #share ማድረግን አትርሱ
-----------------------------
በርካታ አስተማሪና የላቁ ዕይታዎችን በምናጋራበት ወደ #tiktok አካውንታችን 👉 https://www.tiktok.com/@higherperspective1?_t=8liGZZvXfIT&_r=1 እየገባችሁ ቤተሰብ ሁኑ።



tg-me.com/lighthouselearningcenter/3490
Create:
Last Update:

አንድ ሰው ብዙ ሰው ነው፡፡ ብዙ ሰው ግን አንድ ሰው ሊሆን አይችልም፡፡

የአንድ ሰው ብዙነት ከዕድሜው የሚያገኛቸው ብዝሃ ማንነቱ ነው፡፡ አንድ ሰው በልጅነቱ የልጅነት አስተሳሰብና ማንነት አለው፤ በወጣትነቱም የወጣትነቱን ሰውነትና የትኩስነት ማንነቱን ይይዛል፡፡ ያው አንዱ ሰው ሲጎለምስም የጉልምስና ሰውነትን ያንፀባርቃል፡፡ በአዛውንትነት ዕድሜውም በተረጋጋው ማንነቱ ሰውነቱን ያበጃጃል፡፡ በስተመጨረሻም በዘመነ እርጅናው ትናንቱን እየወቀሰና እያሞገሰ፣ ዛሬ ላይ መካሪና ዘካሪ እየሆነና ወዳለፈው ጊዜ በሃሳብ ፈረስ እየጋለበ፣ ትዝታውንም እያቀነቀነ ወዳማይቀረው ይሄዳል፡፡

እነዚህ ሁሉ የተለያዩ ማንነቶች በአንድ ግለሰብ ህይወት ላይ ወጥተው የሚገቡ፤ ገብተው የሚወጡ ማንነቶች ናቸው፡፡

አምላክ የሰው ልጅ ተፈጥሮን አንድ ጊዜ ቢሰራውም ሰው ግን ማንነቱን ብዙ ጊዜ ያበጃጃዋል፡፡ እንደእውቀቱ መጠን፤ እንደአስተሳሰቡ ደረጃ፣ እንደሕይወት ገጠመኙ፣ እንደአኗኗር ሁኔታው፣ እንደአስተዳደግ ዘዬው ራሱን ይለዋውጣል፤ አዕምሮውን ያድሳል፤ ሃሳቡን ያገላብጣል፡፡

ከተፈጥሯዊው የእድሜ ጉዞው በተለየም ሰው ዕውቀትን ሲጨምር፣ አስተሳሰቡን ሲያድስ፣ ኑሮውን ሲቀይር አዲስ የአኗኗር ዘይቤን ሲከተል አዲስ ሰውነትን ይጎናፀፋል፡፡ ያው አንዱ ሰው ብዙ የተለያዩ ማንነቶችን ለራሱ ይጋብዛል፡፡ ታዲያ አንድ ሰው ስንት ነው? ብዙ ነዋ!

አንድ ጥንታዊ ፈላስፋ ያነሳው ግሩም ጥያቄ ነበር፡፡ ጥያቄውም፡-

‹‹እኔ ራሴ አንድ ሰው ሆኜ አላውቅም፡፡ ምክንያቱም አስቀድሞ እንደህፃን፣ ቀጥሎም እንደወጣት፣ ከዚያም እንደጎልማሳ፣ በመጨረሻም እንደሽማግሌ ኖሬአለሁ፡፡ ከሞት በኋላ ሕይወት ቢኖር እንኳን ዘላለማዊውን ሕይወት እንደማን ሆኜ ነው የምኖረው? እኔ የሕይወት ተሞክሮ ውጤት ነኝ፡፡ ስለሆነም ሁለትና ሶስት ወይም ከዚያ በላይ የሰው ባሕሪያትን በውስጤ ይዤ በምድር ላይ ከኖርኩ በኋላ ብሞት በምኖረው ሕይወት የመገለጫዬ ባህርይ ማን ሊሆን ነው?›› ሲል ይጠይቃል፡፡

