Telegram Group & Telegram Channel
"ማርያም እኮ ሞተች"
ኤልያስ ሽታኹን
*           *         *         *        *           
"የአብ ወዳጁ
የወልድ ደጁ
የቅዱስ መንፈስ እጁ፡፡"
                                ማርያም እኮ ሞተች፡፡

የአባጊዮረጊስ ዘጋስጫ
የማትወዳደር ምረጫ
የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴው
የቅዱስ ኤፍሬም ውዳሴው
ዮሴፍ ሲገፍፍ የለበሳት
ያዕቆብ በልቡ ያነገሣት

                              ማርያም እኮ ሞተች፡፡
ገብርኤል ለብስራት
ወዴት ልላክ? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
የቱ ጋር ነች? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
እናትህ የቷ ናት? ብሎ ያልጠየቀው
በሚካኤል አክናፍ መልኳን ስለሚያውቀው፡፡
ሰማይን ያለባላ ያቆመ
ወንዳቺ ሆድ ያዘመመ
ጥንተ ናፍቆት
የመለኮት
ዓይንሽ የሰባቱ ሰማያት መስኮት፡፡
ያ ትሁት ገፅሽን
በክንፍ ላይ ስሎሽ መላእክት ያያሉ
ለምነውት ነበር ፍጠራት እያሉ፡፡
(ቶሎ በል እያሉ)

                                   ማርያም እኮ ሞተች፡፡

በመኑ በአምሳለ መኑ ናስተማስለኪ
ነፍሴ ወዴት ደረስሽ? ማርያምን ሳትነኪ
አንቲ ውዕቱ
እኔ ምዑቱ
አንቲ መሶበ ወርቅ
እኔ የበደል ጨርቅ
አንቺ እመአምላክ
የቱ መግነዝ ቻለሽ
ትንሳኤን ወልደሽው ሞትን ትቀምሻለሽ?
አንቺም? እመብርሃን

                                      ማርያምእኮ ሞተች፡፡

ሰማይና ምድር
ወይቦ መልካቸው ሀዘን እያማጡ
እስከዛሬ አሉ
መላእክት ሁሉ እንደደነገጡ፡ 
ለክልዔቱ ጊዜ እስራኤል ጨነቀው
ከስደት ጀምሮ ኮቴዋን የሚያውቀው፡፡
የዳዊት በገና
ብቻውን ያለቅሳል ራሱን በመግረፍ
ዳዊት አላወቀም የልጅ ልጁን ማረፍ፡፡
ክልዔቱ ጊዜ ጨነቀው እስራኤል
እንኳንና አርፋ
ሲከፋት አይችልም በእርሷ እኮ ሚካኤል::
ክልዔቱ ጊዜ
ሰማይ አለቀሰ የመረረ ከሀሞት
መላእክት አያውቁም ማርያም እንደምትሞት፡፡

                               

                                           ማርያም እኮ ሞተች፡፡

ስትሰማ ኖሯ በሆዷ ቅዳሴ
አረፈች ይሉኛል  ወዮ ነው ለራሴ፡፡
አንቺን እመብርሃን ሞት በምኑ ያዘሽ
አላየሽም እንዴ አምላኩን እንዳዘዝሽ፡፡
የቱ መልአክ ሞት ተላከ ወዳንቺ
ችሎ አይገባም ቤትሽ እሺ ብለሽ እንጂ፡፡
ፍትሃት የለም ለማርያም
የተፈታ የሚገባባት እርሷ ራሷ አርያም፡፡
ለማርያም አይቀደስላት
እርሷ ራሷ ቅዳሴ ናት፡፡

                                        ማርያም እኮ ሞተች፡፡

*       *        *         *        *         *

#ማስታወሻ
   * በነገረ - ማርያም
   * ስንክሳርም እንደተነገረን
እመቤታችን በ፷፬ አመቷ  በገዛ ፍቃዷ አርፋ፡፡
ሞትን ቀምሳለች፡፡ነሐሴ ፲፮  ከሞት ተነስታ ማረጓን ልብ ይሏል፡፡
"ሞትሰ ለመዋቲ ለመዋቲ ይደሉ
ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ"


@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb



tg-me.com/menfesawi_getem_ena_menebanb/153
Create:
Last Update:

"ማርያም እኮ ሞተች"
ኤልያስ ሽታኹን
*           *         *         *        *           
"የአብ ወዳጁ
የወልድ ደጁ
የቅዱስ መንፈስ እጁ፡፡"
                                ማርያም እኮ ሞተች፡፡

የአባጊዮረጊስ ዘጋስጫ
የማትወዳደር ምረጫ
የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴው
የቅዱስ ኤፍሬም ውዳሴው
ዮሴፍ ሲገፍፍ የለበሳት
ያዕቆብ በልቡ ያነገሣት

                              ማርያም እኮ ሞተች፡፡
ገብርኤል ለብስራት
ወዴት ልላክ? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
የቱ ጋር ነች? ብሎ ጌታን ያልጠየቀው
እናትህ የቷ ናት? ብሎ ያልጠየቀው
በሚካኤል አክናፍ መልኳን ስለሚያውቀው፡፡
ሰማይን ያለባላ ያቆመ
ወንዳቺ ሆድ ያዘመመ
ጥንተ ናፍቆት
የመለኮት
ዓይንሽ የሰባቱ ሰማያት መስኮት፡፡
ያ ትሁት ገፅሽን
በክንፍ ላይ ስሎሽ መላእክት ያያሉ
ለምነውት ነበር ፍጠራት እያሉ፡፡
(ቶሎ በል እያሉ)

                                   ማርያም እኮ ሞተች፡፡

በመኑ በአምሳለ መኑ ናስተማስለኪ
ነፍሴ ወዴት ደረስሽ? ማርያምን ሳትነኪ
አንቲ ውዕቱ
እኔ ምዑቱ
አንቲ መሶበ ወርቅ
እኔ የበደል ጨርቅ
አንቺ እመአምላክ
የቱ መግነዝ ቻለሽ
ትንሳኤን ወልደሽው ሞትን ትቀምሻለሽ?
አንቺም? እመብርሃን

                                      ማርያምእኮ ሞተች፡፡

ሰማይና ምድር
ወይቦ መልካቸው ሀዘን እያማጡ
እስከዛሬ አሉ
መላእክት ሁሉ እንደደነገጡ፡ 
ለክልዔቱ ጊዜ እስራኤል ጨነቀው
ከስደት ጀምሮ ኮቴዋን የሚያውቀው፡፡
የዳዊት በገና
ብቻውን ያለቅሳል ራሱን በመግረፍ
ዳዊት አላወቀም የልጅ ልጁን ማረፍ፡፡
ክልዔቱ ጊዜ ጨነቀው እስራኤል
እንኳንና አርፋ
ሲከፋት አይችልም በእርሷ እኮ ሚካኤል::
ክልዔቱ ጊዜ
ሰማይ አለቀሰ የመረረ ከሀሞት
መላእክት አያውቁም ማርያም እንደምትሞት፡፡

                               

                                           ማርያም እኮ ሞተች፡፡

ስትሰማ ኖሯ በሆዷ ቅዳሴ
አረፈች ይሉኛል  ወዮ ነው ለራሴ፡፡
አንቺን እመብርሃን ሞት በምኑ ያዘሽ
አላየሽም እንዴ አምላኩን እንዳዘዝሽ፡፡
የቱ መልአክ ሞት ተላከ ወዳንቺ
ችሎ አይገባም ቤትሽ እሺ ብለሽ እንጂ፡፡
ፍትሃት የለም ለማርያም
የተፈታ የሚገባባት እርሷ ራሷ አርያም፡፡
ለማርያም አይቀደስላት
እርሷ ራሷ ቅዳሴ ናት፡፡

                                        ማርያም እኮ ሞተች፡፡

*       *        *         *        *         *

#ማስታወሻ
   * በነገረ - ማርያም
   * ስንክሳርም እንደተነገረን
እመቤታችን በ፷፬ አመቷ  በገዛ ፍቃዷ አርፋ፡፡
ሞትን ቀምሳለች፡፡ነሐሴ ፲፮  ከሞት ተነስታ ማረጓን ልብ ይሏል፡፡
"ሞትሰ ለመዋቲ ለመዋቲ ይደሉ
ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ"


@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb
@menfesawi_getem_ena_menebanb

BY መንፈሳዊ ግጥም እና መነባንብ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/menfesawi_getem_ena_menebanb/153

View MORE
Open in Telegram


መንፈሳዊ ግጥም እና መነባንብ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

How to Use Bitcoin?

n the U.S. people generally use Bitcoin as an alternative investment, helping diversify a portfolio apart from stocks and bonds. You can also use Bitcoin to make purchases, but the number of vendors that accept the cryptocurrency is still limited. Big companies that accept Bitcoin include Overstock, AT&T and Twitch. You may also find that some small local retailers or certain websites take Bitcoin, but you’ll have to do some digging. That said, PayPal has announced that it will enable cryptocurrency as a funding source for purchases this year, financing purchases by automatically converting crypto holdings to fiat currency for users. “They have 346 million users and they’re connected to 26 million merchants,” says Spencer Montgomery, founder of Uinta Crypto Consulting. “It’s huge.”

What is Telegram?

Telegram is a cloud-based instant messaging service that has been making rounds as a popular option for those who wish to keep their messages secure. Telegram boasts a collection of different features, but it’s best known for its ability to secure messages and media by encrypting them during transit; this prevents third-parties from snooping on messages easily. Let’s take a look at what Telegram can do and why you might want to use it.

መንፈሳዊ ግጥም እና መነባንብ from us


Telegram መንፈሳዊ ግጥም እና መነባንብ
FROM USA