Telegram Group Search
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ሰኔ ፬ ❖

✞✞✞ እንኩዋን ለታላቁዋ ሰማዕት "ቅድስት ሶፍያ" እና ለቅዱስ "ዮሐንስ ዘሐራቅሊ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+*" #ሶፍያ (SOPHIA) "*+

=>ሶፍያ ("ያ" የሚለው ላልቶ ይነበብ) በቀደመው ዘመን በነበሩ ክርስቲያኖች ዘንድ ተወዳጅ ስም ነበር:: ዛሬ ብዙ አሕዛብ ሲጠሩበት ብንሰማም ትርጉሙ "ጥበበ ክርስቶስ" የሚል ነው:: በዚህ ስም የሚጠሩ አያሌ ቅዱሳት አንስት ሲኖሩ አንዷ ዛሬ ትከበራለች::

+*" ቅድስት ሶፍያ ተጋዳሊት "*+

=>ቅድስቷ የተወለደችው በምሥራቅ ሮም ግዛት ውስጥ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ዘመኑ የጭንቅ : የመከራ በመሆኑ ሕዝቡ በስደት ይኖር ነበር::

+የቅድስት ሶፍያ ወላጆች ክርስቲያኖች ናቸውና በመልካሙ መንገድ በንጽሕና አሳድገዋታል:: ባለጠጐች በመሆናቸው አገልጋይ ቀጥረውላት : ያማረ ቤት ሰርተውላት በዚያ ትኖር ነበር:: ሁሉ ያላት ብትሆንም ሁሉን ንቃ በጾምና በጸሎት ትኖር ነበር::

+ለዐቅመ ሔዋን በደረሰች ጊዜ ወላጆቿ ለከተማው መኮንን (ገዢ) ሊድሯት መሆኑን አወቀች:: ወደ ቤቷ ገብታ 100 ጊዜ ሰገደች:: ወደ ፈጣሪዋም ጸለየች:- "ጌታየ ሆይ! የዚህን ዓለም ቀንበር አታሸክመኝ:: አልችለውምና:: ያንተው ቀንበር ግን የፍቅር ነውና እችለዋለሁ" አለች::

+አገልጋዩዋን ጠርታ ብዙ ወይን አጠጥታት ልብስ ተቀያየሩ:: በሌሊትም ወጥታ ወደ በርሃ ሔደች:: ዓላማዋ ምናኔ ቢሆንም የእግዚአብሔር ፈቃዱ ግን ሌላ ነበር:: በመንገድ ብዙ ክርስቲያኖች በመከራ ብዛት ሲሰደዱ አገኘቻቸው:: እርሷ ስደትን አልመረጠችም::

+እያጠያየቀች "ሰው በላ" ከተባለው አረመኔ ንጉሥ ዲዮቅልጢያኖስ ደረሰች:: በንጉሡ ፊት ቀርባ "እኔ ክርስቲያን ነኝ" አለችው:: ንጉሡ ከመልኩዋ ማማርና ከድፍረቷ የተነሳ አደነቀ::

+ሊያባብላት: ሊያስፈራራትም ሞከረ:: ግን
አልተሳካለትም:: ወታደሮቹ መሬት ላይ ጥለው ጦር ባለው
የብረት ዘንግ
ደብድበዋታልና ደም አካባቢውን አለበሰው:: መሬት
ለመሬት እየጐተቱ እሥር ቤት ውስጥ ጣሏት:: ቅዱስ
ገብርኤል መጥቶ
ፈውሷት ሔደ::

+አንዴ በእሳት: አንዴም በስለት: ሌላ ጊዜም በግርፋት
አሰቃዩዋት:: ከሃይማኖቷ ግን ሊያነቃንቁዋት አልቻሉም::
በመጨረሻ አንገቷን እንድትሰየፍ ንጉሡ አዘዘ::
ወታደሮቹም ፈጸሙት:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ
ቅድስት ሶፍያን
በክብር አሳረጋት:: "ስምሽን የጠራ: መታሰቢያሽን ያደረገ
ምሕረትን ያገኛል" አላት::

+"+ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ +"+

=>ቅዱሱ የነበረው በተመሳሳይ በዘመነ ሰማዕታት ነው::
አባቱ ዘካርያስ: እናቱ ኤልሳቤጥ: እርሱ ደግሞ ዮሐንስ
ይባላል:: የሚገርም መንፈሳዊ ግጥጥሞሽ ነው:: የቅዱሱ
ወላጆች የሃገረ ሐራቅሊ አስተዳዳሪዎች ሲሆኑ
የተመሰከረላቸው
ደጐች ነበሩ::

+ዘካርያስ አርፎ ዮሐንስ በመንበሩ የተቀመጠው ገና በ20
ዓመቱ ነበር:: በወቅቱ ከ2 አንዱን መምረጥ ነበረበት::

1.ለጣኦት ሰግዶ በምድራዊ ክብሩ መቀጠል
2.ወይ ደግሞ በክርስትናው መሞት

+ቅዱስ ዮሐንስ ግን ልቡ በክርስቶስ ፍቅር የተሞላ ነውና
2 ከባባድ ነገሮችን ፈጸመ:: በመጀመሪያ በአካባቢው ያሉ
ጣዖት
ቤቶችን አወደመ:: ቀጥሎ ወደ ንጉሡ ሔዶ በመኩዋንንቱ
ፊት "ክርስቶስን የተውክ ሰነፍ" ብሎ ገሠጸው::

+ከዚህ በኋላ በቅዱሱ ላይ የተፈጸመው መከራ የሚነገር
አይደለም:: ያላደረጉት ነገር አልነበረም:: እሳቱ: ስለቱ:
ሰይፉ: መንኮራኩሩ . . . ከሁሉ የከፋው ግን ቆዳውን
ገፈው በእሳት ጠብሰውታል:: እርሱ ግን ስለ ሃይማኖቱ
ይሕንን
ሁሉ ታግሶ በዚህች ቅን አንገቱን ተሰይፏል::

=>አምላካችን እግዚአብሔር ግፍዐ ሰማዕታትን አስቦ
እኛን ከሚመጣው መከራ ሁሉ ይሰውረን:: ከበረከታቸውም
ይክፈለን::

=>ሰኔ 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ሶፍያ ተጋዳሊት ወሰማዕት
2.ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)
3.ቅዱስ ሳኑሲ ሰማዕት
4.ቅድስት ማርያ ሰማዕት
5.ቅዱስ አርቃድዮስና ባልንጀሮቹ (ሰማዕታት)
6.ቅዱስ አሞን ሰማዕት

❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ
2፡ ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ

=>+"+ እንግዲሕ አትፍሯቸው:: የማይገለጥ የተከደነ:
የማይታወቅም የተሠወረ ምንም የለምና:: በጨለማ
የምነግራችሁን
በብርሃን ተናገሩ:: በጀሮም የምትሰሙትን በሰገነት ላይ
ስበኩ:: ሥጋንም የሚገድሉትን: ነፍስን ግን መግደል
የማይቻላቸውን አትፍሩ:: ይልቅስ ነፍስንም: ሥጋንም
በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ:: +"+ (ማቴ.
10:26)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://www.tg-me.com/ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ዘብሔረ ጎንደር ዲ ዮርዳኖስ አበበ /com.zikirekdusn
#Feasts of #Senne_4

✞✞✞On this day we commemorate the Departure of Saint Sophia the Great Martyr and Saint John of Herakleia✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞ Sophia✞✞✞
=>Sophia (‘-ia’ is unstressed) was a name which was popular amongst early Christians. Though today we hear the gentiles being called by it, it means “The Wisdom of Christ”. There are many saints called by this name and the Saint we commemorate today is one of them.

✞✞✞Saint Sophia the Fighter✞✞✞
=>The Saint was born in the Eastern part of the Roman Empire in the 4th century. And because the era was of persecution and unease, people lived in exile.

✞And since Sophia’s parents were Christians, they raised her in a good manner, purely. And as they were wealthy as well, they hired a servant and built her a house. And there, she lived. Though she had everything, she shunned all, and lived by fasting and prayer.

✞And when she came of age, knowing that her parents were going to wed her to the governor of the city, she entered her home and prostrated a 100 times and prayed to her Creator saying, “My Lord! Do not let me carry the weight of this world as I can not bear it but as Your yoke is love I can bear that.”

✞And then she called upon her handmaid, had her drink much wine and she exchanged clothes. And at night, she went to the desert. Though her wish was asceticism, God’s will for her was another. And on her way, she found many Christians fleeing because of great affliction. Nonetheless, she did not choose exile.

✞Instead, by asking for directions, she reached to the one named as the man-eater, Emperor Diocletian. And she approached before him and said, “I am a Christian.” And the Emperor was astounded by her beauty and bravery. Then, he tried to entice her. And when that failed, he tried to frighten her. But all his efforts were unsuccessful.

✞Hence, the soldiers threw her on the ground and beat her with metal rods that had spikes and the place was covered with blood. Then, dragging her on the ground, they threw her into prison. However, Saint Gabriel appeared and after healing her, he disappeared. 

✞And at times the tormentors tortured her with fire, and on other occasions with blades while on other instances they lashed her. But they were not able to shake her from her faith. Thus, the Emperor finally ordered that she be beheaded. And the soldiers executed his instruction. Then our Lord Jesus Christ descended and took up [the soul of] St. Sophia with honor. And He promised her saying, “The person that calls your name or holds your feast will be forgiven.”

✞✞✞Saint John of Herakleia✞✞✞
=>The Saint in a similar manner [to St. Sophia] lived in the Era of Persecution. His father was called Zechariahs and his mother Elisabeth and he was named John. An amazing spiritual similarity [to the family of St. John the Baptist]. The parents of the Saint were the rulers of the place called Herakleia, and their kindness was attested to.

✞John sat on the throne [of his father] at the age of just 20 years after Zacharias passed away. At the time, he had to choose from the following two.
1. Bow down before an idol and continue with his worldly honor.
2. Or die because of his Christianity.

✞And since St. John’s heart was filled by the love of Christ, he did 2 major things. First, he destroyed temples in his surroundings. And second, he went to the Emperor and rebuked him before his dignitaries saying, “You are an indolent that renounced Christ.”

✞And the tortures that were inflicted upon the Saint after that were unspeakable. There was nothing which his tormentors left out. They used fire, blades, swords, crushing wheels . . . but the worst was when they flayed his skin and burned him. However, he endured all these for his faith, and on this day, he was beheaded.

✞✞✞May our God recall the sufferings of the martyrs and conceal us from the trials which are coming. And may He grant us from their blessings.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 4th of Senne
1. St. Sophia the Fighter and Martyr
2. St. John of Herakleia
3. St. Sanusi (Shenousi) the Martyr
4. St. Maria the Martyr
5. St. Arcadius (Akronius) and his friends (Martyrs)
6. St. Amon/Amoun the Martyr

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. John son of Thunder (the Evangelist)
2. St. Andrew Apostle

✞✞✞ “Fear them not therefore: for there is nothing covered, that shall not be revealed; and hid, that shall not be known. What I tell you in darkness, that speak ye in light: and what ye hear in the ear, that preach ye upon the housetops. And fear not them which kill the body, but are not able to kill the soul: but rather fear him which is able to destroy both soul and body in hell.”✞✞✞
Matt. 10:26-28

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊
(ማቴ ፫:፫)

በአማን ተንሥአ መድኃኒነ!
🌿ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።

🌿ወልደ እግዚአብሔር አምላክነ ወመድኃኒነ ዕቀብ  ሕይወተነ እም ገሀነመ እሳት ወእምኵሉ መንሱት በእንተ ቅዱስ ስምከ ወበእንተ ማርያም እምከ ወበእንተ ቅዱስ መስቀል ወበእንተ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ ወበእንተ ኵሎሙ ቅዱሳን ወሀባ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተክርስቲያን።

ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙኅ ትዕግሥት። ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኩሉ ሰዓት እንበለ ንስሐ ኪያነ ኢይንሣእ ሞት።

🌿አንቅሐኒ በጽባሕ ክሥተኒ ዕዝንየ በዘአጸምእ አምላኪየ አምላኪየ እገይሥ ኀቤከ ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ"

ነቢያት ወሐዋርያት፥ ጻድቃን ወሰማዕት፤ ደናግል ወመነኮሳት፥ አዕሩግ ወሕጻናት፤ ገዳማውያን ወሊቃውንት፤ ሰአሉ ለነ ኲልክሙ፥ ቅድመ መንበሩ ለጸባኦት።

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ዘብሔረ ጎንደር ዲ ዮርዳኖስ አበበ /com.zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
Audio
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊 (ማቴ ፫:፫)


ርዕስ፦📝
"" የሚተረጉምልን አጣን! "" (ዘፍ. ፵:፯)

"ቅዱስ ዮሴፍ ንጉሠ ግብጽ"


📅(ሰኔ1 - 2016)

🎤 በመምህር ዲ/ዮርዳኖስ አበበ

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ዜና እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)

🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ዘብሔረ ጎንደር ዲ ዮርዳኖስ አበበ /com.zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
††† እንኳን ለኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ ብሶይ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ አባ ብሶይ ሰማዕት †††

††† ቅዱሱ አባታችን ከዘመነ ሰማዕታት ጣፋጭ ፍሬዎች አንዱና ግንባር ቀደሙ ነው::

††† ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ማጠናቀቂያ አካባቢ ታግሕስጦስና ክሪስ የሚባሉ ክርስቲያኖች ነበሩ:: በቀናው የጽድቅ ጐዳና ቢኖሩም ከጋብቻ በኋላ ለአሥራ ሰባት ዓመታት መውለድ አልቻሉም::

የአሥራ ሰባት ዓመት ልመናቸውን የተመለከተ እግዚአብሔር ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ አበሰራቸው:: "ሕፃኑ ለሰማዕትነት ተመርጧልና ብሶይ በሉት" አላቸው:: ብሶይ በተወለደ በሰባት ዓመቱ ወላጆቹ ይማር ብለው ወደ ገዳም ወሰዱት:: በገዳም ውስጥ መጻሕፍትን አጥንቶ ዲቁናን ተሾመ:: ወደ ዓለም ተመለስ ቢሉትም እንቢ አለ::

ከባልንጀራው ቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ለሃያ አንድ ዓመታት በድንግልና : በተጋድሎ : ጾምና ጸሎትን እያዘወተሩ ኖሩ:: ቅዱስ ብሶይ ሃያ ስምንት ዓመት በሞላው ጊዜ መልአኩ የተናገረው የትንቢት ዘመን ደረሰ:: በርካታ ምዕመናን ክርስቲያን በመሆናቸው ብቻ ታረዱ:: ወደ እሳትም ተጣሉ:: ሞትን የፈሩ ደግሞ በየዱር ገደሉ ተሰደዱ::

ቅዱስ ብሶይም በሚያውቁት ሰዎች ተከሶ ለፍርድ ቀረበ:: ድንገት ከሰማይ ፍጡነ ረድኤት ወሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ደረሰለት:: "አይዞሕ! እኔ እስከ መጨረሻው ከአንተ ጋር ነኝ" አለው::

የጦር መኮንኑ ክርስቶስን እንዲክድ አባበለው:: ቅዱሱ ግን ጣዖታቱ የአጋንንት ማደሪያ መሆናቸውን በገሃድ ነገረው:: መኮንኑ ቢበሳጭ ወታደሮቹ እንዲጨምቁት አዘዘ:: ደሙ እየወረደ ገረፉት:: በፊትና በኋላ ብረት አድርገው ሥጋውን ጨፍልቀው እሥር ቤት ውስጥ ጣሉት:: ሊቀ መላእክት መጥቶ ዳስሶ አዳነው::

መኮንኑ እርሱን ማሰቃየት ደከመው:: የቅዱሳን ሕይወት ግርም ይላል:: ተገራፊው እያለ ገራፊው : ስቃዩን የሚቀበለው እያለ አሰቃዩ ይደክመዋል::

††† ይሕንን መሰለኝ አባ ጽጌ ድንግል:-
"እመዐዛ ጽጌኪ ድንግል ውስተ ዐውደ ስምዕ ዘሰክረ::
ውግረተ አዕባንኒ ይመስሎ ሐሰረ::
እሳትኒ ማየ ባሕር ቆሪረ" ያለው::

ቅዱስ ብሶይን ከአንዱ መኮንን ወደ ሌላው እያመላለሱ አሰቃዩት:: አካሉን ቆራረጡት:: ዓይኑን በጋለ ብረት አወጡት:: በምጣድ ቆሉት:: በጋን ውስጥ ቀቀሉት:: እርሱ ግን በፈጣሪው ፍቅር የጸና ነውና ሁሉን ታገሰ:: በነዚሕ ሁሉ የስቃይ ዓመታት ቁራሽ ዳቦ እንኳ አላቀመሱትም:: በረሃብ ቀጡት እንጂ:: ለእርሱ ግን ምግቡ የክርስቶስ ስም ነበር::

በመጨረሻ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ አንገቱን በሰይፍ አስመታው:: ሥጋውንና የተቆረጠ አንገቱን ገንቦ (ጋን) ውስጥ ከቶ ጣለው:: የቅዱሱን አካል የያዘችው ጋን ግን በእግዚአብሔር ቸርነት : ማንም ሳይሸከማት ከመሬት ከፍ አለች:: ለሃያ ቀናት ተጉዛ ከሶርያ ግብጽ (ቦሃ) ደረሰች:: ክርስቲያኖች ተቀብለው ሲከፍቷት የቅዱስ ብሶይ ራሱና አንገቱ ተጣብቆ ተገኝቷል:: በክብርም አሳርፈውታል::

††† ቅዱስ ያዕቆብ †††

††† ዳግመኛ በዚሕ ቀን ጻድቅና ተአማኒ (ታማኝ) የተባለ የምሥራቅ ሰው ቅዱስ ያዕቆብ መታሠቢያ ይደረግለታል::
ቅዱስ ያዕቆብ ቁስጥንጥንያ አካባቢ በርሃ ውስጥ ይኖር የነበረ አባት ነው:: ከቅድሰና ሕይወቱ ባሻገር በደፋርነቱ (ጥብዐቱ) ይታወቃል:: በ340ዎቹ ዓ/ም ታናሹ ቆስጠንጢኖስ አርዮሳዊ በሆነ ጊዜ ይሔ አባት በይፋ ገስጾታል::

በዚህም ምክንያት መከራን ተቀብሏል:: ታስሯል:: ተገርፏል:: እግዚአብሔርም መናፍቁን ንጉሥ ለጦርነት በወጣበት ቀስፎታል:: ቅዱሱ በዚህች ቀን ዐርፎ ወደ ወደደው ክርስቶስ ሔዷል::

††† ቸር አምላክ ከሰማዕቱ ቅዱስ ብሶይ እና ከቅዱስ ያዕቆብ በረከት ያሳትፈን:: በምልጃቸውም ይቅር ይበለን::

††† ሰኔ 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አባ ብሶይ (ኃያል ሰማዕት)
2.ቅድስት ማርታ ለባሲተ ክርስቶስ (በቅድስናዋ የተወደሰች : በስደት ያረፈች እናት ናት::)
3.ቅዱስ ያዕቆብ ምሥራቃዊ
4.ቅዱስ ቢፋሞን ሰማዕት
5.ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት
6.ቅዱስ መርቆሬዎስና ማኅበሩ (ሰማዕታት)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ
3.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
4.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮጵያዊ
5.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
6.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ)

††† "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ : ወይስ ጭንቀት : ወይስ ስደት : ወይስ ራብ : ወይስ ራቁትነት : ወይስ ፍርሃት : ወይስ ሰይፍ ነውን?
"ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቈጠርን" ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው::
በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" †††
(ሮሜ. ፰፥፴፭-፴፰)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ):
#Feasts of #Senne_5

✞✞✞On this day we commemorate the Departure of Saint Bshay (Ebsoy) the Great Martyr✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Abba Bshay (Ebsoy) the Martyr✞✞✞
=>Our holy father was one of the sweet fruits of the Era of Persecution. And he takes precedence from many of them.

✞If asked about his life, it was as follows.

✞At the end of the 3rd century, there were Christians named Tagestas and Karisa. And while they lived on the righteous path, they were not able to bear a child for seventeen years after marriage.

✞And God, Who saw their seventeen years of plea, sent St. Gabriel and he announced to them and said, “As the child [that you will bore] is chosen to be a martyr, call him Bshay.” And seven years after Bshay was born, his parents took him to a monastery so that he could study. After he studied the Scriptures, he was ordained a deacon. And when they asked him to return to the city, he said “No”.
  
✞[And in the monastery] he lived with his friend, St. Peter, for twenty one years in virginity and in spiritual struggle by making fasting and prayer their routines. And when St. Bshay became twenty eight years old, the era about which the archangel prophesized came to be. And many of the faithful were slaughtered for just being Christians. And some were thrown into fires while others that feared death fled to the wilderness. 

✞And St. Bshay, being accused by people that knew him, was brought before a court. And suddenly, St. Gabriel the Archangel, who hastens for aid, descended from heaven and told him, “Do not worry! I will be with you until the end.”

✞And the officer in charge tried to persuade the Saint to renounce Christ. However, the Saint told the officer that the idols were the abodes of demons upfront and in public. And because the official was angered, he ordered soldiers to press him (with a henbaz). And they lashed him while his blood poured. Then, they threw him after crushing his flesh in between two metal pieces. Thereafter, the Archangel appeared, touched [his wounds], and healed him.
 
✞And the officer grew tired of torturing the Saint. The life of the saints is awe inspiring! While the tortured is there, the oppressor gets tired and while the suffering is there, the one inflicting the pain becomes weary.
  
✞I think that is why Aba Tsegie Dengel said,
“Virgin, enthralled by your Son’s fragrance
The one that is at the square of the martyrs
While stoned, feels the rocks as hulls
And the flames become as the waters of the cold seas”

✞The tormentors tortured St. Bshay by sending him back and forth from one official to another. And they cut his body to pieces, took out his eyes with hot metal rods, roasted him on iron beds and boiled him as well. Nonetheless, he endured all as he was steadfast in the love of his Creator. And in all those years of trials, his oppressors did not even give him a piece of bread, instead they made him suffer from hunger. However, for the Saint, the name of Christ was food.

✞Finally, Emperor Diocletian had him beheaded.  And he placed the Saint’s severed body and head in a vessel and plunged it. But the vessel, which had the Saint’s body, by the mercy of God, without being carried by anyone, was elevated from the ground. And it travelled for twenty days from Syria and reached Egypt (Boha). And when Christians found and opened it, they saw St. Bshay’s head and neck joined [miraculously]. And they buried him with honors.
 
✞✞✞Saint James/Jacob✞✞✞
=>Also on this day, St. James of the East, the righteous and faithful, is commemorated. 

✞St. James was a father that lived in a desert near Constantinople. This father is known, besides his holy life, for his courage. In the 340s when Constantine the Younger became an Arian, this father rebuked him publicly.✞And because of this, he endured trials. He was imprisoned and lashed. Thus, God smote the heretical Emperor [for the affliction he brought upon the Saint] where he went to do battle.
The Saint passed away on this day and went to Christ, Whom he loved.

✞✞✞May the Good God make us partakers of the blessings of St. Bshay the Martyr and St. James. And may He forgive us through their intercessions.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 5th of Senne
1. St. Abba Bshay (Great Martyr)
2. St. Martha who had put on Christ (A mother Praised for her holiness who departed in exile.) 
3. St. James of the East
4. St. Bifamon the Martyr
5. St. Macarius the Martyr
6. St. Mercurius and his followers (Martyrs)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Peter Arch-Apostle (First among the apostles)
2. St. Paul, Light of the World
3. Abune Gebre Menfes Qidus
4. St. Yohani the Ethiopian
5. St. Amoni of Nah(i)so
6. St. Eugenia (Martyr and Righteous)

✞✞✞“Who shall separate us from the love of Christ? shall tribulation, or distress, or persecution, or famine, or nakedness, or peril, or sword? As it is written, For thy sake we are killed all the day long; we are accounted as sheep for the slaughter. Nay, in all these things we are more than conquerors through him that loved us.”✞✞✞
Rom. 8:35-37

✞✞✞Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊
(ማቴ ፫:፫)

በአማን ተንሥአ መድኃኒነ!
🌿ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።

ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።

🌿ወልደ እግዚአብሔር አምላክነ ወመድኃኒነ ዕቀብ  ሕይወተነ እም ገሀነመ እሳት ወእምኵሉ መንሱት በእንተ ቅዱስ ስምከ ወበእንተ ማርያም እምከ ወበእንተ ቅዱስ መስቀል ወበእንተ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ ወበእንተ ኵሎሙ ቅዱሳን ወሀባ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተክርስቲያን።

ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙኅ ትዕግሥት። ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኩሉ ሰዓት እንበለ ንስሐ ኪያነ ኢይንሣእ ሞት።

🌿አንቅሐኒ በጽባሕ ክሥተኒ ዕዝንየ በዘአጸምእ አምላኪየ አምላኪየ እገይሥ ኀቤከ ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ"

ነቢያት ወሐዋርያት፥ ጻድቃን ወሰማዕት፤ ደናግል ወመነኮሳት፥ አዕሩግ ወሕጻናት፤ ገዳማውያን ወሊቃውንት፤ ሰአሉ ለነ ኲልክሙ፥ ቅድመ መንበሩ ለጸባኦት።

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ዘብሔረ ጎንደር ዲ ዮርዳኖስ አበበ /com.zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
Audio
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊 (ማቴ ፫:፫)


ርዕስ፦📝"" ጣዖትን አታምልኩ! ""
                  (፩ ቆሮ. ፲:፯)
ተግሳጽ
📅(ሰኔ 2- 2016)

🎤 በመምህር ዲ/ዮርዳኖስ አበበ

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ዜና እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)

🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ዘብሔረ ጎንደር ዲ ዮርዳኖስ አበበ /com.zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
2024/06/12 00:09:29
Back to Top
HTML Embed Code: