Telegram Group Search
"ሁሉም ሰው የርሱ ታሪክ ባልሆነ ነገር ላይ ጠቢብ ነው።" ዓባስ አል-ዒቃድ
በመከራው ያልተገረፈ ሰው ስለትዕግስት ለማውራት ጠቢብ ይሆናል። የድህነትን ህይወት ያላየ ሰው ድሆችን ስለሀብትና ድህነት በመንገር ሊቅ ይሆናል። ፈተናውን ያልተቋደሰ ሰው ስለፅናት በመምከር አዋቂ ይሆናል። ሁሉም ባልደረሰበት የችግር ህይወትና ታሪክ ውስጥ ጉምቱ ጠቢብ ነው።

@Qteloch
∴…… join……∵
@qteloch'
"ያሳዝናል! ነገሩ የተወሰኑ ቀናት ይሆንና ያልፋል ብዬ አስቤ ነበር። ግን ህይወቴ ሆነ።" ዱስቶቪስኪ

አንዳንዴ… ብዙም የማንኖርባቸውና መሻገሪያችን የሚመስሉን ነገሮች ራሳቸው መዳረሻችንም ይሆናሉ። ድንገት የተፈጠሩ ናቸው እንልና ዝንተዓለሙን እነርሱ ውስጥ እንኖራለን። ለተወሰኑ ቀናት አስበን እንጀምራቸውና የህይወታችን ክፍል ሆነው ይቆያሉ። የጓደኝነት ህይወት፣ የስራ ዓይነትና ወይም ለሆነ ችግር መፍትሄ ያደረጋችሁትን አስቡ። ብዙዎች ለሆኑ ቀናት መታለፍ የተጀመሩ ናቸው፣ አሁን ግን ህይወት ሆነዋል።
@Fuad kheyredin


@Qteloch
፨ Join ፨
@qteloch
"ውብ ቃላቶችን አትመኑ። እውነቱን ከክስተቶች አንደበት ውሰዱ።" ነጂብ መህፉዝ
አንዳንዶቹ ሲያደንቁህ ከሰማይና ከጨረቃ ውበት ጋር ያመሳስሉሃል፣ ውዴታቸውን ሲገልፁልህ ደግሞ ላንተ መስዋዕት እስከመሆን ያዘልቁሃል። ያ ሁሉ የቃል ውዳሴና ውዴታ በፈታኝ ተግባር ውስጥ ግን ኦና ይሆናል። ሁሌም ከጎንህ እንደሆኑ ቢነግሩህም ሲፈልጉህ እንጂ በቁም ነገር ስትፈልጋቸው አታገኛቸውም። ክስተቶች እውነትን ይገልጣሉ። በቃላት የተከሸኑ ውዴታዎችም በአንድ ወቅት በተግባር ይፈተናሉ።
@qteloch
፨Join it፨
@qteloch
"ውድህን ስትፈልገው ውድህ ውዱን ፍለጋ ሄዷል። አንዳንዴ ይህም አለ።"
@Qteloch
@qteloch
አንዳንዶች… ዝም ስትል አዕምሮህ ውስጥ ብዙ ንግግር እንዳለ አይረዱም።
አንዳንዶች… ባላውቃቸው ብለህ ስትጠፋ፣ እንድትረሳቸው አይፈቅዱልህም።
አንዳንዶች… ያንተን ህይወት እነርሱ በኖሩበት መንገድ ብቻ ይለኩታል።
አንዳንዶች… ከክስተቶች መሀል ጠንካራ ስትሆን ምንም የማይሰማው(ስሜት አልባ) አድርገው ያስቡሃል።
አንዳንዶች……

@qteloch
@qteloch
አንዳንድ ያለፉ የህይወት ገፆችን መቅደድ የሚከብደውና አንዳንድ ሰዎችን ከፅሁፉ ውስጥ መሰረዝ የተሳነው ሰው በህይወቱ ውስጥ ብዙ ይሰቃያል፣ ይደክማል።
@Qteloch
@qteloch
"ሁሉም ፕላኔቱን መታደግ ይፈልጋል። ግን ሳህን በማጠብ እናቱን ማገዝ የሚፈልግ ደግሞ ማንም የለም።"
ቻርሊ ቻፕሊን
@qteloch
@qteloch
ልጅ እያለን ወላጆቻችን የማንረዳውን ብዙ ምክር ይነግሩን ነበር። ከዚያም እነዚያን ምክሮች የምናልፍባቸው ቀናት በግልፅ ይተነትኑት ጀመር። "ቀድመን በተረዳነው ኖሮ" ያስብሉናል።
@Qteloch
@qteloch
"የኸዲጃን አይነት እንስት ማግኘት ከሻህ ፣ እንደ ሙሀመድ አይነት ሰው መሆን ይኖርብሃል።"
ሙስጠፋ መህሙድ

በህይወትህ ውስጥ ያልሆንከውን አይነት ሰው ፍለጋ አትኳትን፣ ክፍተትህን የሚሞላልህ ክፋይ እንጂ ምሉዕ ማንነት ሽተህ አትድከም። ምሉዕ ብታገኝ እንኳ አንተ ምሉዕ አይደለህምና። መሻትህ በዓላማ ውስጥ መኖር ከሆነ ህይወትንና አንተን የተረዳ ሰው ይበቃሃል።
Fuad kheyredin
@qteloch
@qteloch
በህይወታችን ውስጥ ብዙ ሰዎችን እናገኛለን። አብዛኞቹ ግን ይሄዳሉ። ጥቂቶቹ ናቸው በልብህ የስክነቱ ዓለም ውስጥ "ፍቅርም ክብርም" ኖሯቸው የሚቀመጡት። ጥቂቶቹ ልባችን ውስጥ የተለየ ክፍል ይኖራቸዋል። የጊዜ አቧራም አያተናቸውም። የዘመን ለውጥም አይፍቃቸውም።
@qteloch
@qteloch
Forwarded from Fuad kheyredin
ከወደዱ…
(ፉአድ ኸይረዲን)

ጨረቃን ናፋቂ አይሸሽም ጨለማን
ብርሃን ፈላጊ፣
ትቀልጣለች ብሎ አይተዋትም ሻማን።

ወዳጅ የተባለ…ውበት ተመልክቶ፣
እሾሁን አይፈራም ፅጌሬዳን ሽቶ።

የተሸነፍክ እንደው
ለሀሳብ እምነቷ ለፀባይዋም ጭምር
ስለቁንጅናዋም ባድናቆትህ ዘምር

ምሉዕ ነገር …
በሰውኛ አዳራሽ
አይገኝም ጭራሽ!
@qelemmrko
Forwarded from Fuad kheyredin (Fuad Kheyredin)
የምትሰራውን ስራ ፅድቅ እንደሆነ ለማብራራት አትሞክር። እነርሱ የማያምፁ የሰባተኛው ሰማይ መልዓክት አይደሉም፣ ከእግሮቻቸው ስርም ገነት የለም። መስራት ያለብህን ብቻ ስራ… በልብህ ሚዛን፣ በእምነትህ መለኪያ!
@qelemmrko
@qelemmrko
Forwarded from Fuad kheyredin (Fuad Kheyredin)
ተፈጥሮ ሆኖ
ብገረምብሽ ባደንቅ መልክሽን
አስተውላለሁ
"ምግባር" የሚሉት የሰው ልክሽን።

ይቻለኛል ወይ?
አንቺን ደፍቼ መልክሽን መዝገን
አይሻልም ወይ?
ከማይፈርስ ውበት ሄዶ መወገን።

የሚያኖረን ምግባር
እርሱን ማመስገን
በርሱ መመስገን።
አይሻልም ወይ?

(ፉአድ ኸይረዲን)
Forwarded from Fuad kheyredin (Fuad Kheyredin)
በፍቅር ውዱዕ
ናፍቆት ሲያቆመው ከስግደቱ በር
"ምን ቸግሮት ነው" የሚልም ነበር
አወይ ሰው መሆን…
አወይ መወጠር
እንዲህ መጠርጠር።

ያንዳንዱ ባሪያ ከፈጣሪው ጋር የያዘው ፍቅር
በችግር እንጂ ለማይመጣ ሰው ያሰኛል "ይቅር"።

"ምን ቸግሮት ነው?"

(ፉአድ ኸይረዲን)

@qelemmrko
👆👆👆Join
Forwarded from Fuad kheyredin (Fuad Kheyredin)
አንዳንዴ የሚያስፈልግህ ዣንጥላ የሚሰጥህ ሰው ሳይሆን አብሮህ የሚበሰብስ ሰው ነው… ስሜትን የመጋራት ሜዳ ከመስጠት ሜዳ ይበልጣል።
@Fuadkheyr
Forwarded from Fuad kheyredin (Fuad Kheyredin)
ዝንተዓለሙን ምርጥ የሆነ ሰው አይገኝም። በባህሪው ምሉዕ የሚባል ፍጡርም የለም። እዚህ…  የሚሞላ ክፍት ቦታና የሚታከም ህመም አለ። እዚያ ደግሞ…  የሚደበቅ ነውርና የሚሰረዝ ጥፋት አለ… አብሮ ለመኖር ስንል። መተራረም እንደሚያስተካክለን ሁሉ… መተላለፍም ፍቅራችንን ያቆየዋል… ሳይበዛ።
@Fuadkheyr
Forwarded from Fuad kheyredin (Fuad Kheyredin)
የሰው ልጅ በከባዱ የሚፈተነው…  መሻቱን በተቃረኑ የአላህ ውሳኔዎች ውስጥ ነው። ሳይፈልጋቸው እንዲሆን በሚገደድባቸው ሁኔታዎች ውስጥ በከባዱ ይፈተናል።  ውስጡ ይንቀጠቀጣል። ከልቡ ጋር ትግል ገጥሞ ለማረጋጋት ይሞክራል።  ግን ግን…  የምር የሆነ  ኢማን እዚህ ቦታ ነው ያለው… የአላህን መሻት ወዶ መቀበል ጋር!!

@Fuadkheyr
@fuadkheyr
2024/06/21 12:21:36
Back to Top
HTML Embed Code: