tg-me.com/eslamic_center/477
Last Update:
#አኽላቃችን
የሰዎች አኽላቅ ይበልጥ ቁልጭ ብሎ የሚታየው በችግር ጊዜ ነው።
በሰላምና ሁሉም ነገር በፈለጉት አቅጣጫ እየሄደ ባለበት ወቅት ላይ ሁሉም ሰው አመለ-ሸጋና አኽላቀ- ሙሉእ ነው።
አኽላቅ ትልቅ የዲን አካል እንደመሆኑ፤ ሰላትና መሰል ዒባዳዎች ላይ በሁሉም ሁኔታዎች ላይ እንደምንጸናው ሁሉ መልካም አኽላቅና ኢስላማዊ አደቦች ላይም ሁሌም እንጽና።
ችግር፣ ንዴትና ሰዎች እኛን መበደላቸው ከሙስሊም የማይጠበቅ የወረደ አኽላቅ እንዲኖረን አያድርገን።
ትክክለኛ ሙስሊም ጦር ሜዳ ላይ እንኳ ሆኖ ኢስላም ያዘዘውን አጠቃላይ አኽላቅና አደብ አይለቅም!
የተነካ ወይም የተጎዳ በመሰለው ቁጥር ከሚገባው በላይ ጸባዩ የሚለዋወጥ፣ ስሜቱን መቆጣጠር የሚሳነውና የሚናገረውን የማያውቅ ሙስሊም፤
{"ትክክለኛ የአላህ ባሮች (የጀነት እጩዎች) በቁጣ ጊዜ ንዴታቸውን ዋጥ የሚያደርጉ ናቸው"} የሚለውን የአላህን ቃል ሊያስታውስና ሊረጋጋ ይገባዋል።
ሁሌም አብሮን የሚኖር መልካም አኽላቅ አላህ ያድለን።
BY ISLAMIC-CENTER
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/eslamic_center/477