Telegram Group Search
ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር
Yonatan BT Furniture

የዘመናዊነት ተምሳሌት!


አድራሻችን፦
1. ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251 995 27 2727
2. ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251 957 86 8686
3. ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251 993 82 8282

👉 Telegram:  https://www.tg-me.com/yonatanbt_furniture
👉 Facebook:  https://www.facebook.com/profile.php?id=100087238034736
👉 TikTok: https://www.tiktok.com/@yonatanbtfurniture
👉 Instagram: https://www.instagram.com/yonatanbtfurniture/
#Ethiopia

ሳፋሪኮም ፥ በ1.5 ቢሊዮን ዶላር 5,000 የቴሌኮም ማማዎችን ሊገነባ መሆኑን ገለጸ።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ማማዎቹን የሚገነባው የኔትወርክ መሰረተ ልማትን በአገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች ለማስፋፋት መሆኑን አስታውቋል። 

በዚህም በቀጣዮቹ 3 ዓመታት የኔትወርክ ማማዎችን ለመገንባት ማቀዱን የገለጸው ተቋሙ ፣ ለግንባታው 1,5 ቢሊዮን ዶላን ፈሰስ ለማድረግ እንደመደበ ገልጿል። 

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄለፑት ባደረጉት  ገለጻ፣ “ ኔትወርካችንን ለማስፋፋት እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን የቴሌኮም ትስስርን ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት እያደረግን እንገኛለን ” ብለዋል።

በአጠቃላይ የኔትወርክ ማማዎችን ቁጥር ወደ 7,000 ለማድረስ እየሰሩ እንደሚገኙ አስረድተው፣ “ በአሁኑ ጊዜ አገልግሎት ከምንሰጥባቸው 2,500 የቴሌኮም ማማዎች ውስጥ 1,5000 እራሳችን የገነባናቸው ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ታግታ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የተጠየቀባት ህጻን ተገኘች።

የ2 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜ ያላት አቢጊያ ዳንኤል የተባለች ህፃን ነዋሪነቷ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 " ሳርቤት ' አካባቢ ሲሆን ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስዳ ትታገታለች።

አጋቿ ቸርነት ጥላሁን የተባለው ግለሰብ ነው።

ግለሰቡ ከቤተሰቡ ጋር በነበረው ቅርበት ህፃን አቢጊያን በተለያዩ ቦታዎች እየወሰደ በማዝናናት እንደ ቤተሰቡ አባል ያጫውታት እንደነበረ እና ከ5 ወር በላይ ከቤተሰቡ ጋር በትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪነት የነበረው ቅርብ ወንጀሉን በቀላሉ ለመፈፀም ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረለት የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ግለሰቡ ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ተኩል ገደማ ወደ ህፃኗ ወላጆች መኖሪያ ቤት በመሄድና "እናቷ አምጣት ብላኛለች "ብሎ ለቤት ሰራተኛዋ ከነገረ በሗላ ህፃን አቢጊያ ዳንኤልን ወስዶ በማገት ገንዘብ እንዲሰጠው ከወላጆቿ ጋር ሲደራደር ቆይቷል።

ተጠርጣሪው ግለሰብ 150 ሺህ የአሜሪካ ዶላር እንዲሰጠው በመጠየቅ ገንዘቡን ማግኘት ካልቻለ ግን ህፃኗን በህይወት እንደማያገኟት ሲዝት ነበር።

የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ህፃኗን ለማስመለስ እና ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።

በተደረገው ክትትልም ዛሬ ሚያዚያ 28/ 2016 ዓ/ም በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አለም ሰላም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተጠርጣሪው ተከራይቶ በሚኖርበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ3 ቀናት ያህል ታግታ የቆየችው ህፃን አቢጊያ ዳንኤል ልትገኝ መቻሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ምንም እንኳን ፖሊስ ህጿን መገኘቷን ቢገልጽም አጋቹ በቁጥጥር ስር ስለመዋሉ ያብራራው ነገር የለም።

@tikvahethiopia
#Update

የታገቱ ሰዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ፦
➡️ ወደ ባቱ ሲጓዙ በታጣቂዎች ስለታገቱና እስካሁን ስላልተለቀቁ 3 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ጉዳይ፤
➡️ ልጃቸው በሊቢያ ስለታገተባቸው የሀዋሳዋ እናት ፣
➡️ ልጃቸው በሊቢያ ስለታገተባቸው የአዲስ አበባው አባት ፤
➡️ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ስትጓዝ የመን ላይ ታግታ 300 ሺህ ብር ስለተጠየቀባት ወጣት መረጃዎችን ማድረሱ ይታወሳል።

ስለታጋቾች አሁንስ #ምን_አዲስ_ነገር_አለ ? በሚል ቤተሰቦቻቸውን ጠይቋል።

የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ታጋቾችን በተመለከተ አዲስ ነገር የጠየቅናቸው የአንዱ ታጋች እህት ወይዘሮ ራሄል ሶስቱም #እንዳልተለቀቁ ገልጸው ፤ “ ምንም አይነት ፍንጭ የሚሰጠንም አጣን። የት እንሂድ ? ምን እናድርግ ? ” ሲሉ በሀዘን ጠይቀዋል።

ልጃቸው በሊቢያ እንደታገተባቸው ገልጸው የነበሩት የሀዋሳዋ ወይዘሮ ገነት ጥላሁን ፥ “ አሁንማ ‘ ፓሊስ ከቧቸዋል ’ ተብሎ ስልክም ብንደውል አይነሳም። ስልካቸው ከጠፋ ከ15 ቀናት በላይ ሆኗል ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ትሪፓሊ ከተማ ከደረሱት ውስጥ መረጃ ስንጠይቅ ‘ፓሊስ መጥቶባቸው ነው ፤ ከበዋቸዋል አካባቢውን’ ” እንዳሏቸው ገልጸዋል።

“ ደላላውን 1 ጊዜ ብቻ አግኝቸው ‘ ፓሊስ ስለመጣብን ሌላ መጋዘን ወስደናቸዋል ’ አለኝ ” ሲሉ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ልጃቸው በሊቢያ ታግቶባቸው 700 ሺሕ ከከፈሉ በኋላ በድጋሚ 400 ሺሕ ብር ተጠይቀው የነበሩት የታጋች አባት አቶ አማረ አለም ፣ ለ2ኛ ጊዜ የተጠየቁትን ገንዘብ ካርታ አስይዘው ተበድረው ከላኩ በኋላ ልጃቸው #እንደተለቀቀ ባሕሩን ለመሻገር አስቦ ሞገድ ስለተነሳ ገና እየጠበቀ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሳዑዲ ለመሄድ  " ራጎ " ላይ ስትደርስ በደላሎች 300 ሺሕ ብር የተጠየቀባት ታጋች ቤተሰቦች በበኩላቸው፣ ገንዘቡ ስላልተሟላ ገና እንዳልተላከ፣ ደላሎቹን ጊዜ እንዲሰጧቸው እየጠየቁ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ፤ እገዛችሁን ጠይቀው የነበሩት ሁሉም የታጋቾች ቤተሰቦች ለረዷቸው ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

የባንክ አካውንት ባንክ ሳይሄዱ መክፈት ይቻላል? አዎ! በአቢሲንያ ቨርቹዋል ባንክ ከእሁድ እስከ እሁድ ለ24 ሰዓት ይቻላል።


አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!

#virtualbanking #bankinginethiopia #banksinethiopia #ITM #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#ታምራት_ፕሌት_እና_ጄቦልት_አቅራቢ

📌ፕሌትና ጄቦልት በፈለጉት አይነት የተዘጋጀ አለን
✂️ላሜራ መቁረጫ መብሻና ማጠፊያ ማሽኖች አሉን
🔗ፌሮ (ቶንዲኖ) ጥርስ እናበጃለን እንዲሁም እናጥፋለን
📐ማንኛዉንም የሞደፊክ ስራዎችን እንሰራለን

📍ኢትዮጵያ ዉስጥ የትም እንልክሎታለን

አድራሻችን፦ ቁ.1 አዉቶብስ ተራ(መሳለሚያ)
                    ቁ.2 መርካቶ
                    ቁ.3 ተክለሀይማኖት

0904040477
0911016833
Manager : Netsanet Tamene
" ፍጹም ሀሰተኛ ነው " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከሰሞኑን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል /Rapid Support Forces - RSF/ በሚባል የሚጠራው " የህወሓት ታጣቂዎች ከሱዳን ወታደራዊ ሃይል /SUDANESE ARMED FORCES  SAF/ ጋር በማበር እየወጉኝ ነው " በማለት ያወጣውን መግለጫ ፍጹም ሀሰተኛ እና መሰረተ ቢስ እንደሆነ ገለጸ።

ሱዳን በእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ከገባች በርከታ ወራት ያለፉ ሲሆን በዚህም የሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ደም አፋሳሽ ግጭት እያደረጉ ናቸው።

ታዲያ ፈጥኖ ደራሹ ኃይል " ህወሓት (TPLF) ከሱዳን ጦር ጋር ሆኖ ወግቶኛል " ብሏል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር  የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መግለጫ ለዘመናት የቆየውና በፅኑ መሰረት የቆመው የትግራይና የሱዳን ህዝቦች ወዳጅነት ከግምት ያላስገባ ነው ብሎታል።

" በሱዳን ያለው የአርስበርስ ግጭት  ዓለምአቀፍ መልክ ለማስያዝና እርዳታ ለማግኘ ያለመ ነው " ሲልም ገልጿል።

ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ በዚሁ የሺዎች ህይወት በመቅጠፍ ላይ ያለውን የአገሪቱ የእርስ በርስ ጦርነት ላክ የህወሓት ሃይሎች ተሳትፈዋል የሚል ክስ ማቅረቡ " ሃሳባዊና  መሬት ላይ መረጋገጥ የማይችል የለየለት ፈጠራ  " ሲል አጣጥሎታል።

" በመሰረቱ ህወሓት የፓለቲካ ድርጅት እንጂ የሚያዘውና የሚያስተዳድረው ታጣቂ ሃይል የለውም " ያለው የጊዚያዊ አስተዳደሩ መግለጫ " የትግራይ ህዝብ ከወንድም የሱዳን ህዝብ የረጅም ጊዜ መልካም ግንኙነትና ጉርብትና አለው " ብሏል።

" ከዚህ አኳያ ትግራይ በሱዳን የውስጥ ጉዳይ ነገሮች በማጋጋል የምትገባበት ምክንያትና የምታገኘው ጥቅም የለም " ሲል አሳውቋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ፤ በሱዳን የተፈጠረው አውዳሚ የአርስ በርስ ጦርነት የሚያስከትለው አደጋ በመረዳት የውጭ ሃይሎች በአገሪቱ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ አሳስቧል። 

@tikvahethiopia
ዛሬ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ ታይቷል።

ነገር ግን አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል መቆሙን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።

መንገዶኞቹም ከአውሮፕላን ላይ ደህንነታቸው እንደተጠበቀ መወርዳቸውን ገልጿል።

" በአሁኑ ሰአት የክስተቱ መንስኤ በመጣራት ላይ ይገኛል " ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት ደንበኞቹን ይቅርታ ይጠይቋል።

@tikvahethiopia
የትንሳኤ ልዩ የሞባይል ጥቅል የቆይታ ጊዜ ነገ ያበቃል!

ልዩ የበዓል ጥቅሎቹን በቴሌብር ሱፐርአፕ ከተጨማሪ 10% ስጦታ ጋር እንዲሁም በማይ ኢትዮቴል፣ አርዲ ቻትቦት ወይም በ*999# ይግዙ፤ ለሚወዷቸውም በስጦታ በማበርከት እስከ 25% ቅናሽ ያግኙ!


#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#AddisAbaba

ሀሙስ ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ ለመምህራንና ለትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት ምዘና ፈተና እንደሚሰጥ ተነግሯል።

ፈተናው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እና የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በጋራ በመሆን ነው የሚሰጡት ተብሏል።
 
ፈተናው በተመረጡ የመፈተኛ ጣቢያዎች በፈቃደኝነት ለተመዘገቡ 18 ሺህ 591 ለሚሆኑ መምህራንና የትምህርት አመራሮች እንደሚሰጥ ተገልጿል።

በፈተና ወቅት ተመዛኞች ስልክ ሆነ ማንኛውንም አይነት ኤሌክትሮኒክስ ግብአቶች ይዞ ፈተና ክፍል መግባት እንደማቻል ተገልጿል።

ተመዛኞች ፦

➡️ የታደሠ መታወቂያ ይዘው መገኘት እንደሚጠበቅባቸው ፣

➡️ ፈተናው ከመጀመሩ በፊት 1:00 ሠዓት ቀደም ብለው (1:30) ላይ የምዘና ፈተና መስጫ ቅጥር ግቢ ውስጥ መገኘት እንዳለባቸው እና አርፍዶ መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ተብሏል።

ምንም እንኳን ፈተናው በፍቃደኝነት ለተመዘገቡ 18,491 መምህራን እና የትምህርት አመራሮች እንደሚሰጥ ቢገለጽም የምዘና ፈተና ለመውሰድ #ስላልተመዘገቡ ወይም ፍቃደኛ ስላልሆኑ መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ምንም የተባለ ነገር የለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ #ጅቦቹ ሰው መተናኮስ ፤ በቀን መታየትና #ሰብሰብ ብሎ መሄድ ጀምረዋል " - ነዋሪዎች

" በኛ ቀበሌ ብቻ 3 ህጸናት በጅቦች ተበልተዋል። 2ቱ ሲሞቱ አንዷ ተርፋለች " - አቶ ማርቆስ ቡታ

ከሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የተራቡ ጅቦች እያደረሱ ስላለው ጥቃት የሚመለከቱ መረጃዎችን ማጋራታችን ይታወሳል።

በተለይ በስልጤ ዞን እና በሀላባ ዙሪያ በተፈጸሙ የጅብ ጥቃቶች ምክኒያት የሰው ህይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት መድረሱን መግለጻችን አይዘነጋም።

በወቅቱ " የጅብ መንጋ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ  ተከስቷል " የሚለውን ዜና የሰሙ የሲዳማ ክልል፣ የሀዋሳ ከተማ ዙሪያ ነዋሪዎች " ችግሩ እኛም ጋር አለ እንዲያዉም ከህጻናት ባለፈ አዋቂዎችንም አሳስቦናል " በማለት መልዕክቶቻቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድረሰዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ አባል በሀዋሳ ዙሪያ ቡሽሎ ፣ ፊንጭ ውሀና ገመጦ... ወዘተ ቀበሌዎች ያሉ ማህበረሰቦችና የጸጥታ አካላትን አነጋግሯል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በጊዜ ወደ ቤታቸው መግባት መጀመራቸውን በመጥቀስ ህጻናት ልጆቸውም ፍርሀት እንዳደረባቸዉ ገልጸዋል።

በተለያየ ጊዜ በ5 ሰዎች ላይ የጅብ ጥቃት ደርሶ እንደነበር እና 2 ህጻናት እንደሞቱ 1 ህጻን እንዲሁም 4 አዋቂዎች ደግሞ እንደተጎዱ አስረድተዋል። የሚመለከተው አካል አንዳች መፍትሄ እንዲሰጣቸውም ጠይቀዋል።

በአካባቢው ለረዥም ጊዜያት ጅቦች እንደነበሩ የሚገልጹት ነዋሪዎቹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ሰው መተናኮስ ፤ በቀን መታየትና #ሰብሰብ ብሎ መሄድ መጀመራቸው እንዳስገረማቸው ገልጸዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የቡሽሎ ቀበሌ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማርቆስ ቡታ ፤ " በእኛ ቀበሌ ብቻ 3 ህጻናት በጅቦች ተበልተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

2ቱ መሞታቸውን ፤ አንዷ ህጻን በወቅቱ በተደረገ ርብርብ ተርፋ በተደረገላት ህክምና መዳኗን ገልጸዋል።

በአጎራባች ቀበሌያት ውስጥ በ2 አዋቂ ሰዎች ላይ አሰቃቂ አደጋ ቢደርስም ለመትረፍ እንደቻሉ የጠቀሱት አቶ ማርቆስ ችግሩ አሳሳቢ በመሆን የጸጥታ አካላት እየተነጋገረበት ነው ብለዋል።

ማህበረሰቡ በጊዜ በመግባት የሚሰጠዉን የጥንቃቄ መልእክት በአግባቡ እንዲተገብርም ጠይቀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
2024/05/08 07:29:42
Back to Top
HTML Embed Code: