Telegram Group & Telegram Channel
"+" ነገረ ሃይማኖት "+"

"+" የሃይማኖት ትምህርት አጠር ተደርጎ የቀረበ "+"
ክፍል ፮

ቅዱስ ትውፊት...የቀጠለ

"+" ቅዱስ ትውፊት በዘመነ ብሉይ"+"
ትውፊት የምእመናን የዘወትር ሕይወት ነው፡፡በመኾኑም ትውፊት ሰው ከመፈጠሩ አንሥቶ የነበረ ነው፡፡እግዚአብሔር አዳምን፡- “መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ከርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለኽና” ብሎ ሲነግረው በጽሑፍ አልነበረም /ዘፍ.2፡17/፡፡አዳምና ሔዋን በገነት ለሰባት ዓመታት ሲኖሩ ይኽን ቅዱስ ትውፊት ጠብቀው ነው፡፡እግዚአብሔር ስይቅርና፥ሰይጣን እንኳን አዳምንና ሔዋንን ያታለላቸው በጽሑፍ አልነበረም፤ቅዱስ ባልኾነውና ከራሱ ካመነጨው ሐሰት እንጂ /ዘፍ.3/፡፡
ቅዱሱ ትውፊት በአቤል በኵል ሲቀጥል፥ዲያብሎስ ያስተዋወቀው ቅዱስ ያልኾነው ትውፊትም በቃየን በኵል ቀጥሏል፡፡የአቤልና የቃየን ትውፊት ግን በቃል እንዲኹም በግብር እንጂ በጽሑፍ የወረሱት አልነበረም /ዘፍ.4/፡፡
ኄኖክ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አድርጐ ሞትን ሳይቀምስ የሔደው በቅዱሱ ትውፊት ሥርዓት መሠረት ስለኖረ ነው፡፡ኖኅ በዚያ ኀጢአት በነገሠበት ዘመን ጻድቅ ኾኖ የተገኘው፥ባልተጻፈው በቅዱሱ ትውፊት እንጂ ከእግዚአብሔር በጽሑፍ ያገኘው ነገር ስለነበረ አይደለም፡፡ኖኅ ንጹሐንና ንጹሐን ያልኾኑትን እንስሳት ለይቶ ያወቀው በጽሑፍ አልነበረም፡፡አብርሃም እግዚአብሔርን አምኖ ከቤተሰቡ ተለይቶ ሲወጣም በጽሑፍ አይደለም፡፡ኖኅ፣አብርሃም፣ይስሐቅና ያዕቆብ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ይሠዉ ነበር፡፡ነገር ግን በጽሑፍ የተሰጣቸው መመሪያ ስለ ነበረ አይደለም፡፡ዮሴፍ በእግዚአብሔር ፊት ኀጢአት ማድረግ እንደማይገባ የተማረው ከቅዱስ ትውፊት በቃል እንጂ በጽሑፍ አይደለም፡፡በአጠቃላይ፥ሊቀ ነቢያት ሙሴ በ1500 ከክርስቶስ ልደት በፊት ተነሥቶ መጽሐፍ እስኪጽፍ ድረስ፥የእግዚአብሔር ሰዎች ከ4000 ዓመታት በላይ ሲመሩ የነበረው በጽሑፍ ሳይኾን በቃልና በተግባር በሚገለጠው ቅዱስ ትውፊት ነበር፡፡
ቅዱስ ትውፊት በዘመነ ሐዋርያት

"+" በዘመነ ሐዲስ ያለውን "+" ስንመለከትም፥ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሦስት ዓመት በላይ ሕዝቡን ደቀ መዛሙርቱን ያስተምር የነበረው በጽሑፍ አልነበረም፡፡ቅዱሳን ሐዋርያትም ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበሉት በወረቀት የተጻፈ ነገር አልነበረም፡፡ወንጌላውያን ከጌታ በቃል ተምረው በተግባር አይተው ኋላ የሚጽፉትን እየዞሩ አስተማሩ እንጂ አስቀድመው ጽፈው ጠቅሰው አላስተማሩም፡፡መጻሕፍት መጻፍ የተዠመሩት፥ቤተ ክርስቲያን በይፋ ከተመሠረተች ከ8 ዓመታት በኋላ ነው (ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት መዠመሪያ የተጻፈው መጽሐፍ የማቴዎስ ወንጌል ሲኾን ይኸውም በ41 ዓ.ም. ላይ ነው)፡፡እስከዚኽ ጊዜ ድረስ ቤተክርስቲያን ስትመራ የነበረው በቃልና በተግባራዊ ምልልስ ሲተላለፍ በነበረው ቅዱስ ትውፊት ነው፡፡በሌላ አገላለጽ ወንጌል ከመጻፉ በፊት፥ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን በቅዱስ ትውፊት ታውቋለች፡፡ወንጌልን ስትኖረው ነበረች፡፡
ከጌታችን ጋር ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከዋለበት እየዋሉ፣ካደረበት እያደሩ ሲያስተምር፣ሲጸልይ፣ሰዎችን ሲያጽናና፣ድውያነ ሥጋን በተአምራት ድውያነ ነፍስንም በትምህርት ሲፈውስ፣ሙታነ ሥጋንና ሙታነ ነፍስን ሕይወት ሲሰጣቸውዐ ይተዋል፤ሰምተዋል፡፡ሥርዓተ ብሉይን አሳልፎ ሥርዓተ ሐዲስን ሲሠራ ተመልክተዋል፡፡ነገር ግን ይኽን ኹሉ በትውፊት ለተላውያነ ሐዋርያት (Apostolic Fathers - ተላውያነ ሐዋርያት የሚባሉት ከሐዋርያት በቀጥታ የተማሩ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡) አስረከቡት እንጂ፥እነርሱ ራሳቸው እንደነገሩን ኹሉንም አልጻፉልንም፡፡የጻፉልን እጅግ ጥቂቱን ብቻ ነው /ዮሐ.21፡25፣ 1ኛዮሐ.1፡1/፡፡ “እንድጽፍላችኁ የምፈልገው ብዙ ነገር ሳለኝ በወረቀትና በቀለም ልጽፈው አልወድም፡፡ዳሩ ግን ደስታችኁ ፍጹም እንደኾነ ወደ እናንተ ልመጣ አፍለ አፍም ልነግራችኁ ተስፋ አደርጋለኹ” እንዲል /2ኛዮሐ.12፣ 3ኛዮሐ.13-14/፥እንኳንስ የጌታችን ይቅርና እነርሱ ራሳቸው ያስተማሩትን ትምህርት ያደረጉትንም ተአምራት በሙሉ አልጻፉልንም፡፡በጽሑፍ የጻፉትም ቢኾን በቃል ያስተማርዋቸውን ምእመናን እንዲጸኑበትና አንዳንድ ቢጽሐሳውያን (ሐሰተኛ ወንድሞች) እውነቱን አዛብተው መጻፍ ስለዠመሩ እንዳይታለሉ ለመጠበቅ ጥቂቱን ነው /ሉቃ.1፡2/፡፡ዋናው መሠረታቸው ግን ከላይ እንደገለጽነው በቃልና በተግባራዊ ሕይወት የተማሩት ትምህርት ነው፡፡
ስለዚኽ ቅዱስ ትውፊት እያልነው ያለ ነው፥እንዲኽ ዓይነቱን በገቢርና በቃል ዕለት ዕለት በቤተ ክርስቲያን ኹለንተናዊ ሕይወት የሚገለጠውና አንድ ጊዜ ለቅዱሳን የተሰጠውን ሃይማኖት ነው /ይሁዳ ቁ.3/፡፡ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይኽን በማስመልከት ሲናገር እንዲኽ ይላል፡- “ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠኁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለኹና” /1ኛቆሮ.11፡23/፡፡ከዚኽ የሐዋርያው ቃል እንደምንረዳው፥ቅዱስ ትውፊት ማለት አንዳንድ የተሳሳቱ ሰዎች እንደሚሉት የአሮጊቶች ተረትተረት ወይም ከሰው የተገኘው ርስ ሳይኾን መለኮታዊ ስጦታ እንደኾነ ነው፡፡ “ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችኁ ላያችኁ እናፍቃለኹና” /ሮሜ.1፡11/፡፡
#የቅዱስ ትውፊት ዋና ማዕከሉ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡በሌላ አገላለጽ ቅዱስ ትውፊት ወንጌል ነው፡፡በዘመነ ብሉይ ቢነገር ይወርዳል ይወለዳል ብሎ ነው፤በዘመነ ሐዲስ ቢነገር ደግሞ ወረደ ተወለደ ብሎ የምሥራችን ለትውልድ ኹሉ በቃልም፣በገቢርም፣በጽሑፍም የሚያውጅ ነው፤ቅዱስ ትውፊት፡፡ “ወንድሞች ሆይ! የሰበክኁላችኁን ደግሞም የተቀበላችኁትን በርሱም ደግሞ የቆማችኁበትን በርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለኹ፡፡በከንቱ ካላመናችኁ በቀር ብታስቡት በምን ቃል እንደሰበክኁላችኁ አሳስባችኋለኹ፡፡እኔ ደግሞ የተቀበልኹትን ከኹሉ በፊት ሰጠኋችኁ” እንዲል /1ኛቆሮ.15፡1/፡፡
ይቆየን
ይቀጥላል...
-----------------------------------
በየእለቱ መንፈስን የሚያለመልሙ አጥንትን የሚያጠነክሩ መንፈሳዊ ጽሁፎች እንዲደርሶት ይቀላቀሉን፡-
👉 @rituaH @rituaH
👉 @rituaH @rituaH
👉 @rituaH @rituaH



tg-me.com/rituaH/246
Create:
Last Update:

"+" ነገረ ሃይማኖት "+"

"+" የሃይማኖት ትምህርት አጠር ተደርጎ የቀረበ "+"
ክፍል ፮

ቅዱስ ትውፊት...የቀጠለ

"+" ቅዱስ ትውፊት በዘመነ ብሉይ"+"
ትውፊት የምእመናን የዘወትር ሕይወት ነው፡፡በመኾኑም ትውፊት ሰው ከመፈጠሩ አንሥቶ የነበረ ነው፡፡እግዚአብሔር አዳምን፡- “መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ከርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለኽና” ብሎ ሲነግረው በጽሑፍ አልነበረም /ዘፍ.2፡17/፡፡አዳምና ሔዋን በገነት ለሰባት ዓመታት ሲኖሩ ይኽን ቅዱስ ትውፊት ጠብቀው ነው፡፡እግዚአብሔር ስይቅርና፥ሰይጣን እንኳን አዳምንና ሔዋንን ያታለላቸው በጽሑፍ አልነበረም፤ቅዱስ ባልኾነውና ከራሱ ካመነጨው ሐሰት እንጂ /ዘፍ.3/፡፡
ቅዱሱ ትውፊት በአቤል በኵል ሲቀጥል፥ዲያብሎስ ያስተዋወቀው ቅዱስ ያልኾነው ትውፊትም በቃየን በኵል ቀጥሏል፡፡የአቤልና የቃየን ትውፊት ግን በቃል እንዲኹም በግብር እንጂ በጽሑፍ የወረሱት አልነበረም /ዘፍ.4/፡፡
ኄኖክ አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር አድርጐ ሞትን ሳይቀምስ የሔደው በቅዱሱ ትውፊት ሥርዓት መሠረት ስለኖረ ነው፡፡ኖኅ በዚያ ኀጢአት በነገሠበት ዘመን ጻድቅ ኾኖ የተገኘው፥ባልተጻፈው በቅዱሱ ትውፊት እንጂ ከእግዚአብሔር በጽሑፍ ያገኘው ነገር ስለነበረ አይደለም፡፡ኖኅ ንጹሐንና ንጹሐን ያልኾኑትን እንስሳት ለይቶ ያወቀው በጽሑፍ አልነበረም፡፡አብርሃም እግዚአብሔርን አምኖ ከቤተሰቡ ተለይቶ ሲወጣም በጽሑፍ አይደለም፡፡ኖኅ፣አብርሃም፣ይስሐቅና ያዕቆብ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ይሠዉ ነበር፡፡ነገር ግን በጽሑፍ የተሰጣቸው መመሪያ ስለ ነበረ አይደለም፡፡ዮሴፍ በእግዚአብሔር ፊት ኀጢአት ማድረግ እንደማይገባ የተማረው ከቅዱስ ትውፊት በቃል እንጂ በጽሑፍ አይደለም፡፡በአጠቃላይ፥ሊቀ ነቢያት ሙሴ በ1500 ከክርስቶስ ልደት በፊት ተነሥቶ መጽሐፍ እስኪጽፍ ድረስ፥የእግዚአብሔር ሰዎች ከ4000 ዓመታት በላይ ሲመሩ የነበረው በጽሑፍ ሳይኾን በቃልና በተግባር በሚገለጠው ቅዱስ ትውፊት ነበር፡፡
ቅዱስ ትውፊት በዘመነ ሐዋርያት

"+" በዘመነ ሐዲስ ያለውን "+" ስንመለከትም፥ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሦስት ዓመት በላይ ሕዝቡን ደቀ መዛሙርቱን ያስተምር የነበረው በጽሑፍ አልነበረም፡፡ቅዱሳን ሐዋርያትም ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበሉት በወረቀት የተጻፈ ነገር አልነበረም፡፡ወንጌላውያን ከጌታ በቃል ተምረው በተግባር አይተው ኋላ የሚጽፉትን እየዞሩ አስተማሩ እንጂ አስቀድመው ጽፈው ጠቅሰው አላስተማሩም፡፡መጻሕፍት መጻፍ የተዠመሩት፥ቤተ ክርስቲያን በይፋ ከተመሠረተች ከ8 ዓመታት በኋላ ነው (ከሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት መዠመሪያ የተጻፈው መጽሐፍ የማቴዎስ ወንጌል ሲኾን ይኸውም በ41 ዓ.ም. ላይ ነው)፡፡እስከዚኽ ጊዜ ድረስ ቤተክርስቲያን ስትመራ የነበረው በቃልና በተግባራዊ ምልልስ ሲተላለፍ በነበረው ቅዱስ ትውፊት ነው፡፡በሌላ አገላለጽ ወንጌል ከመጻፉ በፊት፥ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን በቅዱስ ትውፊት ታውቋለች፡፡ወንጌልን ስትኖረው ነበረች፡፡
ከጌታችን ጋር ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከዋለበት እየዋሉ፣ካደረበት እያደሩ ሲያስተምር፣ሲጸልይ፣ሰዎችን ሲያጽናና፣ድውያነ ሥጋን በተአምራት ድውያነ ነፍስንም በትምህርት ሲፈውስ፣ሙታነ ሥጋንና ሙታነ ነፍስን ሕይወት ሲሰጣቸውዐ ይተዋል፤ሰምተዋል፡፡ሥርዓተ ብሉይን አሳልፎ ሥርዓተ ሐዲስን ሲሠራ ተመልክተዋል፡፡ነገር ግን ይኽን ኹሉ በትውፊት ለተላውያነ ሐዋርያት (Apostolic Fathers - ተላውያነ ሐዋርያት የሚባሉት ከሐዋርያት በቀጥታ የተማሩ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡) አስረከቡት እንጂ፥እነርሱ ራሳቸው እንደነገሩን ኹሉንም አልጻፉልንም፡፡የጻፉልን እጅግ ጥቂቱን ብቻ ነው /ዮሐ.21፡25፣ 1ኛዮሐ.1፡1/፡፡ “እንድጽፍላችኁ የምፈልገው ብዙ ነገር ሳለኝ በወረቀትና በቀለም ልጽፈው አልወድም፡፡ዳሩ ግን ደስታችኁ ፍጹም እንደኾነ ወደ እናንተ ልመጣ አፍለ አፍም ልነግራችኁ ተስፋ አደርጋለኹ” እንዲል /2ኛዮሐ.12፣ 3ኛዮሐ.13-14/፥እንኳንስ የጌታችን ይቅርና እነርሱ ራሳቸው ያስተማሩትን ትምህርት ያደረጉትንም ተአምራት በሙሉ አልጻፉልንም፡፡በጽሑፍ የጻፉትም ቢኾን በቃል ያስተማርዋቸውን ምእመናን እንዲጸኑበትና አንዳንድ ቢጽሐሳውያን (ሐሰተኛ ወንድሞች) እውነቱን አዛብተው መጻፍ ስለዠመሩ እንዳይታለሉ ለመጠበቅ ጥቂቱን ነው /ሉቃ.1፡2/፡፡ዋናው መሠረታቸው ግን ከላይ እንደገለጽነው በቃልና በተግባራዊ ሕይወት የተማሩት ትምህርት ነው፡፡
ስለዚኽ ቅዱስ ትውፊት እያልነው ያለ ነው፥እንዲኽ ዓይነቱን በገቢርና በቃል ዕለት ዕለት በቤተ ክርስቲያን ኹለንተናዊ ሕይወት የሚገለጠውና አንድ ጊዜ ለቅዱሳን የተሰጠውን ሃይማኖት ነው /ይሁዳ ቁ.3/፡፡ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይኽን በማስመልከት ሲናገር እንዲኽ ይላል፡- “ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠኁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለኹና” /1ኛቆሮ.11፡23/፡፡ከዚኽ የሐዋርያው ቃል እንደምንረዳው፥ቅዱስ ትውፊት ማለት አንዳንድ የተሳሳቱ ሰዎች እንደሚሉት የአሮጊቶች ተረትተረት ወይም ከሰው የተገኘው ርስ ሳይኾን መለኮታዊ ስጦታ እንደኾነ ነው፡፡ “ትጸኑ ዘንድ መንፈሳዊ ስጦታ እንዳካፍላችኁ ላያችኁ እናፍቃለኹና” /ሮሜ.1፡11/፡፡
#የቅዱስ ትውፊት ዋና ማዕከሉ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡በሌላ አገላለጽ ቅዱስ ትውፊት ወንጌል ነው፡፡በዘመነ ብሉይ ቢነገር ይወርዳል ይወለዳል ብሎ ነው፤በዘመነ ሐዲስ ቢነገር ደግሞ ወረደ ተወለደ ብሎ የምሥራችን ለትውልድ ኹሉ በቃልም፣በገቢርም፣በጽሑፍም የሚያውጅ ነው፤ቅዱስ ትውፊት፡፡ “ወንድሞች ሆይ! የሰበክኁላችኁን ደግሞም የተቀበላችኁትን በርሱም ደግሞ የቆማችኁበትን በርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለኹ፡፡በከንቱ ካላመናችኁ በቀር ብታስቡት በምን ቃል እንደሰበክኁላችኁ አሳስባችኋለኹ፡፡እኔ ደግሞ የተቀበልኹትን ከኹሉ በፊት ሰጠኋችኁ” እንዲል /1ኛቆሮ.15፡1/፡፡
ይቆየን
ይቀጥላል...
-----------------------------------
በየእለቱ መንፈስን የሚያለመልሙ አጥንትን የሚያጠነክሩ መንፈሳዊ ጽሁፎች እንዲደርሶት ይቀላቀሉን፡-
👉 @rituaH @rituaH
👉 @rituaH @rituaH
👉 @rituaH @rituaH

BY ርቱዓ ሃይማኖት


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/rituaH/246

View MORE
Open in Telegram


ርቱዓ ሃይማኖት Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

For some time, Mr. Durov and a few dozen staffers had no fixed headquarters, but rather traveled the world, setting up shop in one city after another, he told the Journal in 2016. The company now has its operational base in Dubai, though it says it doesn’t keep servers there.Mr. Durov maintains a yearslong friendship from his VK days with actor and tech investor Jared Leto, with whom he shares an ascetic lifestyle that eschews meat and alcohol.

Telegram auto-delete message, expiring invites, and more

elegram is updating its messaging app with options for auto-deleting messages, expiring invite links, and new unlimited groups, the company shared in a blog post. Much like Signal, Telegram received a burst of new users in the confusion over WhatsApp’s privacy policy and now the company is adopting features that were already part of its competitors’ apps, features which offer more security and privacy. Auto-deleting messages were already possible in Telegram’s encrypted Secret Chats, but this new update for iOS and Android adds the option to make messages disappear in any kind of chat. Auto-delete can be enabled inside of chats, and set to delete either 24 hours or seven days after messages are sent. Auto-delete won’t remove every message though; if a message was sent before the feature was turned on, it’ll stick around. Telegram’s competitors have had similar features: WhatsApp introduced a feature in 2020 and Signal has had disappearing messages since at least 2016.

ርቱዓ ሃይማኖት from us


Telegram ርቱዓ ሃይማኖት
FROM USA