Telegram Group & Telegram Channel
"አባት ሆይ! ቢቻልስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ"

[ይህ ጽሑፍ የተወሰደው ዓርብ ሌሊት ስድስት ሰዓት ከሚነበበው ከግብረ ሕማማት መጽሐፍ ነው፡፡ የተጻፈውም በጊዜው ለነበሩ መርቅያናውያንና ማኒያውያን ለተባሉ መናፍቃን ምላሽ ሲሆን በእኛ ዘመን ደግሞ በግልጥ
ለሙስሊም፣ ለይሖዋ ምስክሮችና አውቀውም ይሁን ሳያውቁ (ሎቱ ስብሐትና) ክርስቶስን ዝቅ ዝቅ ለሚያደርጉ ለሌሎች መናፍቃን መልስ የሚሆን ድርሳን (Homily) ነው፡፡]
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስቀድሞ “ይህን ረቂቅ ምክርና ጥልቅ ምሥጢር የማያስተውሉ ጌታ እንዲህ በማለቱ ፈርቶ ነው ይሉታል፡፡ ነገር ግን ወዳጆቼ ሆይ! እኛ ደግመን እንነግራችኋለንና አእምሯቸው ስለ ጠፋባቸው ስለ እነርሱ ዘለፋ ዛሬ
በፊታችሁ እንደ ትልልቆች ያይደሉ አእምሮ እንደሌላቸው ሕፃናት ናቸው ብለን
እንተረጕምላችኋለን” በማለት ይጀምራል፡፡ ቀጥሎም እርሱ ይጠይቅና ጌታ የመለሰለትን መልስ ይነግረናል፡፡
ብጹዕ አባታችን እንዲህ በማለት ጥያቄውን ይቀጥላል፡- “አቤቱ ጌታ ሆይ! ስለ
እኛ መከራ ትቀበል ዘንድ ለምን መጣህ? ለምንስ ለመስቀል ደረስክ? ለምን ወደህ በፈቃድህ ፈራህ? ለምን አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ አልክ? የተገዢን ባሕርይ ገንዘብ ታደርግ ዘንድ ያስገደደህ ሳይኖር አንተ በፈቃድህ የተዋሐድክ አይደለምን? አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ የሞት ጽዋ ከእኔ ይለፍ ብለህ ለምን ትማልዳለህ? ይህንንም ጽዋ ትጠጣው ዘንድ አልተጋህምን? አንተ ራስህ የምጠመቀው ጥምቀት አለኝ፤ እፈጽመውም ዘንድ እተጋለሁ፤ እስከምጠጣውም ድረስ እታወካለሁ ያልክ አይደለምን? ትጠጣው ዘንድ የተሰጠህን ዛሬ ስለምን አልተጋህም? ለምንስ እምቢ አልክ? አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ ለምን አልክ? ስለ እኛ ትሞት ዘንድ እንዳለህ
አላወቅህምን? አንተ የሰው ልጅ ክርስቶስን አብዝተው መከራ ያጸኑበታል፤ ይሰቅሉታል፤ ይገድሉታል፤ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል ያልክ አይደለምን? ደቀ መዝሙርህ ጴጥሮስን ይህ በአንተ ላይ እንዲህ ይሆን ዘንድ አይገባም ባለህ
ጊዜ፡- ከኋላዬ ወግድ አንተ ባለጋራ እንቅፋት ሁነህብኛልና የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ብለህ የገሰጽከው አይደለምን? እርሱን ጴጥሮስን የከለከልከውን እንግዲህ ለምን አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ
አልክ? የሚታየውንና የማይታየውን የፈጠርክ አንተ አይደለህምን? ድውያንን በእጅህ ዳስሰህ እንዳዳንህ በሞት ሥጋው የፈረሰውን አልዓዛርን በቃልህ አጽንተህ እንዳስነሣህ፤ የደም ምንጭም የሚፈሣትን በልብስህ ዘርፍ እንዳደረቅክ፤ በአምስት እንጀራ አምስት ሺህ ሰውን እንዳጠገብክ፤ ባሕሩን ነፋሱን ገስጸህ ጸጥ እንደ አደረግህ፤ ሞትንም ደምስሰህ እንደ አጠፋኸው
እናውቃለን፡፡ ዛሬ ሞትን እንደምትፈራ ሁነህ አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይቺ የሞት ጸዋ ከእኔ ትለፍ ለምን ትላለህ? ሞትን የምትፈራ ከሆነ ትንሣኤም ሕይወትም እኔ ነኝ ለምን አልክ? ሕይወትም ትንሣኤም ሞትን አይፈራም፡፡ እንግዲህ የሚቻል
ከሆነ ይቺ የሞት ጽዋ ከእኔ ትለፍ ለምን አልክ?
ገና ሳትፈጥረው አስቀድመህ ሁሉን የምታውቅ ሆይ! አላወቅህምን? ይህ የሞት ጽዋ ከአንተ ማለፉ ይቻል እንደሆነ አይቻልም እንደ ሆነ አስቀድመህ አታውቅምን? ከወልድ በቀር አብን የሚያውቀው የለም እንዴት አልክ? ይህም
ጽዋ ማለፉንና አለማለፉን አታውቅምን? አንተስ ጳውሎስ ከእርሱ የተሠወረ ፍጥረት የለም፤ ሁሉም በፊቱ ፈጽሞ የተገለጠ ነው እንዴት አልክ? …አሁንም እኔ አላውቅም የሚቻል ከሆነ እንግዲህ ጽዋ ከእኔ ይለፈ እንዴት አልክ? በዚህ ቃል
ውስጥ ገና ያልተገለጸ ሥውር ምሥጢር ቢኖርበትም ይህ ነገር አቤቱ ላንተ አይገባህም፡፡ አንተ የአምላክ ልጅ አምላክ ነህ፤ የእግዚአብሔር አብ ቃል ነህ፤ ጥበብና ኃይል ነህ፤ ጸዳልና ብርሃን ነህ፤ የእውነት ፀሐይ ነህ፤ በኃጢአት ለሞትን
ለእኛ የትንሣኤያችንና የሕይወታችን ምንጭ ነህ፡፡”
ብጹዕ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይህ “አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ” የሚለው ቃል “እንደማይታይና እንደማይመረመር እንደ መለኰትና እንደ ትስብእት ተዋሕዶ ይመስላል፤ ስለዚህም ይህች ምሥጢር ለብዙዎች ጭንቅና
ጠባብ መንገድ ሆነች” በማለት “ኢየሱስ ፈርቶ ይህን ቃል ተናግሮታል” የሚሉትን መናፍቃን ይገስጻል፡፡ ከዚያም ጌታ እንዲህ ሲል ምን ማለቱ እንደሆነ ለማስረዳት እርሱ በጌታ ተገብቶ (ለንግግር ያመች ዘንድ) ይመልስልናል፡፡ እንዲህም ይላል፡- “ጥበብ ለራስዋ ቤትን ሠራች ተብሎ እንደተጻፈ ራሴ የተዋሐድኩትን ሥጋ እንደፈጠርኩ፤ በሞት የደከመ ሥጋዬን ሕያው አድርጌ ማሥነሣት እንደምችል፡- አይሁድ እናንተ ግብዞች ሰነፎች ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አነሣዋለሁ ብያቸው ነበርና፤ አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ሞት ከእኔ ይለፍ ያልኩት ሞትን በመፍራትና በመደንገጥ እዳልሆነ ለራስህ እወቅ፤ ተጠንቀቅ፤ ይህ ሥውር የሆነ የምሥጢር ቃል ነው እንጂ፡፡ ይህንንም ልመና እኔ በጥበብ ተናገርኩ፡፡ ይህች ቃል ሰይጣንን ጠብቃ የምታጠምድ ወጥመድ ናት፤ በእነዚህም ቃሎች ሰይጣን አጠምደው ዘንድ አለኝና፡፡
