Telegram Group & Telegram Channel
"ብእሲት ዘኃደገት ቀሱታ ⇨  መቅጃዋን የተወችው ሴት"
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°•◇•°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°

ከሰማርያ መንደር ከወጡ ደገኛ የቅዱስ መጽሐፍ ባለ ታሪኮች ደጉ ሳምራዊ እና ደጓ ሳምራዊት ጎልተው ይጠቀሳሉ። በመጽሐፈ ስንክሳራችንም መጋቢት ፭ ቀን የስሟ ትርጓሜ ሰላምና ሥምረት የሆነ ቅድስት አውዶክስያ የምትባል አንዲት ሳምራዊት ሴት በታላቅ ተጋድሎ ማረፏን ይነግረናል።

የደጉ ሳምራዊ ታሪክ ለትምህርት ምሳሌ ነው [የሉቃስ ወንጌል 10:33] ፤ የእርሷ ግን በአምላካችን ዘመነ ሥጋዌ የተፈጸመ አስተማሪ ኩነት አዝሏል።  መኖርያዋ ሲካር ነው  ታላቋ «ሳምራዊት» ሴት [የዮሐንስ ወንጌል 4:7]

ይህች ሴት መድኃኔዓለም የሚለውን ስም በወንጌል ቀድሞ በሰው አፍ እንዲጠራ በስብከቷ ምክንያት የሆነች የከበረች ምስክር ናት።

ሰማዕነ ወጠየቅነ ከመ ዝንቱ ውእቱ ክርስቶስ በአማን #መድኅነ_ዓለም
            ↳  ይህ በእውነት የዓለሙ መድኅን ክርስቶስ እንደሆነ ሰምተናል ተረድተናል

ወንጌል ስለመጨረሻው ተልእኮዋ ሲነግረን እንዲህ ይተርከዋል፦
            ☞  "ወኃደገት ቀሱታ ይእቲ ብእሲት ወአተወት ሀገረ ወነገረት ለሰብአ ቤታ ።  ወትቤ ንዑ ትርአዩ ብእሲ ዘነገረኒ ኵሎ ዘገበርኩ እንዳዒ ለእመኑ ውእቱ ክርስቶስ "
            ↳ ሴቲቱም ማድጋዋን ትታ ወደ ሀገር ገብታ ለቤተሰቦቿ ነገረች ። የሠራሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ታዩ ዘንድ ኑ፡ ክርስቶስም እንደሆነ እንጃ አለች ።

መምህረ ዓለም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሐዋርያዊ ሥራዋን በላቀ መንገድ ሲነግረን "ሌሎቹ ሐዋርያት መረባቸውን ጥለው ሲከተሉት እርሷም በሐዋርያነቷ መቅጃዋን ጥላ ተከተለችው ከእነርሱ እነ ፊልጶስ እነ እንድርያስ ሌላውንም እንዲከተለው በአንድ በሁለቱ ፊት ሲመሰክሩ እርሷ ግን መንደሩ ሁሉ እንዲከተለው ሰበከች" አለን ፤ አቤት መታደሏ!


ሳምራዊቷ ሴት ማናት?
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
ከ፹፩ዱ ቅዱስ መጽሐፋችን በተጨማሪ በሌሎች የትውፊት መጻሕፍት አዋልድም ጭምር በተለያዩ  መጠሪያዎች ተጠርታ  ከተጨማሪ ታሪኮች ጋር እናገኛታለን።

       ቀደምት የግሪክ ክታቦች አምስት እኅቶችና ሁለት ልጆች የነበሯት በሰማዕትነት ክብር ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስን ተከትላ የጽድቅ ምስክር ሆና ያረፈች እንደሆነች አስረድተው ስሟ የከበረ ታላቋ ሰማዒት (ምስክር) ሳምራዊቷ ቅድስት #ፎጢን (holy and glorious Great-martyr #Photine of Samaria) እያሉ ገልጠዋታል።

የ’ኛውም ተአምረ ኢየሱስ  ደግሞ ስሟን በመጥቀስ የታሪኳን ፍጻሜ እንዲህ አስቀምጦልናል ፦

             ☞ "ወሶበ ሰምአት ብእሲት ሳምራዊት ዘስማ #ብርፍሴንያ ነገሮ ለእግዚእ ኢየሱስ ሖረት ወዜነወት ለሰብእ እንዘ ትብል ንዑ ኀቤየ አርእየክሙ ብእሴ ዘየአምር ኅቡአተ እስመ ውእቱ ዜነወኒ ግብርየ ዘአኀብኦ እም ሰብእ"
            ↳   ይህችም ብርፍሴንያ የምትባል ሳምራዊት ሴት የጌታ ኢየሱስን ነገር በሰማች ጊዜ ወደሀገር ገብታ ለሰዎቹ ሁሉ በሆዴ ውስጥ ያለውን ምሥጢር ሁሉ የሚናገር ሰው አሳያችሁ ዘንድ ኑ እኔ ከሰው ደብቄ የያዝኩትን ምሥጢር ነግሮኛልና አለቻቸው ።


        ሳምራዊቷ ሴት ቅድስት ብርፍሴንያ መቅጃዋን ጥላ ወደ መንደር ተመልሳ በሀገሩ ያሉትን ሁሉ ወደ ድኅነት ወደ ሕይወት ውኃ ጠራች የበረከት ቃል ከአንደበቷ እየተቀዳ አፏ የሕይወት ውኃ ምንጭ ሆነ።  "ያደረግሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ኑና እዩ" ትላለች። ጠቢቡ “የጻድቅ አፍ የሕይወት ምንጭ ናት፤ የኀጥኣንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል።”  【ምሳሌ 10፥11】

         ለሲካር መንደር ሕዝብ ቅድስት ብርፍሴንያ ለሕይወት ውኃ ክርስቶስ "መቅጃቸው" ናት። እነርሱ ግን የሴት ደቀ መዝሙር ለመባል አፍረው በእርሷ ስብከት ተከትለው ቢያምኑበትም የእርሷን ድርሻ ግን እንዲህ እያሉ ካዱ ፦

             ☞ "ወይቤልዋ ለይእቲ ብእሲት አኮ እንከ በነገረ ዚአኪ ዘአመነ ቦቱ አላ ለሊነ ሰማዕነ ወጠየቅነ ከመ ዝንቱ ውእቱ ክርስቶስ በአማን መድኅነ ዓለም ።"
            ↳ ሴትዮዋንም አሁን በእርሱ ያመን ፡ አንቺ በተናገርሽው አይደለም እኛ ራሳችን ይህ በእውነት የዓለሙ መድኅን ክርስቶስ እንደሆነ ሰምተንና ተረድተን ነው እንጂ አሏት።

የሳምራዊቷን ሴት የቅድስት ብርፍሴንያ [Great-martyr St. Photine]
      ✧ በረከቷ በሁላችን ላይ ይደር!  ✧



tg-me.com/orthodox1/13289
Create:
Last Update:

"ብእሲት ዘኃደገት ቀሱታ ⇨  መቅጃዋን የተወችው ሴት"
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°•◇•°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°

ከሰማርያ መንደር ከወጡ ደገኛ የቅዱስ መጽሐፍ ባለ ታሪኮች ደጉ ሳምራዊ እና ደጓ ሳምራዊት ጎልተው ይጠቀሳሉ። በመጽሐፈ ስንክሳራችንም መጋቢት ፭ ቀን የስሟ ትርጓሜ ሰላምና ሥምረት የሆነ ቅድስት አውዶክስያ የምትባል አንዲት ሳምራዊት ሴት በታላቅ ተጋድሎ ማረፏን ይነግረናል።

የደጉ ሳምራዊ ታሪክ ለትምህርት ምሳሌ ነው [የሉቃስ ወንጌል 10:33] ፤ የእርሷ ግን በአምላካችን ዘመነ ሥጋዌ የተፈጸመ አስተማሪ ኩነት አዝሏል።  መኖርያዋ ሲካር ነው  ታላቋ «ሳምራዊት» ሴት [የዮሐንስ ወንጌል 4:7]

ይህች ሴት መድኃኔዓለም የሚለውን ስም በወንጌል ቀድሞ በሰው አፍ እንዲጠራ በስብከቷ ምክንያት የሆነች የከበረች ምስክር ናት።

ሰማዕነ ወጠየቅነ ከመ ዝንቱ ውእቱ ክርስቶስ በአማን #መድኅነ_ዓለም
            ↳  ይህ በእውነት የዓለሙ መድኅን ክርስቶስ እንደሆነ ሰምተናል ተረድተናል

ወንጌል ስለመጨረሻው ተልእኮዋ ሲነግረን እንዲህ ይተርከዋል፦
            ☞  "ወኃደገት ቀሱታ ይእቲ ብእሲት ወአተወት ሀገረ ወነገረት ለሰብአ ቤታ ።  ወትቤ ንዑ ትርአዩ ብእሲ ዘነገረኒ ኵሎ ዘገበርኩ እንዳዒ ለእመኑ ውእቱ ክርስቶስ "
            ↳ ሴቲቱም ማድጋዋን ትታ ወደ ሀገር ገብታ ለቤተሰቦቿ ነገረች ። የሠራሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ታዩ ዘንድ ኑ፡ ክርስቶስም እንደሆነ እንጃ አለች ።

መምህረ ዓለም ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሐዋርያዊ ሥራዋን በላቀ መንገድ ሲነግረን "ሌሎቹ ሐዋርያት መረባቸውን ጥለው ሲከተሉት እርሷም በሐዋርያነቷ መቅጃዋን ጥላ ተከተለችው ከእነርሱ እነ ፊልጶስ እነ እንድርያስ ሌላውንም እንዲከተለው በአንድ በሁለቱ ፊት ሲመሰክሩ እርሷ ግን መንደሩ ሁሉ እንዲከተለው ሰበከች" አለን ፤ አቤት መታደሏ!


ሳምራዊቷ ሴት ማናት?
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
ከ፹፩ዱ ቅዱስ መጽሐፋችን በተጨማሪ በሌሎች የትውፊት መጻሕፍት አዋልድም ጭምር በተለያዩ  መጠሪያዎች ተጠርታ  ከተጨማሪ ታሪኮች ጋር እናገኛታለን።

       ቀደምት የግሪክ ክታቦች አምስት እኅቶችና ሁለት ልጆች የነበሯት በሰማዕትነት ክብር ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስን ተከትላ የጽድቅ ምስክር ሆና ያረፈች እንደሆነች አስረድተው ስሟ የከበረ ታላቋ ሰማዒት (ምስክር) ሳምራዊቷ ቅድስት #ፎጢን (holy and glorious Great-martyr #Photine of Samaria) እያሉ ገልጠዋታል።

የ’ኛውም ተአምረ ኢየሱስ  ደግሞ ስሟን በመጥቀስ የታሪኳን ፍጻሜ እንዲህ አስቀምጦልናል ፦

             ☞ "ወሶበ ሰምአት ብእሲት ሳምራዊት ዘስማ #ብርፍሴንያ ነገሮ ለእግዚእ ኢየሱስ ሖረት ወዜነወት ለሰብእ እንዘ ትብል ንዑ ኀቤየ አርእየክሙ ብእሴ ዘየአምር ኅቡአተ እስመ ውእቱ ዜነወኒ ግብርየ ዘአኀብኦ እም ሰብእ"
            ↳   ይህችም ብርፍሴንያ የምትባል ሳምራዊት ሴት የጌታ ኢየሱስን ነገር በሰማች ጊዜ ወደሀገር ገብታ ለሰዎቹ ሁሉ በሆዴ ውስጥ ያለውን ምሥጢር ሁሉ የሚናገር ሰው አሳያችሁ ዘንድ ኑ እኔ ከሰው ደብቄ የያዝኩትን ምሥጢር ነግሮኛልና አለቻቸው ።


        ሳምራዊቷ ሴት ቅድስት ብርፍሴንያ መቅጃዋን ጥላ ወደ መንደር ተመልሳ በሀገሩ ያሉትን ሁሉ ወደ ድኅነት ወደ ሕይወት ውኃ ጠራች የበረከት ቃል ከአንደበቷ እየተቀዳ አፏ የሕይወት ውኃ ምንጭ ሆነ።  "ያደረግሁትን ሁሉ የነገረኝን ሰው ኑና እዩ" ትላለች። ጠቢቡ “የጻድቅ አፍ የሕይወት ምንጭ ናት፤ የኀጥኣንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል።”  【ምሳሌ 10፥11】

         ለሲካር መንደር ሕዝብ ቅድስት ብርፍሴንያ ለሕይወት ውኃ ክርስቶስ "መቅጃቸው" ናት። እነርሱ ግን የሴት ደቀ መዝሙር ለመባል አፍረው በእርሷ ስብከት ተከትለው ቢያምኑበትም የእርሷን ድርሻ ግን እንዲህ እያሉ ካዱ ፦

             ☞ "ወይቤልዋ ለይእቲ ብእሲት አኮ እንከ በነገረ ዚአኪ ዘአመነ ቦቱ አላ ለሊነ ሰማዕነ ወጠየቅነ ከመ ዝንቱ ውእቱ ክርስቶስ በአማን መድኅነ ዓለም ።"
            ↳ ሴትዮዋንም አሁን በእርሱ ያመን ፡ አንቺ በተናገርሽው አይደለም እኛ ራሳችን ይህ በእውነት የዓለሙ መድኅን ክርስቶስ እንደሆነ ሰምተንና ተረድተን ነው እንጂ አሏት።

የሳምራዊቷን ሴት የቅድስት ብርፍሴንያ [Great-martyr St. Photine]
      ✧ በረከቷ በሁላችን ላይ ይደር!  ✧

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13289

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Can I mute a Telegram group?

In recent times, Telegram has gained a lot of popularity because of the controversy over WhatsApp’s new privacy policy. In January 2021, Telegram was the most downloaded app worldwide and crossed 500 million monthly active users. And with so many active users on the app, people might get messages in bulk from a group or a channel that can be a little irritating. So to get rid of the same, you can mute groups, chats, and channels on Telegram just like WhatsApp. You can mute notifications for one hour, eight hours, or two days, or you can disable notifications forever.

Telegram auto-delete message, expiring invites, and more

elegram is updating its messaging app with options for auto-deleting messages, expiring invite links, and new unlimited groups, the company shared in a blog post. Much like Signal, Telegram received a burst of new users in the confusion over WhatsApp’s privacy policy and now the company is adopting features that were already part of its competitors’ apps, features which offer more security and privacy. Auto-deleting messages were already possible in Telegram’s encrypted Secret Chats, but this new update for iOS and Android adds the option to make messages disappear in any kind of chat. Auto-delete can be enabled inside of chats, and set to delete either 24 hours or seven days after messages are sent. Auto-delete won’t remove every message though; if a message was sent before the feature was turned on, it’ll stick around. Telegram’s competitors have had similar features: WhatsApp introduced a feature in 2020 and Signal has had disappearing messages since at least 2016.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from us


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA