Telegram Group Search
Forwarded from Maraki News
2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መርሐግብር ይፋ ሆኗል፡፡

መርሐግብሩ ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች በወረቀት እና በበይነ መረብ ፈተናውን ለሚወስዱ ተፈታኞች እንደሚያገለግል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች፤ ከሐምሌ 9-11/2016 ዓ.ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ይሰጣል።

(መርሐግብሩ ከላይ ተያይዟል።)
☑️ @MarakiNews ☑️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና መቼ ይሰጣል?

የሪሚዲያል ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ብቻ እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር ከዚህ ቀደም መግለፁ ይታወሳል፡፡

የሪሚዲያል ፈተና ከሰኔ 1-7/2016 ዓ.ም ወይም ከሰኔ 8-14/2016 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ዘንድሮ ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሪሚዲያል ትምህርታቸውን ከታህሳስ ወር ጀምሮ እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡

ይሁን እንጂ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የሪሚዲያል ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም፡፡ ተማሪዎቹ ወደሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተዘዋውረው የሚማሩበት ዕድል እንዲሁም አማራጭ የፈተና ጊዜ የሚዘጋጅላቸው ስለመሆኑ በባህርዳር ዩኒቨርሲቲም ሆነ በትምህርት ሚኒስቴር የተባለ ነገር የለም፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ተፈታኞች መፈተኛ ይፋ ሆኗል፡፡ **

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በዚህም በበይነ መረብ ፈተናውን የሚወስዱ ተፈታኞች ከዚህ በታች በተገለፀው አድራሻ ብቻ ፈተናውን እንደሚወስዱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡

ስለሆነም ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ሁሉም ተፈታኞች በቂ ልምምድ ማድርግ አስፈላጊ

በመሆኑም ከዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 10/2016 ዓ.ም ጀምሮ የበይነ መረብ ተፈታኞች ባሉበት ሆነው ልምምድ ማድረግ የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ተፈታኞች ልምምድ ለማድረግ ከዚህ በፊት ለክልል/ከተማ አስተዳደር የተላከውን የይለፍ ቃል እና ስም (User Name and Password) ከየትምህርት ቤቶቻቸው ማግኘት ይችላሉ፡፡

በዚሁ መሠረት መጀመሪያ ወደ መፈተኛ ሲሰተሙ እንደገቡ የማይረሱትን የግላቸውን የይለፍ ቃል የሚቀይሩ ይሆናል፡፡

ተፈታኞች ከተደለደሉበት ክለስተር ውጪ ሲሰትሙን መጠቀም #እንደማይችሉ አገልግሎቱ አሳስቧል።

(ፈተናው የሚሰጥበት አድራሻ እና ተፈታኞቹ የሚገኙበት ክልል/ከተማ አስተዳደር ከላይ ተያይዟል።)
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በኦንላይን ለሚወስዱ የተዘጋጀ መለማመጃ

በተቀመጠው መመሪያ መሠረት የኦንላይን ፈተናውን ይለማመዱ።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናን ተማሪዎች በተማሩበት ትምህርት ቤት ለማስፈተን ፍላጎት ያለው ማንኛውም የመንግሥትም ሆነ የግል ትምህርት ቤት የተደራጀ የኮምፒውተር ላብራቶሪ ሊኖረው እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

በዚህም የትኛውም ትምህርት ቤት፦

1. ዴስክቶፕ ወይም ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች
2. የውስጥ ኔትዎርክ (LAN)
3. የኢንተርኔት መስመር ከበቂ ባንድዊድዝ ጋር (ከመፈተኛ የኮምፒውተር ብዛት አንጻር)
4. የመጠባበቂያ ኃይል (ጄኔሬተር) ማሟላትና ለትምህርት ቢሮዎች ማሳወቅ ይጠበቅበታል፡፡

በዚህም በቢሮዎች በኩል መሟላቱ ሲረጋግጥ የፈተና ማዕከል በመሆን ተማሪዎቹን ማስፈተን እንደሚችል ተገልጿል፡፡

ለፈተና የሚዘጋጁት ዴስክቶፕ እና ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ማሟላት ያለበቸው ዝቅተኛ ስፔስፊኬሽን፦

RAM ------------ 4GB or higher
Storage ---------250GB or higher
Processor Speed ----- 2.5GHZ or higher
Processors ----- Intel Core i3 or higher
OS ----------Windows 10
Browsers ---------Safe Exam Browser and other
Accessories ---------- Keyboards and Mouse for desktop computers.
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
#MoE

