Telegram Group & Telegram Channel
"ያመነ የተጠመቀም ይድናል" ተብሏልና "ያመነ" ብሎ ስለሚጀምር እምነት ይቀድማል ከዚያም ጥምቀት ይከተላል የሚሉ  ሕፃናትም ለማመን አልበቁምና ማጥመቅ አይገባም የሚሉ አሉ

[የሕጻናት ጥምቀት- Paedobaptism]

👉 በመጀመርያ በራሳቸው ቅደም ተከተል አበጅተው እምነት ይቀድማል ካሉ በማቴ 28:19  ላይ "እንግዲህ ሂዱ አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኀቸው ያዘዝኀችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኀቸው ደቀ መዛሙርቴ አድርጓቸው፡፡" ላይ እያጠመቃችኀቸው ካለ በኋላ  ነውና አስተምሩ የሚለው እዚህ ላይ ደግሞ ጥምቀት ሲቀድም እንመለከታለን፡፡ ታድያ መጽሐፍ ቅዱስ ርስ በርሱ ይጣረሳል? አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስን ለራስ  እንዲመች አድርጎ የመጥቀስ ስህተት የፈጠረው እንጂ። ለማመን ያልደረሱ ህፃናት በቤተሰብ እምነት ይጠመቃሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያንም ነገረ ሐይማኖትን እንዲያውቁ በመንፈሳዊ ጉዞ በክርስትና ሕይወት እንዲጓዙ ሲባል ኃላፊነት የሚወስድ የክርስትና አባት [God father] ይሰጣል፡፡  በመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው እምነት ተሸጋጋሪ ነው፡፡ የአባት እምነት ለልጅ ሲጠቅም እንመለከታለን፡፡ ለዚህም የመቶ አለቃውና (ማቴ 8:8-10ን ተመልከቱ) የከነናዊቷን ሴት ታሪክ (ማቴ 15:22-28ን ተመልከቱ) ማስታወስ ይበቃል፡፡ በአባት እምነት ልጁ ሲድን ሲፈወስ እንመለከታለን፡፡ በከነናዊቷ ሴትም እምነት ልጇ ስትድን እንመለከታለን፡፡ በአንዱ እምነት ሌላው ሲፈወስ ሲድን እንመለከታለን፡፡ እምነት ተሸጋጋሪ ነውና፡፡ [መርሐ ጽድቅ ባሕለ ኃይማኖት፤ ሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ] ስለዚህ በቤተሰብ እምነት ልጅን ማጥመቅ ይገባል፡፡

ጌታ በወንጌል ለኒቆዲሞስ " ሰው ዳግመኛ ከካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግስት ሊያይ አይችልም" ዮሐ 3:3 ብሎታል። በጥምቀት ዳግም መወለድ ለድኅነት ያስፈልጋል፡፡ ድኅነት ደግሞ ለአዋቂ ብቻ የተሰጠ ሳይሆን ለህፃናትም ጭምር ነው እንጂ፡፡

👉 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
- በሐዋ 16 :15 "እርሷም ከቤተሰቦቿ ጋር ከተጠመቀች በኋላ..."
- ሐዋ 16:33 "ያን ጊዜም እርሱ ከቤተሰቦቹ ጋር ተጠመቀ" ልድያ ከቤተሰቦቿ ጋር እንደተጠመቀች:  የወኅኒ ጠባቂውም ከነቤተሰቦቹ እንደተጠመቀ ይነግረናል፡፡ ህፃናት ደግሞ የቤተሰብ አካል ናቸው፡፡  "ከነቤተሰቦቹ" ተባለ እንጂ ከህፃናት በቀር አልተባለም፡፡ ይህም የህፃናትን ጥምቀት እንዲገባ ያስተምረናል፡፡

👉 በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ከአብርሃም ጋር ቃል ኪዳን በገባው መሰረት የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚባሉት ይገዘሩ ነበር። ግዝረቱም በተወለዱ በ8ኛው ቀን ይፈጸማል። ምንም የማያውቁት ሕጻናት ተገዝረው የእግዚአብሔር ወገን መሆንን ያገኛሉ አይከለከሉምም። ይህ ግዝረት ለጥምቀት ምሳሌ ነው። ቆላ.2:11-12:: ስለዚህ ለማመን ያልደረሱትን ሕጻናትን ማጥመቅ ይገባል። እስራኤል ዘሥጋ ባሕሩ ተከፍሎላቸው የመሻገራቸው ነገር የጥምቀት ምሳሌ ነው። 1ኛ ቆሮ 10:2። ባሕሩ ተከፍሎላቸው የተሻገሩት አዋቂዎች ብቻ አልነበሩም ሕጻናትም ነበሩ። በምሳሌው ይህን ከተማርን በአማናዊው ጥምቀት ደግሞ ሕጻናትን ጭምር ማጥመቅ እንደሚገባ ያስተምረናል።

ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]

ይቀጥላል...



tg-me.com/mnenteyiklo/2814
Create:
Last Update:

"ያመነ የተጠመቀም ይድናል" ተብሏልና "ያመነ" ብሎ ስለሚጀምር እምነት ይቀድማል ከዚያም ጥምቀት ይከተላል የሚሉ  ሕፃናትም ለማመን አልበቁምና ማጥመቅ አይገባም የሚሉ አሉ

[የሕጻናት ጥምቀት- Paedobaptism]

👉 በመጀመርያ በራሳቸው ቅደም ተከተል አበጅተው እምነት ይቀድማል ካሉ በማቴ 28:19  ላይ "እንግዲህ ሂዱ አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኀቸው ያዘዝኀችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኀቸው ደቀ መዛሙርቴ አድርጓቸው፡፡" ላይ እያጠመቃችኀቸው ካለ በኋላ  ነውና አስተምሩ የሚለው እዚህ ላይ ደግሞ ጥምቀት ሲቀድም እንመለከታለን፡፡ ታድያ መጽሐፍ ቅዱስ ርስ በርሱ ይጣረሳል? አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስን ለራስ  እንዲመች አድርጎ የመጥቀስ ስህተት የፈጠረው እንጂ። ለማመን ያልደረሱ ህፃናት በቤተሰብ እምነት ይጠመቃሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያንም ነገረ ሐይማኖትን እንዲያውቁ በመንፈሳዊ ጉዞ በክርስትና ሕይወት እንዲጓዙ ሲባል ኃላፊነት የሚወስድ የክርስትና አባት [God father] ይሰጣል፡፡  በመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው እምነት ተሸጋጋሪ ነው፡፡ የአባት እምነት ለልጅ ሲጠቅም እንመለከታለን፡፡ ለዚህም የመቶ አለቃውና (ማቴ 8:8-10ን ተመልከቱ) የከነናዊቷን ሴት ታሪክ (ማቴ 15:22-28ን ተመልከቱ) ማስታወስ ይበቃል፡፡ በአባት እምነት ልጁ ሲድን ሲፈወስ እንመለከታለን፡፡ በከነናዊቷ ሴትም እምነት ልጇ ስትድን እንመለከታለን፡፡ በአንዱ እምነት ሌላው ሲፈወስ ሲድን እንመለከታለን፡፡ እምነት ተሸጋጋሪ ነውና፡፡ [መርሐ ጽድቅ ባሕለ ኃይማኖት፤ ሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ] ስለዚህ በቤተሰብ እምነት ልጅን ማጥመቅ ይገባል፡፡

ጌታ በወንጌል ለኒቆዲሞስ " ሰው ዳግመኛ ከካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግስት ሊያይ አይችልም" ዮሐ 3:3 ብሎታል። በጥምቀት ዳግም መወለድ ለድኅነት ያስፈልጋል፡፡ ድኅነት ደግሞ ለአዋቂ ብቻ የተሰጠ ሳይሆን ለህፃናትም ጭምር ነው እንጂ፡፡

👉 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
- በሐዋ 16 :15 "እርሷም ከቤተሰቦቿ ጋር ከተጠመቀች በኋላ..."
- ሐዋ 16:33 "ያን ጊዜም እርሱ ከቤተሰቦቹ ጋር ተጠመቀ" ልድያ ከቤተሰቦቿ ጋር እንደተጠመቀች:  የወኅኒ ጠባቂውም ከነቤተሰቦቹ እንደተጠመቀ ይነግረናል፡፡ ህፃናት ደግሞ የቤተሰብ አካል ናቸው፡፡  "ከነቤተሰቦቹ" ተባለ እንጂ ከህፃናት በቀር አልተባለም፡፡ ይህም የህፃናትን ጥምቀት እንዲገባ ያስተምረናል፡፡

👉 በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ከአብርሃም ጋር ቃል ኪዳን በገባው መሰረት የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚባሉት ይገዘሩ ነበር። ግዝረቱም በተወለዱ በ8ኛው ቀን ይፈጸማል። ምንም የማያውቁት ሕጻናት ተገዝረው የእግዚአብሔር ወገን መሆንን ያገኛሉ አይከለከሉምም። ይህ ግዝረት ለጥምቀት ምሳሌ ነው። ቆላ.2:11-12:: ስለዚህ ለማመን ያልደረሱትን ሕጻናትን ማጥመቅ ይገባል። እስራኤል ዘሥጋ ባሕሩ ተከፍሎላቸው የመሻገራቸው ነገር የጥምቀት ምሳሌ ነው። 1ኛ ቆሮ 10:2። ባሕሩ ተከፍሎላቸው የተሻገሩት አዋቂዎች ብቻ አልነበሩም ሕጻናትም ነበሩ። በምሳሌው ይህን ከተማርን በአማናዊው ጥምቀት ደግሞ ሕጻናትን ጭምር ማጥመቅ እንደሚገባ ያስተምረናል።

ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]

ይቀጥላል...

BY ምን እንጠይቅሎ?


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/mnenteyiklo/2814

View MORE
Open in Telegram


ምን እንጠይቅሎ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram announces Anonymous Admins

The cloud-based messaging platform is also adding Anonymous Group Admins feature. As per Telegram, this feature is being introduced for safer protests. As per the Telegram blog post, users can “Toggle Remain Anonymous in Admin rights to enable Batman mode. The anonymized admin will be hidden in the list of group members, and their messages in the chat will be signed with the group name, similar to channel posts.”

How Does Telegram Make Money?

Telegram is a free app and runs on donations. According to a blog on the telegram: We believe in fast and secure messaging that is also 100% free. Pavel Durov, who shares our vision, supplied Telegram with a generous donation, so we have quite enough money for the time being. If Telegram runs out, we will introduce non-essential paid options to support the infrastructure and finance developer salaries. But making profits will never be an end-goal for Telegram.

ምን እንጠይቅሎ from us


Telegram ምን እንጠይቅሎ?
FROM USA