TIKVAH-ETHIOPIA
“ ... 1,500 ካ/ሜ ግሪን ኤርያውን 12 ወጣቶች መጥተው አጠሩት ” - ቅሬታ አቅራቢዎች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አካባቢ በሚገኘውና በ1979 ዓ/ም ለ “ አዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ቤት ሥራ ማኀበር ” ተሰጥቶ ነበር የተባለ 1500 ካ/ሜ መሬት የመከነ ማስረጃ ባቀረቡ ሰዎች መታጠሩን ማኅበሩ ገለጸ። ቦታው በ1979 ዓ/ም ለማኀበሩ ከተሰጠ ጊዜ…
#Update
በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ጀርመን አደባባይ አካባቢ የሚገኘውና በ1979 ዓ/ም ለ “ አዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ቤት ሥራ ማኀበር ” ተሰጥቶ ነበር የተባለ 1,500 ካ/ሜ መናፈሻ መሬት የመከነ ማስረጃ ባቀረቡ ሰዎች መታጠሩን ማኀበሩ መግለጹን መረጃ አጋርተናችሁ ነበር።
ከዚያ ወዲህ ምን ተፈጠረ ?
የማኀበሩ አባላት ትላንት (ዓርብ ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ/ም) ከምሽቱ 3 ገደማ በሰጡት ቃል፣ “ ጨለማን ተገን አድርገው የግንባታ እቃዎች አስገብተዋል ” ብለዋል።
“ ደንቦች ቢባል፣ ሰላምና ጸጥታ ቢባል ምንም ሊፈይድልን አልቻለም። አሁን ለሕይወታችን ሁሉ እየፈራን ነው። የ70 ዓመት አረጋዊ ገፍትረው ጣሉ አታስገቡም ብሎ ሲከለክላቸው ” ሲሉም ወቅሰዋል።
የጸጥታ አካላት መፍትሄ እንዲሰጧቸው ቢጠይቁም ፈቃደኛ እንዳልሆኑላቸው ገልጸው፣ “ የለፋንበት፣ ወጪ ያወጣንበት ቦታ ነው። ኃላፊነት የጎደለው ነገር እየተሰራ ነው ” ብለዋል።
ታጠረ የተባለው ግሪን ኤሪያ ጀርመን አደባባይ አካባቢ የተባበሩት ነዳጅ ማደያ ወደ ውስጥ 300 ሜትር ገባ ብሎ መሆኑን አመላክተዋል።
ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ የጠየቅናቸው አንድ የደንብ ማስከበር አካል፣ ጉዳዩን በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ምላሽ ለመስጠት የማይመች ቦታ ላይ እንደሆኑና ከቆይታ በኋላ እንዲደወል ቢጠይቁም ፣ በድጋሚ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ጀርመን አደባባይ አካባቢ የሚገኘውና በ1979 ዓ/ም ለ “ አዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ቤት ሥራ ማኀበር ” ተሰጥቶ ነበር የተባለ 1,500 ካ/ሜ መናፈሻ መሬት የመከነ ማስረጃ ባቀረቡ ሰዎች መታጠሩን ማኀበሩ መግለጹን መረጃ አጋርተናችሁ ነበር።
ከዚያ ወዲህ ምን ተፈጠረ ?
የማኀበሩ አባላት ትላንት (ዓርብ ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ/ም) ከምሽቱ 3 ገደማ በሰጡት ቃል፣ “ ጨለማን ተገን አድርገው የግንባታ እቃዎች አስገብተዋል ” ብለዋል።
“ ደንቦች ቢባል፣ ሰላምና ጸጥታ ቢባል ምንም ሊፈይድልን አልቻለም። አሁን ለሕይወታችን ሁሉ እየፈራን ነው። የ70 ዓመት አረጋዊ ገፍትረው ጣሉ አታስገቡም ብሎ ሲከለክላቸው ” ሲሉም ወቅሰዋል።
የጸጥታ አካላት መፍትሄ እንዲሰጧቸው ቢጠይቁም ፈቃደኛ እንዳልሆኑላቸው ገልጸው፣ “ የለፋንበት፣ ወጪ ያወጣንበት ቦታ ነው። ኃላፊነት የጎደለው ነገር እየተሰራ ነው ” ብለዋል።
ታጠረ የተባለው ግሪን ኤሪያ ጀርመን አደባባይ አካባቢ የተባበሩት ነዳጅ ማደያ ወደ ውስጥ 300 ሜትር ገባ ብሎ መሆኑን አመላክተዋል።
ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ የጠየቅናቸው አንድ የደንብ ማስከበር አካል፣ ጉዳዩን በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ምላሽ ለመስጠት የማይመች ቦታ ላይ እንደሆኑና ከቆይታ በኋላ እንዲደወል ቢጠይቁም ፣ በድጋሚ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
tg-me.com/tikvahethiopia/87259
Create:
Last Update:
Last Update:
#Update
በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ጀርመን አደባባይ አካባቢ የሚገኘውና በ1979 ዓ/ም ለ “ አዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ቤት ሥራ ማኀበር ” ተሰጥቶ ነበር የተባለ 1,500 ካ/ሜ መናፈሻ መሬት የመከነ ማስረጃ ባቀረቡ ሰዎች መታጠሩን ማኀበሩ መግለጹን መረጃ አጋርተናችሁ ነበር።
ከዚያ ወዲህ ምን ተፈጠረ ?
የማኀበሩ አባላት ትላንት (ዓርብ ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ/ም) ከምሽቱ 3 ገደማ በሰጡት ቃል፣ “ ጨለማን ተገን አድርገው የግንባታ እቃዎች አስገብተዋል ” ብለዋል።
“ ደንቦች ቢባል፣ ሰላምና ጸጥታ ቢባል ምንም ሊፈይድልን አልቻለም። አሁን ለሕይወታችን ሁሉ እየፈራን ነው። የ70 ዓመት አረጋዊ ገፍትረው ጣሉ አታስገቡም ብሎ ሲከለክላቸው ” ሲሉም ወቅሰዋል።
የጸጥታ አካላት መፍትሄ እንዲሰጧቸው ቢጠይቁም ፈቃደኛ እንዳልሆኑላቸው ገልጸው፣ “ የለፋንበት፣ ወጪ ያወጣንበት ቦታ ነው። ኃላፊነት የጎደለው ነገር እየተሰራ ነው ” ብለዋል።
ታጠረ የተባለው ግሪን ኤሪያ ጀርመን አደባባይ አካባቢ የተባበሩት ነዳጅ ማደያ ወደ ውስጥ 300 ሜትር ገባ ብሎ መሆኑን አመላክተዋል።
ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ የጠየቅናቸው አንድ የደንብ ማስከበር አካል፣ ጉዳዩን በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ምላሽ ለመስጠት የማይመች ቦታ ላይ እንደሆኑና ከቆይታ በኋላ እንዲደወል ቢጠይቁም ፣ በድጋሚ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ጀርመን አደባባይ አካባቢ የሚገኘውና በ1979 ዓ/ም ለ “ አዲስ አበባ 100ኛ ዓመት ቤት ሥራ ማኀበር ” ተሰጥቶ ነበር የተባለ 1,500 ካ/ሜ መናፈሻ መሬት የመከነ ማስረጃ ባቀረቡ ሰዎች መታጠሩን ማኀበሩ መግለጹን መረጃ አጋርተናችሁ ነበር።
ከዚያ ወዲህ ምን ተፈጠረ ?
የማኀበሩ አባላት ትላንት (ዓርብ ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ/ም) ከምሽቱ 3 ገደማ በሰጡት ቃል፣ “ ጨለማን ተገን አድርገው የግንባታ እቃዎች አስገብተዋል ” ብለዋል።
“ ደንቦች ቢባል፣ ሰላምና ጸጥታ ቢባል ምንም ሊፈይድልን አልቻለም። አሁን ለሕይወታችን ሁሉ እየፈራን ነው። የ70 ዓመት አረጋዊ ገፍትረው ጣሉ አታስገቡም ብሎ ሲከለክላቸው ” ሲሉም ወቅሰዋል።
የጸጥታ አካላት መፍትሄ እንዲሰጧቸው ቢጠይቁም ፈቃደኛ እንዳልሆኑላቸው ገልጸው፣ “ የለፋንበት፣ ወጪ ያወጣንበት ቦታ ነው። ኃላፊነት የጎደለው ነገር እየተሰራ ነው ” ብለዋል።
ታጠረ የተባለው ግሪን ኤሪያ ጀርመን አደባባይ አካባቢ የተባበሩት ነዳጅ ማደያ ወደ ውስጥ 300 ሜትር ገባ ብሎ መሆኑን አመላክተዋል።
ለቅሬታው ምላሽ እንዲሰጡ የጠየቅናቸው አንድ የደንብ ማስከበር አካል፣ ጉዳዩን በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ምላሽ ለመስጠት የማይመች ቦታ ላይ እንደሆኑና ከቆይታ በኋላ እንዲደወል ቢጠይቁም ፣ በድጋሚ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
BY TIKVAH-ETHIOPIA
Share with your friend now:
tg-me.com/tikvahethiopia/87259