Telegram Group & Telegram Channel
ጥያቄ :- ሰላም እንዴት ናችሁ?
ጥያቄ ለመጠየቅ ነበር መናፍቃን እኛ ኦርቶዶክሳውያንን አንዲት ጥምቀት ተብሎ ተጽፎ ለምን በየዓመቱ ትጠመቃላችሁ? ብለው ይጠይቃሉ ቢያብራሩልን።

መልስ

👉 ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሚለው መጽሐፋቸው የዚህን ጥያቄ መነሻና ምላሹን እንዲህ ብለው ጽፈዋል። "የጠበሉን መረጨት አይተው በቀድሞ ዘመን ወደ ሀገራችን መጥተው የነበሩ ኢየሱሳውያን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ታጠምቃለች ብለው ጽፈዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በያመቱ ይህን የምትፈጽመው ጌታችን ለእኛ ብሎ ያሳየውን ትህትና ለመመስከር ለምዕመናን በረከተ ጥምቀትን ለማሳተፍ እንጂ የተጠመቁትን ምዕመናን እየመላለሰች በየዓመቱ አታጠምቅም። ጥምቀት አሐቲ [አንዲት] መሆኗን ታውቃለችና። [የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ.126]

ዲያቆን ብርሃኑ አድማስም በዓላት በሚለው መጽሐፉ በጥምቀት የምንጠመቀው ለሥርየተ ኃጢአት ጭምር መሆኑን ሲገልጽ እንዲህ ብሎአል።   "የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያንም  ለዚሁ አንጽሖተ ማይ (ውሃውን ለመቀደስ) እና ምእመናኑም በጥምቀት (በልጅነት) የቀደመ ኃጢአታቸው የተሠረየላቸውን ያህል በዚህ ዕለትም የሠሩት ኃጢአት ይሠረይላቸዋል ትላለች። [በዓላት፤ ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ገጽ ገጽ.71] ስለዚህም በረከተ ጥምቀቱን ለምዕመናን በማድረስ ማሳተፍና ሥርየተ ኃጢአትን መስጠት እንጂ  መላልሶ ማጥመቅ አይደለም። ልጅነት አንድ ጊዜ ብቻ ነውና።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት። ኤፌ.{ 4:5። ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት አትደገምም። በጸሎተ ሐይማኖት ላይም "ኃጢአት በሚሰረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን" ይላል።  ጥምቀት ከምናከብራቸው ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ነው። ጌታችን በቅዱስ ዮሐንስ ሊጠመቅ መሄዱን የምናስብበት በዓል ነው ከጌታችን ጥምቀትም በረከትን የምንሳተፍበት በዓል ነው። ጥምቀት ሊደገም ይቅርና ይህን የጌታን ጥምቀትን በማሰብ የምናከብረውን በዓል ለማክበር መብቱ እንኳ ያላቸው ከማሕጸነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ በጥምቀት የሥላሴ ልጅነትን ያገኙ ክርስቲያኖች ናቸው። ስለዚህ በረከተ ጥምቀትን ለመሳተፍ እንጂ ልጅነት የምታሰጠዋ ጥምቀት የምትደገም ሆና አይደለም።

ጌታችን በወንጌል " የክርስቶስ ስለ ሆናችሁ በስሜ ጽዋ ውኃ የሚያጠጣችሁ ሁሉ፥ ዋጋው እንዳይጠፋበት እውነት እላችኋለሁ።" ማር.9:41 እንደተናገረ ስሙን አስበን የምናደርጋቸው የምንዘክራቸው የጌታን ዓበይትና ንዑሳን በዓላትን ማሰብ መዘከር ስለ እርሱም ብሎ ነዳያንን በምሕረት መጎብኘት ዋጋ የማያሳጣ ተግባር ነው።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]



tg-me.com/mnenteyiklo/2821
Create:
Last Update:

ጥያቄ :- ሰላም እንዴት ናችሁ?
ጥያቄ ለመጠየቅ ነበር መናፍቃን እኛ ኦርቶዶክሳውያንን አንዲት ጥምቀት ተብሎ ተጽፎ ለምን በየዓመቱ ትጠመቃላችሁ? ብለው ይጠይቃሉ ቢያብራሩልን።

መልስ

👉 ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሚለው መጽሐፋቸው የዚህን ጥያቄ መነሻና ምላሹን እንዲህ ብለው ጽፈዋል። "የጠበሉን መረጨት አይተው በቀድሞ ዘመን ወደ ሀገራችን መጥተው የነበሩ ኢየሱሳውያን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ታጠምቃለች ብለው ጽፈዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በያመቱ ይህን የምትፈጽመው ጌታችን ለእኛ ብሎ ያሳየውን ትህትና ለመመስከር ለምዕመናን በረከተ ጥምቀትን ለማሳተፍ እንጂ የተጠመቁትን ምዕመናን እየመላለሰች በየዓመቱ አታጠምቅም። ጥምቀት አሐቲ [አንዲት] መሆኗን ታውቃለችና። [የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ታሪክ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ገጽ.126]

ዲያቆን ብርሃኑ አድማስም በዓላት በሚለው መጽሐፉ በጥምቀት የምንጠመቀው ለሥርየተ ኃጢአት ጭምር መሆኑን ሲገልጽ እንዲህ ብሎአል።   "የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያንም  ለዚሁ አንጽሖተ ማይ (ውሃውን ለመቀደስ) እና ምእመናኑም በጥምቀት (በልጅነት) የቀደመ ኃጢአታቸው የተሠረየላቸውን ያህል በዚህ ዕለትም የሠሩት ኃጢአት ይሠረይላቸዋል ትላለች። [በዓላት፤ ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ ገጽ ገጽ.71] ስለዚህም በረከተ ጥምቀቱን ለምዕመናን በማድረስ ማሳተፍና ሥርየተ ኃጢአትን መስጠት እንጂ  መላልሶ ማጥመቅ አይደለም። ልጅነት አንድ ጊዜ ብቻ ነውና።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት። ኤፌ.{ 4:5። ልጅነትን የምታሰጠዋ ጥምቀት አንዲት ናት አትደገምም። በጸሎተ ሐይማኖት ላይም "ኃጢአት በሚሰረይባት በአንዲት ጥምቀት እናምናለን" ይላል።  ጥምቀት ከምናከብራቸው ከጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ነው። ጌታችን በቅዱስ ዮሐንስ ሊጠመቅ መሄዱን የምናስብበት በዓል ነው ከጌታችን ጥምቀትም በረከትን የምንሳተፍበት በዓል ነው። ጥምቀት ሊደገም ይቅርና ይህን የጌታን ጥምቀትን በማሰብ የምናከብረውን በዓል ለማክበር መብቱ እንኳ ያላቸው ከማሕጸነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ በጥምቀት የሥላሴ ልጅነትን ያገኙ ክርስቲያኖች ናቸው። ስለዚህ በረከተ ጥምቀትን ለመሳተፍ እንጂ ልጅነት የምታሰጠዋ ጥምቀት የምትደገም ሆና አይደለም።

ጌታችን በወንጌል " የክርስቶስ ስለ ሆናችሁ በስሜ ጽዋ ውኃ የሚያጠጣችሁ ሁሉ፥ ዋጋው እንዳይጠፋበት እውነት እላችኋለሁ።" ማር.9:41 እንደተናገረ ስሙን አስበን የምናደርጋቸው የምንዘክራቸው የጌታን ዓበይትና ንዑሳን በዓላትን ማሰብ መዘከር ስለ እርሱም ብሎ ነዳያንን በምሕረት መጎብኘት ዋጋ የማያሳጣ ተግባር ነው።


ተክለ ማርያም [ጅማ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት]

BY ምን እንጠይቅሎ?


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/mnenteyiklo/2821

View MORE
Open in Telegram


ምን እንጠይቅሎ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

How to Invest in Bitcoin?

Like a stock, you can buy and hold Bitcoin as an investment. You can even now do so in special retirement accounts called Bitcoin IRAs. No matter where you choose to hold your Bitcoin, people’s philosophies on how to invest it vary: Some buy and hold long term, some buy and aim to sell after a price rally, and others bet on its price decreasing. Bitcoin’s price over time has experienced big price swings, going as low as $5,165 and as high as $28,990 in 2020 alone. “I think in some places, people might be using Bitcoin to pay for things, but the truth is that it’s an asset that looks like it’s going to be increasing in value relatively quickly for some time,” Marquez says. “So why would you sell something that’s going to be worth so much more next year than it is today? The majority of people that hold it are long-term investors.”

Among the actives, Ascendas REIT sank 0.64 percent, while CapitaLand Integrated Commercial Trust plummeted 1.42 percent, City Developments plunged 1.12 percent, Dairy Farm International tumbled 0.86 percent, DBS Group skidded 0.68 percent, Genting Singapore retreated 0.67 percent, Hongkong Land climbed 1.30 percent, Mapletree Commercial Trust lost 0.47 percent, Mapletree Logistics Trust tanked 0.95 percent, Oversea-Chinese Banking Corporation dropped 0.61 percent, SATS rose 0.24 percent, SembCorp Industries shed 0.54 percent, Singapore Airlines surrendered 0.79 percent, Singapore Exchange slid 0.30 percent, Singapore Press Holdings declined 1.03 percent, Singapore Technologies Engineering dipped 0.26 percent, SingTel advanced 0.81 percent, United Overseas Bank fell 0.39 percent, Wilmar International eased 0.24 percent, Yangzijiang Shipbuilding jumped 1.42 percent and Keppel Corp, Thai Beverage, CapitaLand and Comfort DelGro were unchanged.

ምን እንጠይቅሎ from us


Telegram ምን እንጠይቅሎ?
FROM USA