ጥያቄው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡

ሰው ከሞት በኋላ የማንነት መገለጫው ማን እንደሆነና በየትኛውስ ማንነቱ ሊፈረጅ እንደሚገባ ማወቅ አጓጊ ነው፡፡ እንደእኔ ግን ሰው ከሞት በፊት በመጨረሻ ሕይወቱ የያዘው ማንነቱ በዕድሜው ሙሉ ያያቸውና የተለዋወጠባቸው ማንነቶች ድምር ውጤት በመሆኑ የሚፈረጀውም፣ የሚከሰሰውም፣ የሚደነቀውም ሆነ የሚከበረው በኋለኛው የህይወት ማንነቱ ነው፡፡ ምክንያቱም የመጨረሻው ሕይወቱ የዕድሜው ሁሉ መጠቅለያ ማንነት ነው፡፡

ሰው በዕድሜው ካያቸው የራሱ የተለያዩ ማንነቶች የሚወሰደውን ወስዶ፣ የሚጣለውን ጥሎ መልካሙን ማንነት መያዝ የእሱ ድርሻ ነውና፡፡ ከራስ መማርን የመሰለ ምን ወሳኝ ትምህርት አለ?! ምንም!

እድሜ ካልተማርንበት ቁጥር ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ ቁጥር ብቻ ደግሞ ዋጋ የለውም፡፡ ዋጋ ያለው ሕይወት እውን የሚሆነው የሰው ልጅ ዕድሜ በበጎ ስራ ሲቆጠርና ሲተመን ብቻ ነው፡፡ በዚች አስገራሚ ዓለም ሽማግሌ ሆነው እንደ ልጅ የሚኖሩ፤ ልጅ ሆነው እንደአዋቂ የሆኑ መኖራቸው ሃቅ ነውና፡፡

ከሞት መለስ በሕይወት እያለ የሰው ልጅ መጠየቅም፣ መኮነንም፣ መደነቅም ሆነ መከበር ካለበት በአሁናዊው ማንነቱ ነው፡፡ ዛሬ ማንነቱን በበጎ አስተሳሰብ የዋጀ ሰው ትናንት ባጠፋው መወቀስ የለበትም፡፡ የትናንቱ ጥፋት በትናንት ማንነቱ ነው ሊፈረጅ የሚገባው፡፡ ዛሬ አዲስ ሰው ነውና!

የአመክንዮ ሕግም በትናንት ማንነቱ የዛሬውን አዲስ ማንነቱን የሚደመድሙ ሰዎች ልክ እንዳልሆኑ ይናገራል፡፡ ይሄንንም Miss-representation Fallacy ሲል ይገልፀዋል፡፡ ዛሬ አዲስ ሰው ነውና የትናንቱን ሽሯል፡፡ የትናንት አሮጌ አስተሳሰቡን በአዲስ አስተሳሰብ አድሷል፡፡ የትናንት አላዋቂነቱን በዛሬ ዕውቀቱ ቀይሯል፡፡ ትናንት ያልገባው ዛሬ ገብቶታልና፡፡

ታላቁ የነፃነት ታጋይ የነበሩት ኔልሰን ማንዴላ እንዲህ ይሉናል፡-

‹‹በስኬቴ አትዳኙኝ፡፡ ይልቁንስ ምን ያህል ጊዜ ወድቄ ምን ያህል ጊዜ መልሼ እንደተነሳሁ አይታቹህ ፍረዱኝ ›› ይላሉ፡፡

አዎ! የአወዳደቅህ ሳይሆን የአነሳስህ ሁኔታ ያንተን ማንነት አጥርቶ ያሳያል፡፡ የወደቁ ሳይሆን ከውድቀታቸው የተነሱ አዕምሯቸው ሰፊ ስለመሆኑ ክርክር አያሻውም፡፡

በጠባቡ አስተሳሰባቸው ወድቀው በሰፊ አስተሳሰባቸው ሕይወታቸውን ያሰፉና ከውድቀታቸው የተነሱ ትንሳኤ ብሩሃን የሆኑ ሊደነቁ ይገባል፡፡ ምክንያቱም በመውደቅ መነሳታቸው መካከል ያገኙት ትምህርት እንዴት ከውድቀት መነሳት እንደሚቻል አዲስ ዕውቀት አስጨብጧቸዋል፡፡ ተስፋ ቆርጠው ወድቀው አለመቅረታቸው የሚያሳየው የአስተሳሰባቸው ጮራ ምን ያህል የበራ እንደነበረ የሚያሳይ ነውና፡፡

አዎ! ዛሬ ዛሬ ብዙዎቻችን በተለያዩ ውድቀቶችና አወዳደቆች ተፍገምግመናል፡፡ የሚያሳፍረውና የሚያስፈራው ነገር ከውድቀታችን ለመነሳት ፍላጎቱም ሆነ ቁርጠኝነቱ የሌለን መሆኑ ነው፡፡

👉 አንዳንዶች በዘረኝነት ወድቀዋል፣ 👉 ጥቂቶች በትእቢት በአፍጢማቸው ተተክለዋል፡፡
👉 ቀላል ቁጥር የሌላቸው አወቅን ብለው ደንቁረዋል፤ ሰፋን ብለው ጠብበዋል፡፡
👉 ሰለጠንን ያሉት እቡያን ሰይጥነዋል፡፡
👉 ከዕድሜአቸው ያልተማሩ፤ ከብዝሃ ማንነታቸው ቀለም ያልቆጠሩ፣ መልካሙን ያልኮረጁ ቆመ-ቀሮች ቤት ይቁጠራቸው፡፡
👉 ከብዝሃ ማንነታቸው ያልተማሩ በአንዱ ማንነታቸው የሙጥኝ ያሉ አዲስ ሃሳብ ያስደነግጣቸዋል፤ ለውጥ ይቀፋቸዋል፤ አዲስ ማንነት ያስፈራቸዋል፡፡

አዎ! አንድ ሰው ብዙ ነው፡፡ ብዙነቱን ግን እውን የሚያደርገው በሰፊው አስተሳሰቡ ሲሰፋ ነው፡፡

ከተፈራረቁበት ማንነቶቹ ጠቃሚውን ማንነት ፈልቅቆ የሚያወጣ ብልህ ሰው ከብዙነቱ እልፍ ትምህርት ቀስሟል፡፡ ቅስሙን የሚሰብር ሳይሆን ቅስሙን በአዲስ አስተሳሰብ የሚጠግን ጀግና ካለፈው ሕይወቱ ብዙ የተማረ ነው፡፡ ከውድቀቱ የሚማር መላልሶ መነሳት አይቸግረውምና፡፡

ወዳጄ ሆይ…

👉 አንተ አንድ ሰው አይደለህምና እንደብዙ ሰው አስብ!

👉 መውደቅን አትፍራ! ነገር ግን እንዴት ከወደቅበት ቦታ መነሳት እንደምትችል አዕምሮህን አሰራ፡፡

👉 መውደቅ በማንም ላይ የሚደርስ ነው፡፡ ከዛ ይልቅ ወድቆ መቅረት ነው አሳፋሪው ነገር፡፡

ቸር መነሳት! ቸር ትንሳኤ! ቸር ብዝሃነት!

✍️ እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)

ይህን ፅሁፍ አስተማሪ ሆኖ ካገኛችሁት ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ #like #repost #copylink #share ማድረግን አትርሱ
-----------------------------
በርካታ አስተማሪና የላቁ ዕይታዎችን በምናጋራበት ወደ #tiktok አካውንታችን 👉 https://www.tiktok.com/@higherperspective1?_t=8liGZZvXfIT&_r=1 እየገባችሁ ቤተሰብ ሁኑ።

BY Lighthouse Training & Consulting PLC




Share with your friend now:
tg-me.com/lighthouselearningcenter/3490

View MORE
Open in Telegram


Lighthouse Training & Consulting PLC Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram Gives Up On Crypto Blockchain Project

Durov said on his Telegram channel today that the two and a half year blockchain and crypto project has been put to sleep. Ironically, after leaving Russia because the government wanted his encryption keys to his social media firm, Durov’s cryptocurrency idea lost steam because of a U.S. court. “The technology we created allowed for an open, free, decentralized exchange of value and ideas. TON had the potential to revolutionize how people store and transfer funds and information,” he wrote on his channel. “Unfortunately, a U.S. court stopped TON from happening.”

To pay the bills, Mr. Durov is issuing investors $1 billion to $1.5 billion of company debt, with the promise of discounted equity if the company eventually goes public, the people briefed on the plans said. He has also announced plans to start selling ads in public Telegram channels as soon as later this year, as well as offering other premium services for businesses and users.

Lighthouse Training & Consulting PLC from us


Telegram Lighthouse Training & Consulting PLC
FROM USA