Telegram Group & Telegram Channel
📍‹‹በቂ›› ስንት ነው? (How much is enough!

🔷ጊዜ በቂ አይደለም፡፡ ሕይወት በቂ አይደለም፡፡ ዕውቀት በቂ አይደለም፡፡ ገንዘብ በቂ አይደለም፡፡ ደስታችንም በቂ የሚባል ደረጃ ላይ አልደረሰም፡፡  ወዳጅነትም ሆነ ዝምድና በቂ ነው አይባልም፡፡ የዚህ ዓለም ፍቅርም በቂ አይደለም፡፡ አብዛኛው የዘንድሮ ወዳጅነትም ሆነ ዝምድና በወረት ያጠረ እንጂ ዘላቂ አይደለም፡፡

🔶‹‹በቂ›› የሚለውን ቃል በሁለት ፊደል ብቻ መወከል ፍትሐዊ አይደለም፡፡ በቂ እንደየሰዉ መስፈሪያ ከፍም ዝቅም ይላል እንጂ እቅጩን ሆኖ አያውቅም፡፡ የምንም ነገርን መስፈሪያ በግምትና በስምምነት ወይም ከዚህ እስከዚህ የምንለው እንጂ በራሱ በቂ የሆነ አይደለም፡፡ በቂ የመጠን ጉዳይ ነው፡፡ መጠንን መመጠን ደግሞ የመጣኙ ፋንታ ነው፡፡ አንዱ ከመጠኑ አስበልጦ አሙልቶ ሲያፈሰው ሌላው ደግሞ ከመጠኑ በታች አድርጎ ያጎድለዋል፡፡ በቂን የሚያበቃው በአዕምሮ የበቃው ብቻ ነው፡፡

♦️ኑሮ ያልበቃን፣ ገንዘብ ያልበቃን፣ ዕውቀት ያልበቃን፣ ደግነት ያልበቃን፣ ፍቅር ያልበቃን የምንፈልገውን የእውነት ስለፈለግነው ሳይሆን ሌሎች ስለፈለጉት ብቻ እኛም ሰለፈለግነው ነው፡፡ አዎ ብዙዎቻችን የምንፈልገውን የማናውቀው ፍላጎታችን የተመሰረተው በሌሎች ፍላጎት ላይ በመሆኑ ነው፡፡

🔹በእርግጥ መሠረታዊው የሰው ልጅ ፍላጎት ተመሳሳይ ቢሆንም አፈላለጋችንና ፈልገን የምናመጣበት መንገድ የተለያየ ነው፡፡ የሆድ ጉዳያችን፣ ርሃባችን፣ ጥማችን ስሜቱ የጋራ ቢሆንም መንፈሳዊ ረሃባችንና ጥማታችን፣ እንዲሁም አስተሳሰባችንና ግባችን የተለያየ ነው፡፡ የብቃት መለኪያችንም የሚለየው ‹‹በቂ›› የሚለው መስፈሪያ እንደየአስተሳሰባችን አንድ ወጥ ባለመሆኑ ነው፡፡

ሮበርት ስኪደልስኪ የተባለ ፀሐፊ እንዲህ ይላል፡-
‹‹የምንፈልገው ከመጠን በላይ ስለሆነ አይደለም፡፡ ነገር ግን እኛ የምንፈልገው ሌሎች ከሚፈልጉት የበለጠ እንዲሆን ስለምንሻ ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ሌሎችም በተመሳሳይ ሁኔታ የሚፈልጉት እኛ ከምንፈልገው በላይ እንዲሆን ነው፡፡ ይሄም መጨረሻ ወደሌለውና አሸናፊው ወደማይለየው ፉክክር ውስጥ ከትቶናል፡

🔶በመጠን ኑሩ!! ከዕውቀት ሁሉ ዕውቀት ፦ መጠንን ማወቅና ‹‹በቂ››ን መገንዘብ ዋነኛ የህይወት ጉዳይ  ነው፡፡ ከመጠን ያነሰም ሆነ የበዛ ጣጣ አለው፡፡ ከበቂ በላይም ሆነ ከበቂ በታች ሁሉቱም አይጠቅሙም፡፡ በቂ መካከለኛው ነጥብ ነው፡፡ በቂ መጠን ነው፤ መጠን ደግሞ ማስተዋል ነው፡፡

🔷ወዳጄ ሆይ የብልፅግና ዋነኛ ግብ መሆን ያለበት እንደገብጋቦች ማከማቸት ሳይሆን ሕይወትን በምድር ላይ በደስታ ማኖር ነው ። አንድ ሰው ሀብታም ነው ሚባለው ደሞ ባለው ነገር ሲረካና በቃኝ ሲያውቅ ብቻ ነው። አንተም መጠንህን እወቅና ብቃትህን ተጎናፀፍ፡፡ የምትፈልገውን ሁሉ ለማሟላት ስትል ዕድሜህን አትጨርስ፡፡ ከምትፈልገው ይልቅ የሚያስፈልግህን ምረጥ፡፡ ማግበስበስን ሳይሆን መመጠንን ልመድ፡፡ የ‹‹በቂ›› መስፈሪያህን በቅተህ አግኘው፡፡

        በቂ ሕይወትን ተመኘን!
           ውብ ቅዳሜ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot



tg-me.com/EthioHumanity/7150
Create:
Last Update:

📍‹‹በቂ›› ስንት ነው? (How much is enough!

🔷ጊዜ በቂ አይደለም፡፡ ሕይወት በቂ አይደለም፡፡ ዕውቀት በቂ አይደለም፡፡ ገንዘብ በቂ አይደለም፡፡ ደስታችንም በቂ የሚባል ደረጃ ላይ አልደረሰም፡፡  ወዳጅነትም ሆነ ዝምድና በቂ ነው አይባልም፡፡ የዚህ ዓለም ፍቅርም በቂ አይደለም፡፡ አብዛኛው የዘንድሮ ወዳጅነትም ሆነ ዝምድና በወረት ያጠረ እንጂ ዘላቂ አይደለም፡፡

🔶‹‹በቂ›› የሚለውን ቃል በሁለት ፊደል ብቻ መወከል ፍትሐዊ አይደለም፡፡ በቂ እንደየሰዉ መስፈሪያ ከፍም ዝቅም ይላል እንጂ እቅጩን ሆኖ አያውቅም፡፡ የምንም ነገርን መስፈሪያ በግምትና በስምምነት ወይም ከዚህ እስከዚህ የምንለው እንጂ በራሱ በቂ የሆነ አይደለም፡፡ በቂ የመጠን ጉዳይ ነው፡፡ መጠንን መመጠን ደግሞ የመጣኙ ፋንታ ነው፡፡ አንዱ ከመጠኑ አስበልጦ አሙልቶ ሲያፈሰው ሌላው ደግሞ ከመጠኑ በታች አድርጎ ያጎድለዋል፡፡ በቂን የሚያበቃው በአዕምሮ የበቃው ብቻ ነው፡፡

♦️ኑሮ ያልበቃን፣ ገንዘብ ያልበቃን፣ ዕውቀት ያልበቃን፣ ደግነት ያልበቃን፣ ፍቅር ያልበቃን የምንፈልገውን የእውነት ስለፈለግነው ሳይሆን ሌሎች ስለፈለጉት ብቻ እኛም ሰለፈለግነው ነው፡፡ አዎ ብዙዎቻችን የምንፈልገውን የማናውቀው ፍላጎታችን የተመሰረተው በሌሎች ፍላጎት ላይ በመሆኑ ነው፡፡

🔹በእርግጥ መሠረታዊው የሰው ልጅ ፍላጎት ተመሳሳይ ቢሆንም አፈላለጋችንና ፈልገን የምናመጣበት መንገድ የተለያየ ነው፡፡ የሆድ ጉዳያችን፣ ርሃባችን፣ ጥማችን ስሜቱ የጋራ ቢሆንም መንፈሳዊ ረሃባችንና ጥማታችን፣ እንዲሁም አስተሳሰባችንና ግባችን የተለያየ ነው፡፡ የብቃት መለኪያችንም የሚለየው ‹‹በቂ›› የሚለው መስፈሪያ እንደየአስተሳሰባችን አንድ ወጥ ባለመሆኑ ነው፡፡

ሮበርት ስኪደልስኪ የተባለ ፀሐፊ እንዲህ ይላል፡-
‹‹የምንፈልገው ከመጠን በላይ ስለሆነ አይደለም፡፡ ነገር ግን እኛ የምንፈልገው ሌሎች ከሚፈልጉት የበለጠ እንዲሆን ስለምንሻ ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ሌሎችም በተመሳሳይ ሁኔታ የሚፈልጉት እኛ ከምንፈልገው በላይ እንዲሆን ነው፡፡ ይሄም መጨረሻ ወደሌለውና አሸናፊው ወደማይለየው ፉክክር ውስጥ ከትቶናል፡

🔶በመጠን ኑሩ!! ከዕውቀት ሁሉ ዕውቀት ፦ መጠንን ማወቅና ‹‹በቂ››ን መገንዘብ ዋነኛ የህይወት ጉዳይ  ነው፡፡ ከመጠን ያነሰም ሆነ የበዛ ጣጣ አለው፡፡ ከበቂ በላይም ሆነ ከበቂ በታች ሁሉቱም አይጠቅሙም፡፡ በቂ መካከለኛው ነጥብ ነው፡፡ በቂ መጠን ነው፤ መጠን ደግሞ ማስተዋል ነው፡፡

🔷ወዳጄ ሆይ የብልፅግና ዋነኛ ግብ መሆን ያለበት እንደገብጋቦች ማከማቸት ሳይሆን ሕይወትን በምድር ላይ በደስታ ማኖር ነው ። አንድ ሰው ሀብታም ነው ሚባለው ደሞ ባለው ነገር ሲረካና በቃኝ ሲያውቅ ብቻ ነው። አንተም መጠንህን እወቅና ብቃትህን ተጎናፀፍ፡፡ የምትፈልገውን ሁሉ ለማሟላት ስትል ዕድሜህን አትጨርስ፡፡ ከምትፈልገው ይልቅ የሚያስፈልግህን ምረጥ፡፡ ማግበስበስን ሳይሆን መመጠንን ልመድ፡፡ የ‹‹በቂ›› መስፈሪያህን በቅተህ አግኘው፡፡

        በቂ ሕይወትን ተመኘን!
           ውብ ቅዳሜ❤️

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot

BY ስብዕናችን #Humanity


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/EthioHumanity/7150

View MORE
Open in Telegram


ስብዕናችን Humanity Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram announces Anonymous Admins

The cloud-based messaging platform is also adding Anonymous Group Admins feature. As per Telegram, this feature is being introduced for safer protests. As per the Telegram blog post, users can “Toggle Remain Anonymous in Admin rights to enable Batman mode. The anonymized admin will be hidden in the list of group members, and their messages in the chat will be signed with the group name, similar to channel posts.”

What is Telegram Possible Future Strategies?

Cryptoassets enthusiasts use this application for their trade activities, and they may make donations for this cause.If somehow Telegram do run out of money to sustain themselves they will probably introduce some features that will not hinder the rudimentary principle of Telegram but provide users with enhanced and enriched experience. This could be similar to features where characters can be customized in a game which directly do not affect the in-game strategies but add to the experience.

ስብዕናችን Humanity from ua


Telegram ስብዕናችን #Humanity
FROM USA