Telegram Group & Telegram Channel
አምስት፣ አምስት ደረጃ ያላቸው የኒሻን ዓይነቶችን አቋቁሟል፡፡

ዝርዝሩን በተለይም አሁን ላይ ሆኖ ለሚያየው በጣም ይደንቃል፣ ይገርማል፡፡ መንግሥትና ሕግ በእንዲህ ያለ ጉዳይ እንዲህ ‹‹ሥራ ይፈታሉ?›› ጉልበትና ገንዘብ ያባክናሉ? ያሰኛል፡፡ ለምሳሌ የማኅተመ ሰሎሞን ማዕረግ የሚባለው ኒሻን የመጀመርያው ዓይነት ባዝግና (ኮለር) በተለይ ለማን እንደተወሰነ (ለንጉሠ ነገሥቱና ለእቴጌዪቱ የተመደበ መሆኑን)፣ ንጉሠ ነገሥቱ በልዩ አስተያየታቸው ለንጉሣዊ ቤተ ዘመዳቸውና ለውጭ አገር ነገሥታት፣ እንዲሁም ደግሞ እጅግ ከፍ ያለ አገልግሎት ላላቸው ሰዎች የሚሰጥ እግጅ በጣም የከበረ ሽልማት መሆኑ ተደንግጓል፡፡ የእያንዳንዱ ምሥልና ቅርፅ ከተጓዳኝ ዝርዝሮች ጋር በሕግ ተወስኗል፡፡ የእያንዳንዱ የኒሻን ዓይነትና ማዕረግ በተለይም የማኅተመ ሰሎሞን፣ የንግሥተ ሳባ ማዕረግ ኒሻኖች ተሸላሚዎች ቁጥር ከተወሰነ ቁጥር እንዳይበልጥ በሕግ ተደንግጓል፡፡ ከሦስት፣ ከአሥር፣ ከ20 … ፣ ከ45፣ ከ55 አይበልጥም ተብሎ በሕግ ተከልክሏል (በነገራችን ላይ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታኅሳስ 2 ቀን 1940 ዓ.ም. ለፊልድ ማርሻል ሞንትጎመሪ የሸለሟቸው ታላቁን የሰሎሞን ኒሻንን ነው)፡፡

ይህ የክብርና የማዕረግ የሽልማት ሥርዓት በመላው የንጉሠ ነገሥቱ የሥልጣን ዘመን ዘለቀ፡፡ ከመስከረም 1967 ዓ.ም. ጀምሮ ሥልጣን የያዘው ወታደራዊ መንግሥት በ1971 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ (ስለቀድሞዎቹ ሜዳይዎችና ኒሻኖች በሕግ በግልጽ ሳይነገር) የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥትን የሜዳይና የኒሻን አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 169/71) አወጀ፡፡ በአዋጁም በሕጉ በዝርዝር በተወሰኑት ሜዳይዎችና ኒሻኖች መሠረት በጦር ሜዳ ሜዳልያዎቹ ዝርዝር ውስጥ፣ የጦር ሜዳ ሜዳልያዎችና ዓርማ የሚባሉት የኅብረተሰባዊ ኢትዮጵያ ወደር የሌለው ጀግና ሜዳይ፣ የላቀ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ፣ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ሦስተኛ ደረጃና የጦር ሜዳ ቁስለኛ ሜዳይ፣ እንዲሁም የአብዮታዊ ዘማች ዓርማ የሚባሉ ተደንግገዋል፡፡ እነዚህ የሜዳይ ሽልማቶች ለማንና ምን ለፈጸመ እንደሚሰጡና ተሸላሚውም የሚያገኘው ልዩ መብት በዝርዝር ተወስኗል፡፡

በዚሁ ፈርጅ ውስጥ የተወሰኑ የሥራና የአገልግሎት ሜዳልያዎችም አሉ፡፡ የኅብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ የሥራ ጀግና ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የከፍተኛ ውትድርና አገልግሎት ሜዳይ፣ የብሔራዊ አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የውትድርና አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የፖሊስነት አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ እንዲሁም የአገልግሎት ዘመን ሪባን የሚባሉ አሉ፡፡ ሕጉ የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ታላቅ የክብር ኮከብ ኒሻን፣ የየካቲት 1966 አብዮት ኒሻን (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የቀይ ባህር ኒሻን (ባለሦስት ደረጃዎች)፣ የጥቁር ዓባይ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ)፣ የአፍሪካ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ) የሚባሉ የኒሻን ዓይነቶችንም መሥርቷል፡፡ እነዚህ ሁሉ ለማን እንደሚሰጡ፣ የሚያገኘው ሰው የሚኖረው ልዩ መብት፣ የሜዳሊያዎቹና የኒሻኖቹ ቅርፅ፣ መጠንና አካል ምንነት በዝርዝር ተደንግጓል፡፡ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ኮሚሽንም ተቋቁሟል፡፡ ከርዕሰ ብሔሩ ፈቃድ ሳያገኝ ኢትዮጵያዊ የውጭ አገር ሜዳይ ወይም ኒሻን መቀበል የተከለከለ መሆኑም ተደንግጓል፡፡ ይህም የአገር ሕግ ሆኖ እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ ዘለቀ፡፡ ደርግ ወደቀ፡፡ ኢሕአዴግ መጣ፡፡

በኢሕአዴግ የሥልጣን ዘመን በወታደራዊው ዘርፍ እንኳን የሜዳይ፣ የኒሻንና የሽልማት ጉዳይ የመከላከያ ሠራዊት የ1987 ዓ.ም. አዋጅ ውስጥ የተካተተው በ1990 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ በአዋጅ ቁጥር 123/1990 (የመከላከያ ሠራዊት ማሻሻያ አዋጅ) ነው፡፡ በዚህ ሕግ የዓድዋ ድል ሜዳይ የሚባል ወደር የሌለው ጀግንነት በዓውደ ውጊያ ለፈጸመ ኢትየጵያዊ ግለሰብ ወይም የሠራዊት አሃድ ወይም ቡድን የሚሰጥ የመጨረሻ ከፍተኛ የጀግና ሽልማት ሆኖ የተቋቋመውን ጨምሮ የተለያዩ የሜዳሊያዎች፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ሽልማቶች ተመሠረቱ፡፡

ፖሊስን የሚመለከት የሜዳይ፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ነገር በቀዳማዊ ሕግ ደረጃ (ፓርላማ በሚያወጣው ሕግ) የተነሳው ገና አሁን በቅርቡ በ2004 ዓ.ም. በአዋጅ ቁጥር 720 ነው፡፡ እሱም ለፖሊስ አባላት የሚሰጡ ሜዳዮች፣ ሪባኖችና የምስክር ወረቀቶች በፌዴራል ፖሊስ መተዳደሪያ ደንብ ይወሰናል ሲል ወሰነ፡፡ በዚህም መሠረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 268/2005 የጀግንነት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የላቀ ሥራ ውጤት ሜዳይ፣ የፖሊስ አገልግሎት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ) እና የፖሊስ አገልግሎት ሪባን የሚባሉ የሽልማት ዓይነቶችን አቋቋመ፡፡

አገር ባለውለታነቷን ከምታረጋግጥበት፣ ውለታዎችን ከምትስታውስበትና ለወደፊትም እንዲበረታቱ ከምታደርግበት መንገዶች አንዱ ይህ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ሥርዓት የአገሪቱን ያህል ረዥም ዘመን ያለው ቢሆንም፣ ተከታታይ መንግሥታት እየወረሱ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ባህልና የአገር ሀብት አልሆነም፡፡ ይህ ሳያንስ የተከታታይ መንግሥታት ይህንን የመንግሥት ታላቅ ሥራ የሚከናወንበትን የሕግና የተቋም ጎዶሎ፣ ቶሎና ወዲያውኑ መሙላት አለመቻላቸው፣ በተለይም በዚህ የኢሕአዴግ መንግሥት ዘመን እንደተመሰከረው አወቅነውም፣ አላወቅነውም ብሔራዊ/የአገር ማፈሪያ እየሆነ ነው፡፡ እስካሁን እንደተመለከትነው በኢሕአዴግ/በኢፌዴሪ መንግሥት የመከላከያው ጎን (የፖሊስን ጨምሮ) የሜዳይና የኒሻን ሽልማት እንኳን የተሟላው ከረዥም ጊዜ ግዴለሽነትና ቸልተኝነት በኋላ ነው፡፡ አገር ባለውለታዊነቷን የምትገልጽበትና የምታረጋገጥበት የሲቪል የመንግሥት ሽልማት ሥርዓት ግን ዛሬም ያልተሟላ ጎዶሏችን ነው፡፡

የሚሰማ ስለሌለ፣ ደንገጥ የሚልና የሚደንቀው ሰው ስለጠፋ እንጂ፣ ጉዳዩ በተለይም ጎልቶ የተነሳው የኢትዮጵያ ሚሊኒየም በተከበረበት ወቅት ‹‹ለማይመለስ ውለታህ …›› (የተሟላ ትክክለኛ መጠሪያው ምን እንደተባለ እርግጠኛ አይደለሁም) የሚል ዓይነት አስቀድሞ በሕግ ያልተቋቋመ ሜዳሊያ ስንሰጥ/ሰጠን ስንል ነው፡፡

ከዚያ በፊትና ከዚህ ወዲህም ባለሥልጣኑና ሥልጣን አለኝ የሚለው ሁሉ እየተነሳ ‹‹የከተማውን ቁልፍ››፣ ‹‹የክብር ዜግነት›› ሲሰጥ ዓይተናል፡፡ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥና አጠራርም ጭምር በጣም ግራ የተጋባና መሳቂያ ሆኖ አርፎታል፡፡ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸውን እነዚህን ቁምነገሮች የሚገዙ ሥርዓትና አሠራር መዘርጋት፣ ለመንግሥትና ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለምን የቸገረ ነገር ይሆናል፡፡

ያኔ ፕሬዚዳንት ኦባማ በአቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአስተዳደር ዘመን ኢትዮጵያን ሲጎበኙ በአጋጣሚው ‹‹ማሳሰቢያ›› ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ ኢትዮጵያ ለዜጋም ሆነ ለውጭ ሰው የምትሰጠው የሲቪል ሜዳሊያ ወይም ኒሻን ወይም ሌላ በሕግ የተቋቋመ ሽልማት የሌላት መሆኑን ነበር፡፡ ያ ከሆነ በኋላ ሚያዝያ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ለአቶ ኃይለ ማርያምና ለባለቤታቸው ‹‹ሜዳሊያ›› እና ‹‹የአገሪቱ ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጡ ዓይተናል፡፡ ከዚያም በኋላ አሁን ለዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ለተሰናባቹ የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት (ለባለቤታቸውም) ‹‹ኒሻን›› እና ‹‹ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጣቸው መስክረናል፡፡

ሽልማቱ በተሰጠበት የሥር ምክንያት ላይ ተቃውሞም ሆነ



tg-me.com/wedefkr/15924
Create:
Last Update:

አምስት፣ አምስት ደረጃ ያላቸው የኒሻን ዓይነቶችን አቋቁሟል፡፡

ዝርዝሩን በተለይም አሁን ላይ ሆኖ ለሚያየው በጣም ይደንቃል፣ ይገርማል፡፡ መንግሥትና ሕግ በእንዲህ ያለ ጉዳይ እንዲህ ‹‹ሥራ ይፈታሉ?›› ጉልበትና ገንዘብ ያባክናሉ? ያሰኛል፡፡ ለምሳሌ የማኅተመ ሰሎሞን ማዕረግ የሚባለው ኒሻን የመጀመርያው ዓይነት ባዝግና (ኮለር) በተለይ ለማን እንደተወሰነ (ለንጉሠ ነገሥቱና ለእቴጌዪቱ የተመደበ መሆኑን)፣ ንጉሠ ነገሥቱ በልዩ አስተያየታቸው ለንጉሣዊ ቤተ ዘመዳቸውና ለውጭ አገር ነገሥታት፣ እንዲሁም ደግሞ እጅግ ከፍ ያለ አገልግሎት ላላቸው ሰዎች የሚሰጥ እግጅ በጣም የከበረ ሽልማት መሆኑ ተደንግጓል፡፡ የእያንዳንዱ ምሥልና ቅርፅ ከተጓዳኝ ዝርዝሮች ጋር በሕግ ተወስኗል፡፡ የእያንዳንዱ የኒሻን ዓይነትና ማዕረግ በተለይም የማኅተመ ሰሎሞን፣ የንግሥተ ሳባ ማዕረግ ኒሻኖች ተሸላሚዎች ቁጥር ከተወሰነ ቁጥር እንዳይበልጥ በሕግ ተደንግጓል፡፡ ከሦስት፣ ከአሥር፣ ከ20 … ፣ ከ45፣ ከ55 አይበልጥም ተብሎ በሕግ ተከልክሏል (በነገራችን ላይ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታኅሳስ 2 ቀን 1940 ዓ.ም. ለፊልድ ማርሻል ሞንትጎመሪ የሸለሟቸው ታላቁን የሰሎሞን ኒሻንን ነው)፡፡

ይህ የክብርና የማዕረግ የሽልማት ሥርዓት በመላው የንጉሠ ነገሥቱ የሥልጣን ዘመን ዘለቀ፡፡ ከመስከረም 1967 ዓ.ም. ጀምሮ ሥልጣን የያዘው ወታደራዊ መንግሥት በ1971 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ (ስለቀድሞዎቹ ሜዳይዎችና ኒሻኖች በሕግ በግልጽ ሳይነገር) የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥትን የሜዳይና የኒሻን አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 169/71) አወጀ፡፡ በአዋጁም በሕጉ በዝርዝር በተወሰኑት ሜዳይዎችና ኒሻኖች መሠረት በጦር ሜዳ ሜዳልያዎቹ ዝርዝር ውስጥ፣ የጦር ሜዳ ሜዳልያዎችና ዓርማ የሚባሉት የኅብረተሰባዊ ኢትዮጵያ ወደር የሌለው ጀግና ሜዳይ፣ የላቀ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ፣ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ሦስተኛ ደረጃና የጦር ሜዳ ቁስለኛ ሜዳይ፣ እንዲሁም የአብዮታዊ ዘማች ዓርማ የሚባሉ ተደንግገዋል፡፡ እነዚህ የሜዳይ ሽልማቶች ለማንና ምን ለፈጸመ እንደሚሰጡና ተሸላሚውም የሚያገኘው ልዩ መብት በዝርዝር ተወስኗል፡፡

በዚሁ ፈርጅ ውስጥ የተወሰኑ የሥራና የአገልግሎት ሜዳልያዎችም አሉ፡፡ የኅብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ የሥራ ጀግና ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የከፍተኛ ውትድርና አገልግሎት ሜዳይ፣ የብሔራዊ አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የውትድርና አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የፖሊስነት አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ እንዲሁም የአገልግሎት ዘመን ሪባን የሚባሉ አሉ፡፡ ሕጉ የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ታላቅ የክብር ኮከብ ኒሻን፣ የየካቲት 1966 አብዮት ኒሻን (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የቀይ ባህር ኒሻን (ባለሦስት ደረጃዎች)፣ የጥቁር ዓባይ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ)፣ የአፍሪካ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ) የሚባሉ የኒሻን ዓይነቶችንም መሥርቷል፡፡ እነዚህ ሁሉ ለማን እንደሚሰጡ፣ የሚያገኘው ሰው የሚኖረው ልዩ መብት፣ የሜዳሊያዎቹና የኒሻኖቹ ቅርፅ፣ መጠንና አካል ምንነት በዝርዝር ተደንግጓል፡፡ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ኮሚሽንም ተቋቁሟል፡፡ ከርዕሰ ብሔሩ ፈቃድ ሳያገኝ ኢትዮጵያዊ የውጭ አገር ሜዳይ ወይም ኒሻን መቀበል የተከለከለ መሆኑም ተደንግጓል፡፡ ይህም የአገር ሕግ ሆኖ እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ ዘለቀ፡፡ ደርግ ወደቀ፡፡ ኢሕአዴግ መጣ፡፡

በኢሕአዴግ የሥልጣን ዘመን በወታደራዊው ዘርፍ እንኳን የሜዳይ፣ የኒሻንና የሽልማት ጉዳይ የመከላከያ ሠራዊት የ1987 ዓ.ም. አዋጅ ውስጥ የተካተተው በ1990 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ በአዋጅ ቁጥር 123/1990 (የመከላከያ ሠራዊት ማሻሻያ አዋጅ) ነው፡፡ በዚህ ሕግ የዓድዋ ድል ሜዳይ የሚባል ወደር የሌለው ጀግንነት በዓውደ ውጊያ ለፈጸመ ኢትየጵያዊ ግለሰብ ወይም የሠራዊት አሃድ ወይም ቡድን የሚሰጥ የመጨረሻ ከፍተኛ የጀግና ሽልማት ሆኖ የተቋቋመውን ጨምሮ የተለያዩ የሜዳሊያዎች፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ሽልማቶች ተመሠረቱ፡፡

ፖሊስን የሚመለከት የሜዳይ፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ነገር በቀዳማዊ ሕግ ደረጃ (ፓርላማ በሚያወጣው ሕግ) የተነሳው ገና አሁን በቅርቡ በ2004 ዓ.ም. በአዋጅ ቁጥር 720 ነው፡፡ እሱም ለፖሊስ አባላት የሚሰጡ ሜዳዮች፣ ሪባኖችና የምስክር ወረቀቶች በፌዴራል ፖሊስ መተዳደሪያ ደንብ ይወሰናል ሲል ወሰነ፡፡ በዚህም መሠረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 268/2005 የጀግንነት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የላቀ ሥራ ውጤት ሜዳይ፣ የፖሊስ አገልግሎት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ) እና የፖሊስ አገልግሎት ሪባን የሚባሉ የሽልማት ዓይነቶችን አቋቋመ፡፡

አገር ባለውለታነቷን ከምታረጋግጥበት፣ ውለታዎችን ከምትስታውስበትና ለወደፊትም እንዲበረታቱ ከምታደርግበት መንገዶች አንዱ ይህ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ሥርዓት የአገሪቱን ያህል ረዥም ዘመን ያለው ቢሆንም፣ ተከታታይ መንግሥታት እየወረሱ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ባህልና የአገር ሀብት አልሆነም፡፡ ይህ ሳያንስ የተከታታይ መንግሥታት ይህንን የመንግሥት ታላቅ ሥራ የሚከናወንበትን የሕግና የተቋም ጎዶሎ፣ ቶሎና ወዲያውኑ መሙላት አለመቻላቸው፣ በተለይም በዚህ የኢሕአዴግ መንግሥት ዘመን እንደተመሰከረው አወቅነውም፣ አላወቅነውም ብሔራዊ/የአገር ማፈሪያ እየሆነ ነው፡፡ እስካሁን እንደተመለከትነው በኢሕአዴግ/በኢፌዴሪ መንግሥት የመከላከያው ጎን (የፖሊስን ጨምሮ) የሜዳይና የኒሻን ሽልማት እንኳን የተሟላው ከረዥም ጊዜ ግዴለሽነትና ቸልተኝነት በኋላ ነው፡፡ አገር ባለውለታዊነቷን የምትገልጽበትና የምታረጋገጥበት የሲቪል የመንግሥት ሽልማት ሥርዓት ግን ዛሬም ያልተሟላ ጎዶሏችን ነው፡፡

የሚሰማ ስለሌለ፣ ደንገጥ የሚልና የሚደንቀው ሰው ስለጠፋ እንጂ፣ ጉዳዩ በተለይም ጎልቶ የተነሳው የኢትዮጵያ ሚሊኒየም በተከበረበት ወቅት ‹‹ለማይመለስ ውለታህ …›› (የተሟላ ትክክለኛ መጠሪያው ምን እንደተባለ እርግጠኛ አይደለሁም) የሚል ዓይነት አስቀድሞ በሕግ ያልተቋቋመ ሜዳሊያ ስንሰጥ/ሰጠን ስንል ነው፡፡

ከዚያ በፊትና ከዚህ ወዲህም ባለሥልጣኑና ሥልጣን አለኝ የሚለው ሁሉ እየተነሳ ‹‹የከተማውን ቁልፍ››፣ ‹‹የክብር ዜግነት›› ሲሰጥ ዓይተናል፡፡ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥና አጠራርም ጭምር በጣም ግራ የተጋባና መሳቂያ ሆኖ አርፎታል፡፡ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸውን እነዚህን ቁምነገሮች የሚገዙ ሥርዓትና አሠራር መዘርጋት፣ ለመንግሥትና ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለምን የቸገረ ነገር ይሆናል፡፡

ያኔ ፕሬዚዳንት ኦባማ በአቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአስተዳደር ዘመን ኢትዮጵያን ሲጎበኙ በአጋጣሚው ‹‹ማሳሰቢያ›› ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ ኢትዮጵያ ለዜጋም ሆነ ለውጭ ሰው የምትሰጠው የሲቪል ሜዳሊያ ወይም ኒሻን ወይም ሌላ በሕግ የተቋቋመ ሽልማት የሌላት መሆኑን ነበር፡፡ ያ ከሆነ በኋላ ሚያዝያ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ለአቶ ኃይለ ማርያምና ለባለቤታቸው ‹‹ሜዳሊያ›› እና ‹‹የአገሪቱ ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጡ ዓይተናል፡፡ ከዚያም በኋላ አሁን ለዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ለተሰናባቹ የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት (ለባለቤታቸውም) ‹‹ኒሻን›› እና ‹‹ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጣቸው መስክረናል፡፡

ሽልማቱ በተሰጠበት የሥር ምክንያት ላይ ተቃውሞም ሆነ

BY አርማጌዶን


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/wedefkr/15924

View MORE
Open in Telegram


አርማጌዶን Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram Be The Next Best SPAC

I have no inside knowledge of a potential stock listing of the popular anti-Whatsapp messaging app, Telegram. But I know this much, judging by most people I talk to, especially crypto investors, if Telegram ever went public, people would gobble it up. I know I would. I’m waiting for it. So is Sergei Sergienko, who claims he owns $800,000 of Telegram’s pre-initial coin offering (ICO) tokens. “If Telegram does a SPAC IPO, there would be demand for this issue. It would probably outstrip the interest we saw during the ICO. Why? Because as of right now Telegram looks like a liberal application that can accept anyone - right after WhatsApp and others have turn on the censorship,” he says.

The Singapore stock market has alternated between positive and negative finishes through the last five trading days since the end of the two-day winning streak in which it had added more than a dozen points or 0.4 percent. The Straits Times Index now sits just above the 3,060-point plateau and it's likely to see a narrow trading range on Monday.

አርማጌዶን from us


Telegram አርማጌዶን
FROM USA