ተአምራትን እንዳደረግሁ፣ በሽተኞችን በእጄ ዳስሼ እንዳዳንኩ፣ አጋንንትም በቃሌ እንዳባረርኩ፣ የሸተተ በድን እንዳስነሣሁ፣ ባሕሩን ነፋሱን እንደገሠፅኩ፣ እነርሱም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ እንደታዘዙልኝ ሰይጣን አይቶኝ ነበር፡፡ ያደረግሁትን ይህን ተአምራት አይቶ እኔ የአምላክ ልጅ እንደሆንኩ አውቆ እኔም ብሰቀል እርሱ እንደሚጠፋ ወደ ሲዖልም ብወርድ የብረቱን መቆለፍያ ቀጥቅጬ እንደማጠፋ የብረቱን የናሐሱን መዝጊያ ሰብሬ ሁሉን ወደ ሰማይ እንደማሳርግ ልብ ብሎ አስተውሎ ፈርቶ እንዳሸሽ፣ እንዳይጠፋ፣ በመስቀል የሚደረገው
ምሥጢረ ድኅነት እንዳይቀር እንዳይቋረጥ ምን ላድርግ? አልኩ፡፡ ስለዚህ ራሴን ብልህ እንዳጠመደው ወጥመድ አድርጌ ፈርቶ ከሞት እንደሚደነግጥም አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ አልኩ፡፡ በእነዚህም የትሕትና ቃሎቼ ዕሩቅ ብእሲ (ሰው ብቻ) እመስለዋለሁ፤ ምሥጢረ ድኅነት የሚፈጸምበት መስቀል በምድር መካከል ይተከል ዘንድ ይቸኩላል፤ በእኔ ላይ የሚጠበብብኝ እየመሰለው እኔ ግን ለሰው ሁሉ ድኅነት ከእርሱ የሚደረግብኝ ሁሉ እታገሥ ዘንድ
አለኝ፡፡እርሱ የመጀመርያውን ሰው አዳምን ያጠፋው ዘንድ እጅግ ተተንኩሎ ተጠብቦበት ነበር፡፡ በተንኰል አነጋገር አዳምን እንደ ተጠበበበት እንግዲህ እኔ ሁሉን ለማዳን በይበልጥ ለምን አልጠበብበት? እንደዚሁ እኔም እርሱ ባመጣው ተንኰል ላጠምደው ትሕትናን በተመሉ ቃሎች ተጠበብኩበት፡፡ በመለኰታዊ
አነጋገርም ለሰይጣን አልተገለጽኩለትም፤ አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ሞት ከእኔ ይለፍ አልኩ እንጂ፡፡
ዓሣ አጥማጅ መቃጥኑን በመብል ሸፍኖ ወደ ባሕር ውስጥ በሚጥለው ጊዜ ሲስበው ለዓሣው እንደሚያስጐመጀው አንድ ጊዜም ሊጐርሰው ጕረሮውን እንደሚከፍት እንዲሁም እኔ መለኰቴን መብል አድርጌ ጣልኩለት፡፡ ለዘላለሙ
በማትመረመር ተዋሕዶ በሥጋዬ ውስጥ ያለ የመለኰት መቃጥንን ጣልኩለት፡፡
በሚያጠምድበት ላይ የተደረገው የሚጐረስ ትል (ወላፍ) ካልተንቀሳቀሰ ዓሣው መንጠቆውን ለመጕረስ አይጐመጅም፡፡ ስለዚህ ሥጋዬን እንደሚጐረስ (ወላፍ) ትል አድርጌ አሳየሁት፡፡ እኔ ሰው ያይደለሁ ትል ነኝ አልኩ፡፡ ይህን ሰምቶ በዚህ
በሥጋዬ ውስጥ ያለችን መቃጥን ሩጦ ሂዶ ይጐርስ ዘንድ፡፡እኔም በመቃጥኔ እስበዋለሁ፤ በኢዮብ መጽሐፍ ከይሲን በወጥመድ ትስበዋለህ ተብሎ የተጻፈውን ይፈጸም ዘንድ፡፡እኔም ፈርቶ እንደሚሸሽ ሰው ሆኜ ነፍሴ እስከ ሞት..



tg-me.com/rituaH/2274
Create:
Last Update:

"አባት ሆይ! ቢቻልስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ"

[ይህ ጽሑፍ የተወሰደው ዓርብ ሌሊት ስድስት ሰዓት ከሚነበበው ከግብረ ሕማማት መጽሐፍ ነው፡፡ የተጻፈውም በጊዜው ለነበሩ መርቅያናውያንና ማኒያውያን ለተባሉ መናፍቃን ምላሽ ሲሆን በእኛ ዘመን ደግሞ በግልጥ
ለሙስሊም፣ ለይሖዋ ምስክሮችና አውቀውም ይሁን ሳያውቁ (ሎቱ ስብሐትና) ክርስቶስን ዝቅ ዝቅ ለሚያደርጉ ለሌሎች መናፍቃን መልስ የሚሆን ድርሳን (Homily) ነው፡፡]
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስቀድሞ “ይህን ረቂቅ ምክርና ጥልቅ ምሥጢር የማያስተውሉ ጌታ እንዲህ በማለቱ ፈርቶ ነው ይሉታል፡፡ ነገር ግን ወዳጆቼ ሆይ! እኛ ደግመን እንነግራችኋለንና አእምሯቸው ስለ ጠፋባቸው ስለ እነርሱ ዘለፋ ዛሬ
በፊታችሁ እንደ ትልልቆች ያይደሉ አእምሮ እንደሌላቸው ሕፃናት ናቸው ብለን
እንተረጕምላችኋለን” በማለት ይጀምራል፡፡ ቀጥሎም እርሱ ይጠይቅና ጌታ የመለሰለትን መልስ ይነግረናል፡፡
ብጹዕ አባታችን እንዲህ በማለት ጥያቄውን ይቀጥላል፡- “አቤቱ ጌታ ሆይ! ስለ
እኛ መከራ ትቀበል ዘንድ ለምን መጣህ? ለምንስ ለመስቀል ደረስክ? ለምን ወደህ በፈቃድህ ፈራህ? ለምን አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ አልክ? የተገዢን ባሕርይ ገንዘብ ታደርግ ዘንድ ያስገደደህ ሳይኖር አንተ በፈቃድህ የተዋሐድክ አይደለምን? አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ የሞት ጽዋ ከእኔ ይለፍ ብለህ ለምን ትማልዳለህ? ይህንንም ጽዋ ትጠጣው ዘንድ አልተጋህምን? አንተ ራስህ የምጠመቀው ጥምቀት አለኝ፤ እፈጽመውም ዘንድ እተጋለሁ፤ እስከምጠጣውም ድረስ እታወካለሁ ያልክ አይደለምን? ትጠጣው ዘንድ የተሰጠህን ዛሬ ስለምን አልተጋህም? ለምንስ እምቢ አልክ? አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ ለምን አልክ? ስለ እኛ ትሞት ዘንድ እንዳለህ
አላወቅህምን? አንተ የሰው ልጅ ክርስቶስን አብዝተው መከራ ያጸኑበታል፤ ይሰቅሉታል፤ ይገድሉታል፤ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል ያልክ አይደለምን? ደቀ መዝሙርህ ጴጥሮስን ይህ በአንተ ላይ እንዲህ ይሆን ዘንድ አይገባም ባለህ
ጊዜ፡- ከኋላዬ ወግድ አንተ ባለጋራ እንቅፋት ሁነህብኛልና የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ብለህ የገሰጽከው አይደለምን? እርሱን ጴጥሮስን የከለከልከውን እንግዲህ ለምን አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ
አልክ? የሚታየውንና የማይታየውን የፈጠርክ አንተ አይደለህምን? ድውያንን በእጅህ ዳስሰህ እንዳዳንህ በሞት ሥጋው የፈረሰውን አልዓዛርን በቃልህ አጽንተህ እንዳስነሣህ፤ የደም ምንጭም የሚፈሣትን በልብስህ ዘርፍ እንዳደረቅክ፤ በአምስት እንጀራ አምስት ሺህ ሰውን እንዳጠገብክ፤ ባሕሩን ነፋሱን ገስጸህ ጸጥ እንደ አደረግህ፤ ሞትንም ደምስሰህ እንደ አጠፋኸው
እናውቃለን፡፡ ዛሬ ሞትን እንደምትፈራ ሁነህ አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይቺ የሞት ጸዋ ከእኔ ትለፍ ለምን ትላለህ? ሞትን የምትፈራ ከሆነ ትንሣኤም ሕይወትም እኔ ነኝ ለምን አልክ? ሕይወትም ትንሣኤም ሞትን አይፈራም፡፡ እንግዲህ የሚቻል
ከሆነ ይቺ የሞት ጽዋ ከእኔ ትለፍ ለምን አልክ?
ገና ሳትፈጥረው አስቀድመህ ሁሉን የምታውቅ ሆይ! አላወቅህምን? ይህ የሞት ጽዋ ከአንተ ማለፉ ይቻል እንደሆነ አይቻልም እንደ ሆነ አስቀድመህ አታውቅምን? ከወልድ በቀር አብን የሚያውቀው የለም እንዴት አልክ? ይህም
ጽዋ ማለፉንና አለማለፉን አታውቅምን? አንተስ ጳውሎስ ከእርሱ የተሠወረ ፍጥረት የለም፤ ሁሉም በፊቱ ፈጽሞ የተገለጠ ነው እንዴት አልክ? …አሁንም እኔ አላውቅም የሚቻል ከሆነ እንግዲህ ጽዋ ከእኔ ይለፈ እንዴት አልክ? በዚህ ቃል
ውስጥ ገና ያልተገለጸ ሥውር ምሥጢር ቢኖርበትም ይህ ነገር አቤቱ ላንተ አይገባህም፡፡ አንተ የአምላክ ልጅ አምላክ ነህ፤ የእግዚአብሔር አብ ቃል ነህ፤ ጥበብና ኃይል ነህ፤ ጸዳልና ብርሃን ነህ፤ የእውነት ፀሐይ ነህ፤ በኃጢአት ለሞትን
ለእኛ የትንሣኤያችንና የሕይወታችን ምንጭ ነህ፡፡”
ብጹዕ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይህ “አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ” የሚለው ቃል “እንደማይታይና እንደማይመረመር እንደ መለኰትና እንደ ትስብእት ተዋሕዶ ይመስላል፤ ስለዚህም ይህች ምሥጢር ለብዙዎች ጭንቅና
ጠባብ መንገድ ሆነች” በማለት “ኢየሱስ ፈርቶ ይህን ቃል ተናግሮታል” የሚሉትን መናፍቃን ይገስጻል፡፡ ከዚያም ጌታ እንዲህ ሲል ምን ማለቱ እንደሆነ ለማስረዳት እርሱ በጌታ ተገብቶ (ለንግግር ያመች ዘንድ) ይመልስልናል፡፡ እንዲህም ይላል፡- “ጥበብ ለራስዋ ቤትን ሠራች ተብሎ እንደተጻፈ ራሴ የተዋሐድኩትን ሥጋ እንደፈጠርኩ፤ በሞት የደከመ ሥጋዬን ሕያው አድርጌ ማሥነሣት እንደምችል፡- አይሁድ እናንተ ግብዞች ሰነፎች ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አነሣዋለሁ ብያቸው ነበርና፤ አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ሞት ከእኔ ይለፍ ያልኩት ሞትን በመፍራትና በመደንገጥ እዳልሆነ ለራስህ እወቅ፤ ተጠንቀቅ፤ ይህ ሥውር የሆነ የምሥጢር ቃል ነው እንጂ፡፡ ይህንንም ልመና እኔ በጥበብ ተናገርኩ፡፡ ይህች ቃል ሰይጣንን ጠብቃ የምታጠምድ ወጥመድ ናት፤ በእነዚህም ቃሎች ሰይጣን አጠምደው ዘንድ አለኝና፡፡
ተአምራትን እንዳደረግሁ፣ በሽተኞችን በእጄ ዳስሼ እንዳዳንኩ፣ አጋንንትም በቃሌ እንዳባረርኩ፣ የሸተተ በድን እንዳስነሣሁ፣ ባሕሩን ነፋሱን እንደገሠፅኩ፣ እነርሱም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ እንደታዘዙልኝ ሰይጣን አይቶኝ ነበር፡፡ ያደረግሁትን ይህን ተአምራት አይቶ እኔ የአምላክ ልጅ እንደሆንኩ አውቆ እኔም ብሰቀል እርሱ እንደሚጠፋ ወደ ሲዖልም ብወርድ የብረቱን መቆለፍያ ቀጥቅጬ እንደማጠፋ የብረቱን የናሐሱን መዝጊያ ሰብሬ ሁሉን ወደ ሰማይ እንደማሳርግ ልብ ብሎ አስተውሎ ፈርቶ እንዳሸሽ፣ እንዳይጠፋ፣ በመስቀል የሚደረገው
ምሥጢረ ድኅነት እንዳይቀር እንዳይቋረጥ ምን ላድርግ? አልኩ፡፡ ስለዚህ ራሴን ብልህ እንዳጠመደው ወጥመድ አድርጌ ፈርቶ ከሞት እንደሚደነግጥም አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ አልኩ፡፡ በእነዚህም የትሕትና ቃሎቼ ዕሩቅ ብእሲ (ሰው ብቻ) እመስለዋለሁ፤ ምሥጢረ ድኅነት የሚፈጸምበት መስቀል በምድር መካከል ይተከል ዘንድ ይቸኩላል፤ በእኔ ላይ የሚጠበብብኝ እየመሰለው እኔ ግን ለሰው ሁሉ ድኅነት ከእርሱ የሚደረግብኝ ሁሉ እታገሥ ዘንድ
አለኝ፡፡እርሱ የመጀመርያውን ሰው አዳምን ያጠፋው ዘንድ እጅግ ተተንኩሎ ተጠብቦበት ነበር፡፡ በተንኰል አነጋገር አዳምን እንደ ተጠበበበት እንግዲህ እኔ ሁሉን ለማዳን በይበልጥ ለምን አልጠበብበት? እንደዚሁ እኔም እርሱ ባመጣው ተንኰል ላጠምደው ትሕትናን በተመሉ ቃሎች ተጠበብኩበት፡፡ በመለኰታዊ
አነጋገርም ለሰይጣን አልተገለጽኩለትም፤ አባት ሆይ የሚቻል ከሆነ ይህ ጽዋ ሞት ከእኔ ይለፍ አልኩ እንጂ፡፡
ዓሣ አጥማጅ መቃጥኑን በመብል ሸፍኖ ወደ ባሕር ውስጥ በሚጥለው ጊዜ ሲስበው ለዓሣው እንደሚያስጐመጀው አንድ ጊዜም ሊጐርሰው ጕረሮውን እንደሚከፍት እንዲሁም እኔ መለኰቴን መብል አድርጌ ጣልኩለት፡፡ ለዘላለሙ
በማትመረመር ተዋሕዶ በሥጋዬ ውስጥ ያለ የመለኰት መቃጥንን ጣልኩለት፡፡
በሚያጠምድበት ላይ የተደረገው የሚጐረስ ትል (ወላፍ) ካልተንቀሳቀሰ ዓሣው መንጠቆውን ለመጕረስ አይጐመጅም፡፡ ስለዚህ ሥጋዬን እንደሚጐረስ (ወላፍ) ትል አድርጌ አሳየሁት፡፡ እኔ ሰው ያይደለሁ ትል ነኝ አልኩ፡፡ ይህን ሰምቶ በዚህ
በሥጋዬ ውስጥ ያለችን መቃጥን ሩጦ ሂዶ ይጐርስ ዘንድ፡፡እኔም በመቃጥኔ እስበዋለሁ፤ በኢዮብ መጽሐፍ ከይሲን በወጥመድ ትስበዋለህ ተብሎ የተጻፈውን ይፈጸም ዘንድ፡፡እኔም ፈርቶ እንደሚሸሽ ሰው ሆኜ ነፍሴ እስከ ሞት..

BY ርቱዓ ሃይማኖት


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/rituaH/2274

View MORE
Open in Telegram


ርቱዓ ሃይማኖት Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The SSE was the first modern stock exchange to open in China, with trading commencing in 1990. It has now grown to become the largest stock exchange in Asia and the third-largest in the world by market capitalization, which stood at RMB 50.6 trillion (US$7.8 trillion) as of September 2021. Stocks (both A-shares and B-shares), bonds, funds, and derivatives are traded on the exchange. The SEE has two trading boards, the Main Board and the Science and Technology Innovation Board, the latter more commonly known as the STAR Market. The Main Board mainly hosts large, well-established Chinese companies and lists both A-shares and B-shares.

Find Channels On Telegram?

Telegram is an aspiring new messaging app that’s taking the world by storm. The app is free, fast, and claims to be one of the safest messengers around. It allows people to connect easily, without any boundaries.You can use channels on Telegram, which are similar to Facebook pages. If you’re wondering how to find channels on Telegram, you’re in the right place. Keep reading and you’ll find out how. Also, you’ll learn more about channels, creating channels yourself, and the difference between private and public Telegram channels.

ርቱዓ ሃይማኖት from us


Telegram ርቱዓ ሃይማኖት
FROM USA