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተናን በኦንላይን የሚወስዱ ተፈታኞች በክላስተር የተዘጋጀ ማስፈንጠሪያ (URL) ላይ በመግባት እንዲለማመዱ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።

ከስር የተቀመጡት ማስፈንጠሪያዎች ተፈታኝ ተማሪዎች የሚለማመዱበት ሲሆን የፈተናው ዕለት ደግሞ መፈተኛ ይሆናሉ።

Note:

እስካሁን Username እና Password ያለገኛችሁ ተፈታኞች፤ ከትምህርት ቤት አስተባባሪዎች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ክላስተር አንድ

አዲስ አበባ፦ https://c2.exam.et
ሲዳማ ክልል፦ https://c2.exam.et
ትግራይ ክልል፦ https://c2.exam.et

ክላስተር ሁለት

ደቡብ ም/ኢ/ክልል፦ https://c3.exam.et
ጋምቤላ ክልል፦ https://c3.exam.et
አማራ ክልል፦ https://c3.exam.et

ክላስተር ሦስት

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፦ https://c4.exam.et
ሀረሪ ክልል፦ https://c4.exam.et
አፋር ክልል፦ https://c4.exam.et
ኦሮሚያ ክልል - 1
• አዳማ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• አጋሮ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• አምቦ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ አርሲ፦ https://c4.exam.et
• ምዕራብ አርሲ፦ https://c4.exam.et
• አሰላ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ባሌ፦ https://c4.exam.et
• ባቱ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቤሾፍቱ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቦረና፦ https://c4.exam.et
• ቡሌ ሆራ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቡኖ በደሌ፦ https://c4.exam.et
• ዶዶላ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ባሌ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ቦረና፦ https://c4.exam.et
• ጉጂ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ሐረርጌ፦ https://c4.exam.et
• ምዕራብ ሐረርጌ፦ https://c4.exam.et
• ሆለታ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ሆሮ ጉዱሩ፦ https://c4.exam.et
• ኢሉባቦር፦ https://c4.exam.et

ክላስተር አራት

ድሬዳዋ ከተማ፦ https://c5.exam.et
ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል - 2
• ጅማ፦ https://c5.exam.et
• ጅማ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ቄለም ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• ማያ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• መቱ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሞጆ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሞያሌ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ነጆ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ነቀምት ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሮቤ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሰንዳፋ በኬ፦ https://c5.exam.et
• ሻኪሶ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሻሸመኔ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሸገር ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሸኖ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ምስራቅ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• ሰሜን ሸዋ (ኦሮሚያ)፦ https://c5.exam.et
• ደቡብ ምዕራብ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• ምስራቅ ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ጉጂ፦ https://c5.exam.et
• ወሊሶ ከተማ፦ https://c5.exam.et

@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
ተማሪዎች በበይነ መረብ መፈተናቸው ስህተትን መቀነስን ጨምሮ በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።

የበይነ መረብ ፈተና ለስህተት በር አይከፍትም

የበይነ መረብ ፈተና አንድ ጥያቄ ሳይመልሱ ወደ ፈለጉት ጥያቄ በአንድ Click የመሔድ እንዲሁም ተመልሰው መስራት የሚፈልጉትን ጥያቄ Flag በማድረግ ተመልሶ የመስራት ዕድልን ይሰጣል።

ጊዜ ቆጣቢ ነው

በአንድ Click የፈተና ጥያቄን መልስ ለመስጠት ያስችላል። እንዲሁም ምን ያህል ደቂቃ እንደተጠቀሙ ከመፈተኛ ስክሪን ላይ ማየት ስለሚቻል ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ያስችላል።

የተሻሻለ የመረጃ ቋት አለው

የበይነ መረብ ፈተናዎች በቂ የፈተና መረጃዎችን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በማከማቸት ለተፈታኞች አመጣጥኖ ያቀርባል፡፡

የተሰሩ ጥያቄዎችን መልስ በፍጥነት በራሱ ይልካል

በፈተና ወቅት ጥያቄዎቹን ሰርተው ሳያጠናቀቁ የተሰጠው ደቂቃ ካለቀ የሰሩትን በጠቅላላ በራሱ በፍጥነት ይልካል።

ፈጣን ግብረ መልስ ይሰጣል

በበይነ መረብ ፈተናዎች ሲሰጡ ውጤታቸው ከሌላው ጊዜ በተለየ ፈጥኖ የመታወቅ ዕድል ይሰጣል።

ተማሪዎች በቤታቸው እያደሩ እንዲፈተኑ ዕድል ይሰጣል

ትምህርት ቤቶች የተደራጀ የኮምፒውተር ቤተሙከራ ካላቸውና የመፈተኛ ክላስተር ለመሆን አስፈላጊውን መስፈርቶች ማሟላታቸው ከተረጋገጠ ተማሪዎች በተማሩበት ትምህርት ቤት ሆነው እንዲፈተኑ ዕድል ይፈጥራል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
በአዲስ አበባ የስምንተኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም ይሰጣል።

በተመሳሳይ የስድስተኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 12 እስከ 14/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ፈተናዎቹን ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

በአዲስ አበባ የስምንተኛ ክፍል ፈተናውን 86,671 ተማሪዎች እንዲሁም የስድስተኛ ክፍል ፈተናውን 86,217 ተማሪዎች እንደሚወስዱ በቢሮው የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክተር ዲናኦል ጫላ ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡

ከተፈቀዱ የፈተና ቁሳቁሶች ውጪ፣ ዲጂታል ሰዓትን ጨምሮ ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎችን ይዞ ወደ ፈተና መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የዘንድሮ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 701 ሺሕ 489 ተማሪዎች እንደሚወስዱ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ዘንድሮ በሚሰጠው ድብልቅ የ12ኛ ክፍል መልቂያያ ፈተና ላይ መግለጫ ሰጥቷል።

ፈተናው በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ የተገለጸ ሲሆን እንደሀገር የአቅም ችግር በመኖሩ ምክንያት ፈተናውን ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት አለመቻሉን ተገልጿል።

በመሆኑም የዘንድሮ የፈተና አሰጣጥ በትምህርት ቤቶች አቅም የሚወሰን ይሆናል ነው የተባለው።

የኦንላይን ፈተና ውጤትን በቶሎ በማሳወቅ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ ፈተናን ለመስጠት፣ ስህተትን በመቀነስ እና በሌሎችም ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ላይ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተመላክቷል።

ከኢንተርኔት እና የመብራት መቆራረጥ ጋር ተያይዞ ያሉ ስጋቶችን ለመቀነስ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በትብብር በመስራትና የመብራት መቆራረጥ እንዳይኖር ጀነሬተሮችን በፈተና መስጫ ተቋማት ማሟላት መቻሉ ተገልጿል።

ተማሪዎች ለኦንላይን ፈተና የመፈተኛ ኮምፒውተር እንዲያመጡ ተገደዋል የሚባለው ወሬ እውነትነት የሌለውና ከትምህርት ሚኒስቴር እውቅና ውጪ እንደሆነም በመግለጫው ተነስቷል።
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
የ8ኛ ክፍል ክልላዊ/ከተማ አቀፍ ፈተና ዛሬ ሰኔ 5/2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል።

ፈተናው በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች በመሠጠት ላይ ነው።

የፀጥታ ችግር ያለባቸው አካባቢዎች በተለይም በምዕራብ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች ፈተናው እየተሠጠ አይደለም። በምስራቅ ጎጃም ዞን ደግሞ በከፊል እየተሰጠ ነው።

ከዓመታት በኋላ ባለፈው ዓመት በድጋሜ መሠጠት የጀመረው የ6ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 12 እስከ 14/2016 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡
@Timihirt_Minister
@Timihirt_Minister
Forwarded from quality botton
⭕️ ሰላም ሰላም ተማሪዎች አዲስ መረጃ ከትምህርት ሚንስቴር ወጥቷል :: ለሁሉም የኢትዮጵያ ተማሪዎች አንድ የቴሌግራም ቻናል ተከፍቷል :: ሁሉም መረጃ በዛው ቻናል በኩል ለተማሪዎች ይሰራጫል ተብሏል :: ስለዚህ ሁላችሁም ፈጥናችሁ ተቀላቀሉ ::

📥ቻናሉን ለመቀላቀል 👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/addlist/LvHoNVvVJnJlYmRk
Forwarded from Quality Button
🔴 ሰበር ዜና ዛሬ ትምህርት ሚኒሰትር ያወጣው አዲስ ያልተጠበቀ መግለጫ   ‼️

ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ ከስር open ሚለውን ይጫኑ 👇👇
2024/06/16 21:49:07
Back to Top
HTML Embed Code: