tg-me.com/mnenteyiklo/2809
Last Update:
Contemplation on The Nativity of Our Lord and Savior Jesus Christ
ክፍል ሁለት
👉 በልደቱ ጊዜ ሁለት አካላት ጌታችንን አግኝተዋል የመጀመሪያዎቹ ሰብዓ ሰገል ሲሆኑ ሁለተኛዎቹ ደግሞ የበጎቹ እረኞች ናቸው። እኚህ የበጎች እረኞች የተባሉት ሰዎች የሚያግዱት በጎችን ነው፡። በዚያች ሌሊት በጎችን ለማገድ ያደረጋቸው ምክንያት በጎቹ ለኦሪት መስዋዕትነት የሚቀርቡ ስለሆነ በአውሬ እንዳይበሉ በእረኞች ይጠበቁ ነበር። ለኦሪቱ መስዋዕት የሚሆኑትን እረኞች በሌሊት ሲጠብቁ አማናዊው በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ተወለደ። እኛስ አማናዊው በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ተወልዶ የድሮ በጎቻችንን ለመሰዋት የድሮ በግ ዝሙት ዳንኪራ ዘፈን ውስጥ ያለን ስንቶቻችን ነን?
👉 እረኞች የጌታችንን ልደት ለመስማት ከ ሰብዓሰገል የቀደሙ ሆነዋል። ሰብዓ ሰገል ባለ ዕውቀት ባለ ጥበብ ናቸው ረጅም ጉዞን ካደረጉ በኋላ ነው ጌታችንን ያገኙት ለርሱ ስጦታንም ያቀረቡት ምንም የማያውቁት የዋሃን የሆኑት የሆኑት እረኞች ግን የጌታችንን ልደት በቅርብ ርቀት ነው የተረዱት። ይህ የሚያስተምረን ሌላው ነገር ቢኖር ወደ እግዚአብሔር ለመድረስ ሁለት መንገዶች ያሳየናል የመጀመሪው ልክ እንደ ሰብዓ ሰገል ረጅሙና አድካሚው በጥበብና በእውቀት የሚገኘው መንገድ የተጓዙ ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ ያልተማሩ ነገር ግን የዋሀን የሆኑት እረኞች የተጓዙበት የትህትና እና የየዋህነት መንገድ ነው። እግዚአብሔርን በቀላሉ ለማግኘት የየዋኅነትን የትህትናን መንገድ መከተል ይገባል ሲል ነው።
👉 ጌታችን የተወለደባት ቤቴልሔም ሌላው ጉዳይ ነው። ። በቤቴልሔም እንስሳት ለጌታችን እስትንፋስን ገብረውለታል። ሰው ግን ጌታችንን እያሳደደ ነበር። ሰው ያሳደደውን አምላክ እንስሳት እስትንፋስ ገበሩለት። መላዕክት መጥተው አመሰገኑ ብስራትን አደረጉ መላዕክት ሰው ሰላም በማግኘቱ ደስ ይሰኛሉ። ለኛ ብሎ የመጣውን አምላክ መላዕክት ደስ ሲሰኙበት ለኛ ብሎ የመጣውን አምላክ ግን ከልደቱ አንስቶ እስከ ሞቱ ድረስ ያሳደደው ሰው ነው። የጌታችን ፍቅር በምን ይገለጣል? ላድነው ብመጣ አሳደደኝ ብሎ ሰውን ከመውደድ ያልተመለሰ አምላካችን እንደምን ያለ ነው?
👉 የጌታችን ትዕግስት የተገለጠበት ሌላው ጉዳይ ጌታችን አምላክ ሆኖ ሳለ ወዲያው ልደግ በቅጽበት ልደግ አላለም ወንጌል በጥቂት በጥቂቱ አደገ አለን። 9 ወር በማህጸን ቆየ። ቅዱስ ኤፍሬም ይህን ይዞ አትሰላቹ ደካማ አትሁኑ ጌታችን ለመወለድ አምላክ ሆኖ ሳለ ዘጠኝ ወርን በማህጸን ታግሶ የለምን? በክፉዎች አይሁድ መሃል 30 ዓመት ቆይቶ የለምን? በማለት ይናገራል።
✍ ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]
BY ምን እንጠይቅሎ?
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/mnenteyiklo/2809