Telegram Group & Telegram Channel
"ወንጌላዊው ዮሐንስ እመቤታችንን የጠራበት መንገድ"

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን …………“የኢየሱስ
እናት” ብሎ ጠርቷታል፡፡ ይኼ ሐዋርያ በጻፈው
ወንጌል ላይ የራሱንም ስም እንኳን አንድ ጊዜ
ያልጠራ ትሑት ሰው ቢሆንም የእመቤታችንን
ስም የጠራበት መንገድ እንዲሁ የምናልፈው
አይደለም፡፡ በወንጌሉ/በዮሐንስ ወንጌል/
እመቤታችንን ስምንት ጊዜ አንስቷታል፡፡ /ዮሐ
፪፥፩‚ ፪፥፫‚ ፪፥፭‚ ፪፥፲፪‚ ፮፥፵፪‚ ፲፱፥፳፭
‚ ፲፱፥፳፮‚ ፲፱፥፳፯/ ስምንት ጊዜ ሲጠራት ግን
አንድም ቦታ “ማርያም” ብሎ በስሟ
አልጠራትም፡፡ የጠራት “የኢየሱስ እናት” “እናቱ”
ብቻ ብሎ ነው፡፡ ቅርበት ባይኖረው ነው እንዳንል
ወንጌሉ ድንግል ማርያም በመስቀሉ ሥር
ለዮሐንስ ተሰጥታው “ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ወደ
ቤቱ ወሰዳት” ይላል፡፡ /ዮሐ ፲፱፥፳፯/ ሥጋዋን
መላእክት ነጥቀው ወደ ሰማይ ሲወስዱትም
አብሯት ተነጥቋል፡፡ ይህ ሐዋርያ በወንጌሉ ዐሥራ
አራት ጊዜ ማርያም የሚባሉ ሴቶችን ስም
ቢጽፍም አንድም ጊዜ እመቤታችንን በስሟ
አልጠራትም፡፡
ነገሩን አልን እንጂ እሱማ መጽሐፍ ቅዱስን
ስንመረምር አምላክን ከወለደች ጀምሮ
ከመላእክትም ወገን ሆነ ከሰዎች ወገን እሷን
የጠሩበት መንገድ ሲቀይሩ አይተናል፡፡አምላክን
ከመጸነሷ በፊት “ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር
ፊት ጸጋን አግኝተሻልና አትፍሪ” ሲሉ የነበሩት
መላእክት ከወለደች በኋላ ግን “ሕጻኑና እናቱን
ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ” ሲሉ እናገኛለን፡፡ ሉቃ
፩፥፴ ማቴ ፪፥፵፫ አክስቷ ኤልሳቤጥ ልትጠይቅ
በሔደች ጊዜ ኤልሳቤጥ “የጌታ እናት አለች
እንጂ” እንደ ዝምድናዋ “ማርያም” ብላ
አልጠራቻትም፡፡ ሉቃ ፩፥፵፫
ይህ የሆነበት ምክንያት ድንግል ማርያም እጅግ
ታላቅ የክብር ስሟ “እናቱ” “የኢየሱስ እናት”
“የጌታ እናት” “የአምላክ እናት” የሚለው ስለሆነ
ነው፡፡ አንዲት እናት የታወቀ የከበረ ዝነኛ ልጅ
ካላት ለከሟ ይልቅ የእገሌ እናት ተብላ መጠራቷ
የተለመደና ተገቢ ነው፡፡ እመቤታችን ሰማይና
ምድር በእጁ የሠራው የገናናው አምላክ
ለእግዚአብሔር እናቱ ሆናለች፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው
በስሟ ከመጥራት ይልቅ በክብር ስሟ “የኢየሱስ
እናት” ብሎ ሊጠራት ወደደ፡፡ ይህን የቅዱስ
ዮሐንስ የመላእክት የቅዱሳኑ ትውፊትና የጉባኤ
ኤፌሶን ውሳኔ ይዘን እኛም ማርያም ከማለት
ይልቅ ወላዲተ አምላክ እመ አምላ እመቤታችን
እመ ብርሃን እንላታለን፡፡

የወላዲተ አምላክ ምልጃዋ ረድኤቷ አይለየን!!

💚 @finote_kidusan 💚
💛 @finote_kidusan 💛
❤️ @finote_kidusan ❤️



tg-me.com/finote_kidusan/343
Create:
Last Update:

"ወንጌላዊው ዮሐንስ እመቤታችንን የጠራበት መንገድ"

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን …………“የኢየሱስ
እናት” ብሎ ጠርቷታል፡፡ ይኼ ሐዋርያ በጻፈው
ወንጌል ላይ የራሱንም ስም እንኳን አንድ ጊዜ
ያልጠራ ትሑት ሰው ቢሆንም የእመቤታችንን
ስም የጠራበት መንገድ እንዲሁ የምናልፈው
አይደለም፡፡ በወንጌሉ/በዮሐንስ ወንጌል/
እመቤታችንን ስምንት ጊዜ አንስቷታል፡፡ /ዮሐ
፪፥፩‚ ፪፥፫‚ ፪፥፭‚ ፪፥፲፪‚ ፮፥፵፪‚ ፲፱፥፳፭
‚ ፲፱፥፳፮‚ ፲፱፥፳፯/ ስምንት ጊዜ ሲጠራት ግን
አንድም ቦታ “ማርያም” ብሎ በስሟ
አልጠራትም፡፡ የጠራት “የኢየሱስ እናት” “እናቱ”
ብቻ ብሎ ነው፡፡ ቅርበት ባይኖረው ነው እንዳንል
ወንጌሉ ድንግል ማርያም በመስቀሉ ሥር
ለዮሐንስ ተሰጥታው “ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ወደ
ቤቱ ወሰዳት” ይላል፡፡ /ዮሐ ፲፱፥፳፯/ ሥጋዋን
መላእክት ነጥቀው ወደ ሰማይ ሲወስዱትም
አብሯት ተነጥቋል፡፡ ይህ ሐዋርያ በወንጌሉ ዐሥራ
አራት ጊዜ ማርያም የሚባሉ ሴቶችን ስም
ቢጽፍም አንድም ጊዜ እመቤታችንን በስሟ
አልጠራትም፡፡
ነገሩን አልን እንጂ እሱማ መጽሐፍ ቅዱስን
ስንመረምር አምላክን ከወለደች ጀምሮ
ከመላእክትም ወገን ሆነ ከሰዎች ወገን እሷን
የጠሩበት መንገድ ሲቀይሩ አይተናል፡፡አምላክን
ከመጸነሷ በፊት “ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር
ፊት ጸጋን አግኝተሻልና አትፍሪ” ሲሉ የነበሩት
መላእክት ከወለደች በኋላ ግን “ሕጻኑና እናቱን
ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ” ሲሉ እናገኛለን፡፡ ሉቃ
፩፥፴ ማቴ ፪፥፵፫ አክስቷ ኤልሳቤጥ ልትጠይቅ
በሔደች ጊዜ ኤልሳቤጥ “የጌታ እናት አለች
እንጂ” እንደ ዝምድናዋ “ማርያም” ብላ
አልጠራቻትም፡፡ ሉቃ ፩፥፵፫
ይህ የሆነበት ምክንያት ድንግል ማርያም እጅግ
ታላቅ የክብር ስሟ “እናቱ” “የኢየሱስ እናት”
“የጌታ እናት” “የአምላክ እናት” የሚለው ስለሆነ
ነው፡፡ አንዲት እናት የታወቀ የከበረ ዝነኛ ልጅ
ካላት ለከሟ ይልቅ የእገሌ እናት ተብላ መጠራቷ
የተለመደና ተገቢ ነው፡፡ እመቤታችን ሰማይና
ምድር በእጁ የሠራው የገናናው አምላክ
ለእግዚአብሔር እናቱ ሆናለች፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው
በስሟ ከመጥራት ይልቅ በክብር ስሟ “የኢየሱስ
እናት” ብሎ ሊጠራት ወደደ፡፡ ይህን የቅዱስ
ዮሐንስ የመላእክት የቅዱሳኑ ትውፊትና የጉባኤ
ኤፌሶን ውሳኔ ይዘን እኛም ማርያም ከማለት
ይልቅ ወላዲተ አምላክ እመ አምላ እመቤታችን
እመ ብርሃን እንላታለን፡፡

የወላዲተ አምላክ ምልጃዋ ረድኤቷ አይለየን!!

💚 @finote_kidusan 💚
💛 @finote_kidusan 💛
❤️ @finote_kidusan ❤️

BY ፍኖተ ቅዱሳን ꜰɪɴᴏᴛᴇᴋɪᴅᴜsᴀɴ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/finote_kidusan/343

View MORE
Open in Telegram


ፍኖተ ቅዱሳን ꜰɪɴᴏᴛᴇᴋɪᴅᴜsᴀɴ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

What is Secret Chats of Telegram

Secret Chats are one of the service’s additional security features; it allows messages to be sent with client-to-client encryption. This setup means that, unlike regular messages, these secret messages can only be accessed from the device’s that initiated and accepted the chat. Additionally, Telegram notes that secret chats leave no trace on the company’s services and offer a self-destruct timer.

ፍኖተ ቅዱሳን ꜰɪɴᴏᴛᴇᴋɪᴅᴜsᴀɴ from us


Telegram ፍኖተ ቅዱሳን ꜰɪɴᴏᴛᴇᴋɪᴅᴜsᴀɴ
FROM USA