Telegram Group Search
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

የአብርሐምን ቤት የባረኩ ሥላሴ እኛንም በህይወታችን በኑሮዋጭን በአገልግሎታችን በትዳርአችን በትምርታችን በሥራችን ይባርኩን ።

ሥሉስ ቅዱስ ለሚታምን ሁሉ እምነትን በረከትን ሀገራችን ኢትዮጽያን ሰላም ያድርጉልን አሜን ::

#መልካም እለተ ይሁንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
.
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው
========================

ሰኔ 7/2016 ዓ.ም (የጋ/አ/ዞ/ሀ/ስ አርባምንጭ )

በጋሞ እና አካባቢው ዞኖች አህጉረ ስብከት በአርባ ምንጭ ከተማ በደብረ መ/መድኃኔዓለም ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ከሰኔ 7-9/2016 ዓ.ም የሚካሄደውን ታላቅ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ ተጋባዥ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና መምህራነ ወንጌል እንዲሁም ዘማሪያን በዛሬው እለት ወደ አርባ ምንጭ ሲገቡ በጋሞ አባቶች እና በርካታ ቁጥር ባላቸው ማህበረ ምዕመናን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

@ortodoxtewahedo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የመምህር ተስፈየ አበራ ትምህርቶች የምትቀበሉ እና ትክክል አይደለም የምትሉ በኦርቶዶክሳዊ ጨዋነትና በመረጃ ሀሳብ ስጡ ????

@ortodoxtewahedo
“በጋሞ የሚገኙ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ለመርዳት፣ ባህሉን ለማጠናከር የምታደገርጉት ሥራ ሁሉ የሚያስመሰግን ነው፡፡ ለሰው በሚገባው በራሱ ቋንቋ ማስተማር የሚያስደስት ነው፡፡”
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል አስተባባሪ የተመሠረተበትን 24ኛ ዓመት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ አከበረ፡፡
ዘጋቢ መ/ር ጌታቸው በቀለ
(#EOTCTV ሰኔ ፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም )
+++++++++++++++++++++++++++++++++++ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር አገልግሎቱን እያካሄደ የሚገኘው የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል ማስተበባበሪያ የተመሠረበት ዋና ዓላማ በጋሞ የሚገኙ የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን ለመርዳት፣ ስብከተ ወንጌል በጋሞኛ ቋንቋ ለማስፋፋት በመሆኑ፤ የተመሠረተበትን ፳፬ ኛ ዓመት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት ሰኔ ፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ አክብሯል፡፡
በዕለቱም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ባስተላለፉት መልእክት “የ፳፬ኛ ዓመት በዓላችሁን ለማክበር በመብቃታችሁ እንኳን አደረሳችሁ፤ እንኳን ደስ አላችሁ” ብለዋል፡፡ ቅዱስነታቸው አያይዘውም “በጋሞ የሚገኙ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ለመርዳት፣ ባህሉን ለማጠናከር የምታደገርጉት ሥራ ሁሉ የሚያስመሰግን ነው፡፡ ለሰው በሚገባው በራሱ ቋንቋ ማስተማር የሚያስደስት ነው፡፡ የጀመራችሁትን የገጠር አብያተ ክርስቲያናትን መርዳት፣ በጋሞኛ ቋንቋ ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት የምታደርጉትን በጎ ሥራችሁን ቀጥሉበት፤ እግዚአብሔር የሚወደው ይህን ሥራ ነው፡፡ እናንተ አሁን የምትሠሩትን ሥራ ልጆቻችሁም የእናንተን ፈለግ ተከትለው በበጎ ነገር እንዲሠማሩ አስተምሯቸው፡፡” በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላለውፈዋል፡፡
የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል አስተባባሪ ኮሚቴ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት መንፈሳዊ አገልግሎት እንዲሟላ፣ የአገልጋዮች ደመወዝ በወቅቱ እንዲከፈል፣ ፈዋሽ የጠበል ቦታዎች ይዘታቸውን ጠብቀው እንዲቀጥሉ፣ አብያተ ክርስቲያናት ደረጃቸውን በጠበቀ በዘመናዊ ሕንጻ እንዲገነቡ እያደረገ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
የጋሞ አብያተ ክርስቲያናት የጋራ ልማትና የስብከተ ወንጌል አስተባባሪ ኮሚቴ በስብከተ ወንጌልም ምእመናን በሚገባቸው በጋሞኛ ቋንቋ ወንጌል በማስተማር፣ መዝሙር በማስጠናት ሰፊ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ በቋንቋው የሚያስተምሩ መምህራን ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ፣ ከሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ እንዲሁም በየሰንበት ትምህርት ቤቶች የተማሩ ደቀመዛሙርት በየጉባኤያቱ እና ማኅበራት ጋር እየተገኙ እንዲያስተምሩ እየተደረገ መሆኑን በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
በገዳማትና አድባራት በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ጋሞኛ ክፍል በአዲሱ የቤተክርስቲያን ሥርዐተ ትምህርት መሠረት ከ1ኛ-8ኛ ክፍል ከአንድ ሺህ አንድ መቶ በላይ በተማሪዎች ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ቤታቸው የፈረሰባቸውን ጉባኤያትና አባላት መልሶ ከማቋቋም አንጻር በዚህ ዓመት እንጦጦ እና አካባቢው አንድ፣ አየር ጤና እና ጀሞ ሦስት፣ ሸገር ከተሞች ሁለት ጉባኤያት መልሰው እንዲቋቋሙ ማድረጋቸውን የቀረበው ሪፖርት ያስረዳል፡፡

@ortodoxtewahedo
#ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤተክርስቲያን ::

@ortodoxtewahedo
❖ ሰኔ ፲፪ ❖

✞ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት [በነገዱ ውስጥ፥ በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት..፣ በእስክንድርያ ከተማ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት..፣ የሞት መልእክት የተጻፈባትን የቅዱስ ባሕራንን ደብዳቤ የለወጠበት..፣ ቅድስት አፎምያን ያዳነበት..፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት..በእለኚህ ምክንያት ነው በዓሉን የምናከብረው] ✞

"ሰላም ለሚካኤል መሐሪ ውእቱ፤ ወተአዛዚ ለሰብእ በዲበ ሠናይቱ፤ ለቀርነ ዝንቱ መልአክ በድምፀ ንፍሐቱ፤ በከመ ኮነ ቀዳሚ ውስተ ሰማያት ዕርገቱ፤ ለእግዚአብሔር ይከውን ዳግመ ምጽአቱ።"

@ortodoxtewahedo
#ጾመ_ሐዋርያት

‹‹ይኽ ጾም በአላዋቂዎችን እና በቤተክርስቲያን ጠላቶች የሽማሌዎች ጾም እየተባለ ምዕመናን እንዳይጾሙት ብዙ ተለፍቷል..››

በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ የሚዠምሩ ሶስት አጽዋማት ብቻ አሉ ፡፡ ከእነርሱ መሀከል አንዱ ጾመ ሐዋርያት ነው ፡፡ ቅበላው በዕለተ እሑድ ይሆንና ጾሙ ሰኞ ይውላል ፡፡ የ2016 ዓ.ም ጾመ ሐዋርያት ሰኔ 17 ይገባል ፡፡

ይህ ጾም እራሱ ጌታቸን ኢየሱስ ክርቶስ ትንቢት የተናገረለት ጾም ነው፡፡
ይኽ ታላቅ ጾም የዛሬ 1902 ዓመት በፊት በራሳቸው በቅዱሳን ሐዋርያት የተጀመረ ጾም ነው ፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መሀከልም አንዱ ነው ፡፡
ፈሪሳውያ ጌታችንን ደቀ መዛሙርትህ አይጾሙም ብለው በጠየቁት ጊዜ እርሱም ‹‹ ሚዜዎች ሙሽራ ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን መሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ፤ በዚያ ጊዜም ይጾማሉ ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም ፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና ፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል ፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም ፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል የወይን ጠጁም ይፈሳል ፡፡አቁማዳው ይጠፋል ፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ ፡፡›› ማቴ 9 ፥ 14-17 አላቸው ፡፡ይኽ ቃለ እራሱ ጌታችን መድኀኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ስለ ጾመ ሐዋርያት የተናገረው ትንቢት ነው ፡፡

‹‹#መሽራው_ከተወሰደ በኃላ›› ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኃላ ማለት ሲኾን ይኽን ጾም ከዕረገት በኋላ የምንዠምረው ፤ ይኽን ምሳሌ በማድረግ ነው ፡፡ ዐሥር ቀን ዘግይቶ መዠመሩም የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበትና ነው ፡፡

የዚኽን ማብራርያ በቀጣይ ጽሑፋችን እንመለስበታልን፡፡
ይኽ ጾም በአላዋቂዎችን እና በቤተክርስቲያን ጠላቶች የሽማሌዎች ጾም እየተባለ ምዕመናን እንዳይጾሙት ብዙ ተለፍቷል ልናውቅ የሚገባው ነገር ግን ሐዋርያት ዓለምን ዞረው ከማስተማራቸው በፊት ይህን ጾም ጾመዋል ፡፡ በዚህም ጌታችን የተናረው ተንቢት ተፈጽሟል፡፡ ከሰባቱ አጽዋማትን አንዱ ነው ፡፡ በዚህ ምክንያት ይህን ጾም ታላቅ እና ልዩ ያስብለዋል ፡፡ ይኽንን አውቀን ሁላችንም በሕግ በሥርዓት ልንጾመው ይገባል ፡፡

@ortodoxtewahedo
2024/06/25 07:45:34
Back to Top
HTML Embed Code: