Telegram Group & Telegram Channel
ቤት ማዘዣ ማንንም በቁጥጥር ሥር ማዋል እንደማይቻል ቢደነግግም፣ ባለሥልጣናት ተጠርጣሪን ያለ ምንም ማስረጃ በቁጥር ሥር እንደሚያውሉ፣ ክስ ሳይመሠረት ለ14 ቀናት እንደሚያቆዩ፣ ፍርድ ቤቶች በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ለሚቀርቡ ክሶች ማስረጃ እንዲቀርብ ግፊት ቢያደርጉም ፖሊስ ተጨማሪ መረጃ እየጠየቀ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ዜጎችን የእስር ጊዜ እንደሚያራዝም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በዋስትና መፈታት መብት ቢሆንም ፖሊስ በዋስትና እንዲፈቱ በፍርድ ቤት ውሳኔ ያገኙ ዜጎችን እንደማይለቅ፣ ይባስ ብሎ ሌላ ተጨማሪ ክስ እንደሚመሠርት የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ በተደጋጋሚ የዋስትና መብቶች እንደሚጣሱ አንዳንዴም እስረኞችን ወደ ክልሎች በማዘዋወር በሌላ ተጨማሪ ወንጀል እንዲጠየቁ እንደሚያደርግ ተጠቅሷል፡፡

መንግሥት ከነሐሴ 2015 ዓ.ም. ወዲህ ተግባራዊ እያደረገ ባለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት መጋዘኖችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ የወጣት ማዕከላትን፣ የግል መኖሪያዎችንና ሌሎች ቦዎታችን ወደ ማቆያነት በመቀየር በሺዎች የሚቆጠሩ የአማራና የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ በተወሰኑ አካባቢዎች ሕፃናትን በወንጀል ተጠርጥረዋል በሚል ጥርጣሬ ብቻ በማቆያ ቦታ እንደሚታገቱ አብራርቷል፡፡

ረዥም ጊዜ የሚወስድ የፍርድ ሒደት፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው እስረኛ፣ ቀልጣፋ ያልሆነ የፍርድ ቤት ውሳኔና ውስን የሰው ኃይል ያላቸው ፍርድ ቤቶች ለፍርድ ሒደት መዘግየት አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በሕጉ መሠረት ፍርድ ቤቶች ነፃና ገለልተኛ እንዲሆኑ ቢጠበቅም፣ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት የፍርድ ቤቶችን ገለልተኛናትና ሚዛናዊነት የማያከብር መሆኑን የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ የፍትሐ ብሔር ችሎቶች በተሻለ በገለልተኝነት ቢሠሩም የወንጀል ጉዳይ ችሎቶች ደካማና በከፍተኛ ሁኔታ የታጨቁና የተጨናነቁ ናቸው ይላል፡፡

የመንግሥት አካላት ከድንበር ያለፈ የማስፈራራት ተግባር ይፈጽማሉ የሚለው ሪፖርቱ፣ ለአብነትም ከሳዑዲ ዓረቢያ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፎ የተሰጠ ጋዜጠኛ ስለመኖሩ አስረድቷል፡፡ በተመሳሳይ በውጭ አገር የሚኖሩ ዳያስፖራ ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ ያሉ ቤተሰቦቻቸው ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰባቸው ነው ብሏል፡፡

ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ የግል ንብረትን መበርበር እንደማይቻል በሕግ የተቀመጠ ቢሆንም መንግሥት ይህንን ፈጽሞ እንደማያከብር ያብራራል፡፡

መንግሥት የፖለቲከኞችንና የግለሰቦችን ስልክ በአቅጣጫ ጠቋሚ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችና በኢንተርኔት የታገዘ የኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎችን በመጠቀም፣ የመጥለፍ ሥራ ላይ መሰማራቱ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

የመንግሥት አካላት እ.ኤ.አ. ከ2021 ጀምሮ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ዜጎችን ስልክ ለመበርበር የሚረዳ ሰለብራይት ከተባለ የእስራኤል ኩባንያ የስለላ መሣሪያ ገዝቶ ሥራ ላይ ማዋሉን፣ የኦንላይን የመረጃ ምንጭ የሆኑ ድረ ገጾችንና ኢንተርኔት በተደጋጋሚ መዝጋቱንና ለዚህም ይግባኝና አቤቱታ የሚጠየቅበት መንገድና አሠራር አለመኖሩን አብራርቷል፡፡

የመንግሥትን አሠራር አጥብቀው የሚጠይቁ የሰብዓዊ መብቶችና የሚዲያ ተቋማት ቢሮዎች ተሰብሮ መገባቱን፣ የሚዲያና የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት ላይ የሚፈጸምን ዝርፊያ በተመለከተ ምርመራ እንዲያካሂድ መንግሥት ቢጠይቅም እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ምን ዓይነት ዕርምጃ እንደወሰደ ማወቅ አልተቻለም ብሏል፡፡

የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ የሚነሱ የሰብዓዊ ዕርዳታዎች አቀራረብና የፀጥታ ሁኔታውን በተመለከተ አስተያየት የሚሰጡ ጋዜጠኞች፣ የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ሌሎችንም አስገድዶ እንደሚያስር በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በርካታ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞችን በበቀል ዕርምጃ በወንጀል ክሶች በተለይም ከፅንፈኝነትና ከአሸባሪነት ጋር በተገናኘ በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው በኋላ፣ በቁጥጥር ሥር በዋሉበት ጉዳይ ሳይጠየቁ የጋዜጠኝነት ሥራቸውን ስላከናወኑ ብቻ ለተወሰነ ጊዜ ታስረው እንደሚለቀቁ፣ ይህም የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋዜጠኞችን አፋቸውን ለማዘጋትና ፍራቻን ለመልቀቅ የሚጠቀሙበት ሥልት በመሆኑ ነው ሲል ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በኢትዮጵያ በቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ የመንግሥት ተፅዕኖ መስፋቱን የገለጸው ሪፖርቱ፣ በኢትዮ ቴሌኮም አማካይነት የኦንላይን ሚዲያ በአገር አቀፍ ደረጃ እየዘረጋ ነው ብሏል፡፡

ዕውቅና ያልተሰጣቸው ሰላማዊ ሠልፎች የወንጀል ዕርምጃ እንደሚያስከትሉ የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ሰላማዊ ሠልፎችን ማድረግ ያልተለመደ ተግባር መሆኑን፣ ሰላማዊ ሠልፎች ከተካሄዱ ግን የፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ ለውጥ መኖሩ ማሳያ ስለመሆኑ ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡

ሕጉ በአገር ውስጥ መንቀሳቀስ፣ የውጭ አገሮች ጉዞ ማድረግ፣ መሰደድና መመለስን የሚያከብር ቢሆንም መንግሥት የዜጎችን እንቅስቃሴ በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ ጉዞዎች ላይ ክልከላና ገደብ ስለማስቀመጡ ያወሳል፡፡ በአገር ውስጥ ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል በሚደረጉ ጉዞዎች በተለይም ትግራይ፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝና ምዕራብ ወለጋ አካባቢዎች መንቀሳቀስ የማይቻል ነው ይላል፡፡ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት በርካታ የኬላ መቆጣሪያዎች በተለይ ክልሎችን በሚያገናኙ መንገዶች መኖራቸው፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ለማከናወን እንዳይቻል ስለማድረጉ አብራርቷል፡፡

ሪፖርቱ እ.ኤ.አ. በ2023 የኦሮሚያ ክልልና የፌዴራል ፖሊስ በሕዝብ በዓላትና መሰል ጉዳዮች ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ ጉዞዎችን የፀጥታ ሥጋት በሚል ሰበብ ከከተማ ውጭ የሚመጡ ዜጎች እንዳይገቡ ገደብ ስለመጣላቸው አውስቷል፡፡ በዚህ ገደብ የተነሳ በአመዛኙ ከጎጃምና ከጎንደር የአማራ ክልል ከተሞች የሚመጡ ወጣቶች ላይ ያተኮረ እንደነበር አስረድቷል፡፡ በተመሳሳይ ወደ ውጭ አገር የሚጓዙ ግለሰቦች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ያለ ምንም ትዕዛዝ ከአገር እንዳይወጡ እንደሚከልከሉ አመላክቷል፡፡ ለአብነትም የቀድሞ የአማራ ልዩ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ለሕክምና ወደ እስራኤል ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ በፀጥታ ኃይሎች መሰረዙን አስታውሷል፡፡

መንግሥት እ.ኤ.አ. ከ2020 ጀምሮ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ለጥገኝነት የሚመጡ ዜጎችን መመዝገብ ማቆሙን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ድርጅት ማስታወቁን ጠቅሶ በዚህም የተነሳ ያልተመዘገቡ ኤርትራውያን ጥገኝነት ፈላጊዎች ቁጥር ማሻቀቡንና እንደ ስደተኛ ባለመመዝገባቸው ምንም ዓይነት አቅርቦት እንደማይደርሳቸው ጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ኤርትራውያንን መመዝገብ ቢያቆምም ለ40 ሺሕ ሱዳናውያንና ለ100 ሺሕ የሶማሌላንድ ዜጎች የጥገኝነት ምዝገባ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ በተጨማሪም የጥገኝነት ምዝገባ ተደርጎላቸው የሚኖሩ ሰዎች የመንቀሳቀስ መብታቸው የተገደበ ነው ይላል፡፡

በአገሪቱ ሕግ በሙስና ድርጊት የተሳተፉ አካላት በወንጀል እንደሚጠየቁ የተደነገገ ቢሆንም፣ መንግሥት ሕጉን በሚገባው መጠን እንደማይተገብረው ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡

የተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ሰብዓዊ መብቶችን በተመለከተ የሚያከናውናቸው ተግባራት፣ በማያቋርጥ የደኅንነት ሥጋትና ገደብ የተነሳ ምርመራ አካሂደው ለሕዝብ ይፋ ለማድረግ እንደሚቸገሩ ጠቅሷል፡፡ የአገር ውስጥ ድርጅቶች በተደጋጋሚ፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ድገሞ አልፎ አልፎ ከፀጥታ አካላት ማስፈራሪያና ዛቻ እንደሚደርሰባቸውና  በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡

ሪፖርቱ ዓለም አቀፍና አገር አቀፍ የዕርዳታ ድርጀቶች፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማትና ዲፕሎማቶችና በተለዩ ቦታዎች እንዳይንቀሳቀሱ ገደብ እንደሚጣልባቸው ሪፖርቱ ያብራራል፡፡

አስገድዶ መድፈር



tg-me.com/wedefkr/15922
Create:
Last Update:

ቤት ማዘዣ ማንንም በቁጥጥር ሥር ማዋል እንደማይቻል ቢደነግግም፣ ባለሥልጣናት ተጠርጣሪን ያለ ምንም ማስረጃ በቁጥር ሥር እንደሚያውሉ፣ ክስ ሳይመሠረት ለ14 ቀናት እንደሚያቆዩ፣ ፍርድ ቤቶች በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ለሚቀርቡ ክሶች ማስረጃ እንዲቀርብ ግፊት ቢያደርጉም ፖሊስ ተጨማሪ መረጃ እየጠየቀ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ዜጎችን የእስር ጊዜ እንደሚያራዝም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በዋስትና መፈታት መብት ቢሆንም ፖሊስ በዋስትና እንዲፈቱ በፍርድ ቤት ውሳኔ ያገኙ ዜጎችን እንደማይለቅ፣ ይባስ ብሎ ሌላ ተጨማሪ ክስ እንደሚመሠርት የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ በተደጋጋሚ የዋስትና መብቶች እንደሚጣሱ አንዳንዴም እስረኞችን ወደ ክልሎች በማዘዋወር በሌላ ተጨማሪ ወንጀል እንዲጠየቁ እንደሚያደርግ ተጠቅሷል፡፡

መንግሥት ከነሐሴ 2015 ዓ.ም. ወዲህ ተግባራዊ እያደረገ ባለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት መጋዘኖችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ የወጣት ማዕከላትን፣ የግል መኖሪያዎችንና ሌሎች ቦዎታችን ወደ ማቆያነት በመቀየር በሺዎች የሚቆጠሩ የአማራና የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ በተወሰኑ አካባቢዎች ሕፃናትን በወንጀል ተጠርጥረዋል በሚል ጥርጣሬ ብቻ በማቆያ ቦታ እንደሚታገቱ አብራርቷል፡፡

ረዥም ጊዜ የሚወስድ የፍርድ ሒደት፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው እስረኛ፣ ቀልጣፋ ያልሆነ የፍርድ ቤት ውሳኔና ውስን የሰው ኃይል ያላቸው ፍርድ ቤቶች ለፍርድ ሒደት መዘግየት አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በሕጉ መሠረት ፍርድ ቤቶች ነፃና ገለልተኛ እንዲሆኑ ቢጠበቅም፣ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት የፍርድ ቤቶችን ገለልተኛናትና ሚዛናዊነት የማያከብር መሆኑን የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ የፍትሐ ብሔር ችሎቶች በተሻለ በገለልተኝነት ቢሠሩም የወንጀል ጉዳይ ችሎቶች ደካማና በከፍተኛ ሁኔታ የታጨቁና የተጨናነቁ ናቸው ይላል፡፡

የመንግሥት አካላት ከድንበር ያለፈ የማስፈራራት ተግባር ይፈጽማሉ የሚለው ሪፖርቱ፣ ለአብነትም ከሳዑዲ ዓረቢያ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፎ የተሰጠ ጋዜጠኛ ስለመኖሩ አስረድቷል፡፡ በተመሳሳይ በውጭ አገር የሚኖሩ ዳያስፖራ ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ ያሉ ቤተሰቦቻቸው ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰባቸው ነው ብሏል፡፡

ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ የግል ንብረትን መበርበር እንደማይቻል በሕግ የተቀመጠ ቢሆንም መንግሥት ይህንን ፈጽሞ እንደማያከብር ያብራራል፡፡

መንግሥት የፖለቲከኞችንና የግለሰቦችን ስልክ በአቅጣጫ ጠቋሚ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችና በኢንተርኔት የታገዘ የኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎችን በመጠቀም፣ የመጥለፍ ሥራ ላይ መሰማራቱ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

የመንግሥት አካላት እ.ኤ.አ. ከ2021 ጀምሮ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ዜጎችን ስልክ ለመበርበር የሚረዳ ሰለብራይት ከተባለ የእስራኤል ኩባንያ የስለላ መሣሪያ ገዝቶ ሥራ ላይ ማዋሉን፣ የኦንላይን የመረጃ ምንጭ የሆኑ ድረ ገጾችንና ኢንተርኔት በተደጋጋሚ መዝጋቱንና ለዚህም ይግባኝና አቤቱታ የሚጠየቅበት መንገድና አሠራር አለመኖሩን አብራርቷል፡፡

የመንግሥትን አሠራር አጥብቀው የሚጠይቁ የሰብዓዊ መብቶችና የሚዲያ ተቋማት ቢሮዎች ተሰብሮ መገባቱን፣ የሚዲያና የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት ላይ የሚፈጸምን ዝርፊያ በተመለከተ ምርመራ እንዲያካሂድ መንግሥት ቢጠይቅም እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ምን ዓይነት ዕርምጃ እንደወሰደ ማወቅ አልተቻለም ብሏል፡፡

የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ የሚነሱ የሰብዓዊ ዕርዳታዎች አቀራረብና የፀጥታ ሁኔታውን በተመለከተ አስተያየት የሚሰጡ ጋዜጠኞች፣ የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ሌሎችንም አስገድዶ እንደሚያስር በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በርካታ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞችን በበቀል ዕርምጃ በወንጀል ክሶች በተለይም ከፅንፈኝነትና ከአሸባሪነት ጋር በተገናኘ በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው በኋላ፣ በቁጥጥር ሥር በዋሉበት ጉዳይ ሳይጠየቁ የጋዜጠኝነት ሥራቸውን ስላከናወኑ ብቻ ለተወሰነ ጊዜ ታስረው እንደሚለቀቁ፣ ይህም የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋዜጠኞችን አፋቸውን ለማዘጋትና ፍራቻን ለመልቀቅ የሚጠቀሙበት ሥልት በመሆኑ ነው ሲል ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በኢትዮጵያ በቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ የመንግሥት ተፅዕኖ መስፋቱን የገለጸው ሪፖርቱ፣ በኢትዮ ቴሌኮም አማካይነት የኦንላይን ሚዲያ በአገር አቀፍ ደረጃ እየዘረጋ ነው ብሏል፡፡

ዕውቅና ያልተሰጣቸው ሰላማዊ ሠልፎች የወንጀል ዕርምጃ እንደሚያስከትሉ የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ሰላማዊ ሠልፎችን ማድረግ ያልተለመደ ተግባር መሆኑን፣ ሰላማዊ ሠልፎች ከተካሄዱ ግን የፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ ለውጥ መኖሩ ማሳያ ስለመሆኑ ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡

ሕጉ በአገር ውስጥ መንቀሳቀስ፣ የውጭ አገሮች ጉዞ ማድረግ፣ መሰደድና መመለስን የሚያከብር ቢሆንም መንግሥት የዜጎችን እንቅስቃሴ በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ ጉዞዎች ላይ ክልከላና ገደብ ስለማስቀመጡ ያወሳል፡፡ በአገር ውስጥ ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል በሚደረጉ ጉዞዎች በተለይም ትግራይ፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝና ምዕራብ ወለጋ አካባቢዎች መንቀሳቀስ የማይቻል ነው ይላል፡፡ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት በርካታ የኬላ መቆጣሪያዎች በተለይ ክልሎችን በሚያገናኙ መንገዶች መኖራቸው፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ለማከናወን እንዳይቻል ስለማድረጉ አብራርቷል፡፡

ሪፖርቱ እ.ኤ.አ. በ2023 የኦሮሚያ ክልልና የፌዴራል ፖሊስ በሕዝብ በዓላትና መሰል ጉዳዮች ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ ጉዞዎችን የፀጥታ ሥጋት በሚል ሰበብ ከከተማ ውጭ የሚመጡ ዜጎች እንዳይገቡ ገደብ ስለመጣላቸው አውስቷል፡፡ በዚህ ገደብ የተነሳ በአመዛኙ ከጎጃምና ከጎንደር የአማራ ክልል ከተሞች የሚመጡ ወጣቶች ላይ ያተኮረ እንደነበር አስረድቷል፡፡ በተመሳሳይ ወደ ውጭ አገር የሚጓዙ ግለሰቦች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ያለ ምንም ትዕዛዝ ከአገር እንዳይወጡ እንደሚከልከሉ አመላክቷል፡፡ ለአብነትም የቀድሞ የአማራ ልዩ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ለሕክምና ወደ እስራኤል ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ በፀጥታ ኃይሎች መሰረዙን አስታውሷል፡፡

መንግሥት እ.ኤ.አ. ከ2020 ጀምሮ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ለጥገኝነት የሚመጡ ዜጎችን መመዝገብ ማቆሙን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ድርጅት ማስታወቁን ጠቅሶ በዚህም የተነሳ ያልተመዘገቡ ኤርትራውያን ጥገኝነት ፈላጊዎች ቁጥር ማሻቀቡንና እንደ ስደተኛ ባለመመዝገባቸው ምንም ዓይነት አቅርቦት እንደማይደርሳቸው ጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ኤርትራውያንን መመዝገብ ቢያቆምም ለ40 ሺሕ ሱዳናውያንና ለ100 ሺሕ የሶማሌላንድ ዜጎች የጥገኝነት ምዝገባ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ በተጨማሪም የጥገኝነት ምዝገባ ተደርጎላቸው የሚኖሩ ሰዎች የመንቀሳቀስ መብታቸው የተገደበ ነው ይላል፡፡

በአገሪቱ ሕግ በሙስና ድርጊት የተሳተፉ አካላት በወንጀል እንደሚጠየቁ የተደነገገ ቢሆንም፣ መንግሥት ሕጉን በሚገባው መጠን እንደማይተገብረው ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡

የተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ሰብዓዊ መብቶችን በተመለከተ የሚያከናውናቸው ተግባራት፣ በማያቋርጥ የደኅንነት ሥጋትና ገደብ የተነሳ ምርመራ አካሂደው ለሕዝብ ይፋ ለማድረግ እንደሚቸገሩ ጠቅሷል፡፡ የአገር ውስጥ ድርጅቶች በተደጋጋሚ፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ድገሞ አልፎ አልፎ ከፀጥታ አካላት ማስፈራሪያና ዛቻ እንደሚደርሰባቸውና  በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡

ሪፖርቱ ዓለም አቀፍና አገር አቀፍ የዕርዳታ ድርጀቶች፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማትና ዲፕሎማቶችና በተለዩ ቦታዎች እንዳይንቀሳቀሱ ገደብ እንደሚጣልባቸው ሪፖርቱ ያብራራል፡፡

አስገድዶ መድፈር

BY አርማጌዶን


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/wedefkr/15922

View MORE
Open in Telegram


አርማጌዶን Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Importantly, that investor viewpoint is not new. It cycles in when conditions are right (and vice versa). It also brings the ineffective warnings of an overpriced market with it.Looking toward a good 2022 stock market, there is no apparent reason to expect these issues to change.

አርማጌዶን from us


Telegram አርማጌዶን
FROM USA