Telegram Group & Telegram Channel
የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ላይ ብቻ ያጠነጠነ ሆነና እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ በአፍሪካ ጉዳዮች ንቁ ተሳታፊ መሆን አልቻልንም፡፡ የአፍሪካን አሥር በመቶ የሕዝብ ቁጥር መያዝ ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነ አገር ለአፍሪካዊ ጉዳዮች ባዳ ሆኖ የአፍሪካ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ነፃነት ትግል ስኬት ላይ የሚፈጥረው ውስንነት በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡

አፍሪካዊ ማንነትን የተላበሰና በአፍሪካ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነቱን የሚወጣ የፖለቲካ ባህል የገነቡ አገሮች ገዥው ፓርቲም ይሁን የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ይሁን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡ ደቡብ አፍሪካን ለአብነት እናንሳና ለአፍሪካ ቀን የሚሰጡትን ትኩረት በጨረፍታ እንመልከት፡፡

የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ANC) የአፍሪካ ቀንን በተለይዩ ፕሮግራሞች ያከብራል፡፡ ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ የቀድሞ ፕሬዚዳንቶችም የፕሮግራሙ ታዳሚዎችና ንግግር አቅራቢዎች ናቸው፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲ በኩልም ለምሳሌ የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋይተርስ (EFF) የአፍሪካ ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ሁኔታ ያከብራል፡፡ በተለይ እ.ኤ.አ. በ2022 የአፍሪካ ቀን ሲከበር የፓርቲው አባላት በመሪያቸው ጁሊየስ ማሌማ መሪነት በፈረንሣይ ኤምባሲ በመገኘት፣ ፈረንሣይ በቀድሞ የቅኝ ግዛቶቿ ላይ ያላትን ተፅዕኖ እንድታቆም የሚጠይቅና ጦሯን ከእነዚሁ የአፍሪካ አገሮች እንድታወጣ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ነበር፡፡ መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማትም በኩል በተለይ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪ ፋውንዴሽን የአፍሪካ ቀን ዓመታዊ ገለጻዎች (Annual Africa Day Lecture) ላለፉት 14 ዓመታት የተካሄደ ሲሆን፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ  እ.ኤ.አ. በ2019 በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በተዘጋጀው የአፍሪካ ቀን ፕሮግራም ላይ ንግግር አቅራቢ እንደነበሩ እናስታውሳለን፡፡ የደቡብ አፍሪካን ልምድ ከአገራችን ጋር ማነፃፀሩን ብቻ ሳይሆን ምን እንማራለን የሚለው የሁላችንም ጥያቄ ይሁን፡፡

ፖለቲካችን ከኢትዮጵያ ተሻግሮ አፍሪካዊ ማንነትን ወደተላበሰ ፖለቲካ ቢሸጋገር እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ ለአፍሪካችን የምናበረክተው አበርክቶ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለአገራችን የሚኖረው በረከት ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ከሰሞኑ በሌላ ጽሑፍ እመለስበታለሁ፡፡

ወደ ነጥቤ ስመለስ የትምህርት ሚኒስቴር በተለይም የሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ቁርጠኝነትና ተባባሪነትን በመመኘት ነው፡፡ የመጀመሪያው ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ 1209/2012 መሠረት የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማ በትምህርት ቤቶች እንዲሰቀል፣ እንዲሁም መዝሙሩ እንዲዘመር የማድረግ ኃላፊነቱን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እንዲወጣ ነው፡፡ የአዋጁ መተግበር አፍሪካዊ ማንነቱን የሚያወድስ፣ በአፍሪካ ውስጥ ያሉትን ዕድሎች የሚያይና ተግዳሮቶቿን በአሸናፊነት እንድትወጣ የድርሻውን መወጣት የሚችል ዜጋ ለማፍራት ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡  

ሁለተኛው የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን አከባበር ነው፡፡ እንደሚታወቀው የአፍሪካ ኅብረት የ2024 መሪ ቃል ትምህርት ነው፡፡ ትምህርት የአኅጉራችን የትኩረት አቅጣጫ በሆነበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች ከእስከ ዛሬው የተለየ ዝግጅቶች ሊኖር እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ወትሮውንም ትምህርት ቤቶች ዋና የአፍሪካ ቀን የድምቀት ቦታዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ቤቶቻችን ከመዝናኛነት ባሻገር ምንም ዓይነት ታሪካዊም ሆነ ትምህርታዊ ፋይዳ የሌላቸው ‹‹ከለር ዴይ፣ ኦልዲስ ዴይ፣ ክሬዚ ዴይ…፣ ወዘተ›› እያከበሩ የአፍሪካ ቀን አለማክበራቸው አሳዛኝ ነው፡፡ ይህን ታሪክ ለመቀየር የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የትኩረት አቅጣጫው ትምህርት መሆኑ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች የአፍሪካ ቀንን ማክበር እንዲጀምሩ ለማስቻል፣ ከዚህ የተሻለ ወቅትና ዕድል ያለ አይመስለኝም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደር የትምህርት ቢሮዎች በኩል የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች እንዲከበር ጥሪ ቢያስተላልፍ ውጤቱ ለዘንድሮው የአፍሪካ ቀን በዓል ብቻ ሳይሆን፣ ለመጪዎቹም ዓመታት ተማሪዎቹ የአፍሪካ ቀን በየዓመቱ እንዲያከብሩና ስለአፍሪካ የተሻለ የማወቅ ዝንባሌ እንዲኖራቸው ያግዛል፡፡

አፍሪካ ዴይ ኢኒሼቲቭ የአፍሪካን ብዝኃነት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ሙዚቃና ዳንስ ከተማሪዎች ጋር ለማክበር ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚያም ባሻገር ተማሪዎቹ ስለአፍሪካ ያላቸውን ዕውቀት የሚፈትሹበትና ለወደፊቱም ስለአፍሪካ የበለጠ ለማወቅ እንዲተጉ የሚያደርጉ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ይኖራሉ፡፡ ትብብሩን ካገኘን የአፍሪካ ቀን የትውልድ ቦታውን የሚመጥን የአፍሪካ ቀን አከባበር ይኖረናል፡፡ አፍሪካዊ ማንነታችንን እያወደስን የአፍሪካ ቀንን በጋራ እናክብር!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

The post ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ



tg-me.com/wedefkr/15934
Create:
Last Update:

የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ላይ ብቻ ያጠነጠነ ሆነና እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ በአፍሪካ ጉዳዮች ንቁ ተሳታፊ መሆን አልቻልንም፡፡ የአፍሪካን አሥር በመቶ የሕዝብ ቁጥር መያዝ ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነ አገር ለአፍሪካዊ ጉዳዮች ባዳ ሆኖ የአፍሪካ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ነፃነት ትግል ስኬት ላይ የሚፈጥረው ውስንነት በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡

አፍሪካዊ ማንነትን የተላበሰና በአፍሪካ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነቱን የሚወጣ የፖለቲካ ባህል የገነቡ አገሮች ገዥው ፓርቲም ይሁን የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ይሁን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡ ደቡብ አፍሪካን ለአብነት እናንሳና ለአፍሪካ ቀን የሚሰጡትን ትኩረት በጨረፍታ እንመልከት፡፡

የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ANC) የአፍሪካ ቀንን በተለይዩ ፕሮግራሞች ያከብራል፡፡ ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ የቀድሞ ፕሬዚዳንቶችም የፕሮግራሙ ታዳሚዎችና ንግግር አቅራቢዎች ናቸው፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲ በኩልም ለምሳሌ የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋይተርስ (EFF) የአፍሪካ ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ሁኔታ ያከብራል፡፡ በተለይ እ.ኤ.አ. በ2022 የአፍሪካ ቀን ሲከበር የፓርቲው አባላት በመሪያቸው ጁሊየስ ማሌማ መሪነት በፈረንሣይ ኤምባሲ በመገኘት፣ ፈረንሣይ በቀድሞ የቅኝ ግዛቶቿ ላይ ያላትን ተፅዕኖ እንድታቆም የሚጠይቅና ጦሯን ከእነዚሁ የአፍሪካ አገሮች እንድታወጣ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ነበር፡፡ መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማትም በኩል በተለይ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪ ፋውንዴሽን የአፍሪካ ቀን ዓመታዊ ገለጻዎች (Annual Africa Day Lecture) ላለፉት 14 ዓመታት የተካሄደ ሲሆን፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ  እ.ኤ.አ. በ2019 በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በተዘጋጀው የአፍሪካ ቀን ፕሮግራም ላይ ንግግር አቅራቢ እንደነበሩ እናስታውሳለን፡፡ የደቡብ አፍሪካን ልምድ ከአገራችን ጋር ማነፃፀሩን ብቻ ሳይሆን ምን እንማራለን የሚለው የሁላችንም ጥያቄ ይሁን፡፡

ፖለቲካችን ከኢትዮጵያ ተሻግሮ አፍሪካዊ ማንነትን ወደተላበሰ ፖለቲካ ቢሸጋገር እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ ለአፍሪካችን የምናበረክተው አበርክቶ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለአገራችን የሚኖረው በረከት ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ከሰሞኑ በሌላ ጽሑፍ እመለስበታለሁ፡፡

ወደ ነጥቤ ስመለስ የትምህርት ሚኒስቴር በተለይም የሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ቁርጠኝነትና ተባባሪነትን በመመኘት ነው፡፡ የመጀመሪያው ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ 1209/2012 መሠረት የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማ በትምህርት ቤቶች እንዲሰቀል፣ እንዲሁም መዝሙሩ እንዲዘመር የማድረግ ኃላፊነቱን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እንዲወጣ ነው፡፡ የአዋጁ መተግበር አፍሪካዊ ማንነቱን የሚያወድስ፣ በአፍሪካ ውስጥ ያሉትን ዕድሎች የሚያይና ተግዳሮቶቿን በአሸናፊነት እንድትወጣ የድርሻውን መወጣት የሚችል ዜጋ ለማፍራት ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡  

ሁለተኛው የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን አከባበር ነው፡፡ እንደሚታወቀው የአፍሪካ ኅብረት የ2024 መሪ ቃል ትምህርት ነው፡፡ ትምህርት የአኅጉራችን የትኩረት አቅጣጫ በሆነበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች ከእስከ ዛሬው የተለየ ዝግጅቶች ሊኖር እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ወትሮውንም ትምህርት ቤቶች ዋና የአፍሪካ ቀን የድምቀት ቦታዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ቤቶቻችን ከመዝናኛነት ባሻገር ምንም ዓይነት ታሪካዊም ሆነ ትምህርታዊ ፋይዳ የሌላቸው ‹‹ከለር ዴይ፣ ኦልዲስ ዴይ፣ ክሬዚ ዴይ…፣ ወዘተ›› እያከበሩ የአፍሪካ ቀን አለማክበራቸው አሳዛኝ ነው፡፡ ይህን ታሪክ ለመቀየር የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የትኩረት አቅጣጫው ትምህርት መሆኑ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች የአፍሪካ ቀንን ማክበር እንዲጀምሩ ለማስቻል፣ ከዚህ የተሻለ ወቅትና ዕድል ያለ አይመስለኝም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደር የትምህርት ቢሮዎች በኩል የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች እንዲከበር ጥሪ ቢያስተላልፍ ውጤቱ ለዘንድሮው የአፍሪካ ቀን በዓል ብቻ ሳይሆን፣ ለመጪዎቹም ዓመታት ተማሪዎቹ የአፍሪካ ቀን በየዓመቱ እንዲያከብሩና ስለአፍሪካ የተሻለ የማወቅ ዝንባሌ እንዲኖራቸው ያግዛል፡፡

አፍሪካ ዴይ ኢኒሼቲቭ የአፍሪካን ብዝኃነት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ሙዚቃና ዳንስ ከተማሪዎች ጋር ለማክበር ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚያም ባሻገር ተማሪዎቹ ስለአፍሪካ ያላቸውን ዕውቀት የሚፈትሹበትና ለወደፊቱም ስለአፍሪካ የበለጠ ለማወቅ እንዲተጉ የሚያደርጉ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ይኖራሉ፡፡ ትብብሩን ካገኘን የአፍሪካ ቀን የትውልድ ቦታውን የሚመጥን የአፍሪካ ቀን አከባበር ይኖረናል፡፡ አፍሪካዊ ማንነታችንን እያወደስን የአፍሪካ ቀንን በጋራ እናክብር!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

The post ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ

BY አርማጌዶን


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/wedefkr/15934

View MORE
Open in Telegram


አርማጌዶን Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Traders also expressed uncertainty about the situation with China Evergrande, as the indebted property company has not provided clarification about a key interest payment.In economic news, the Commerce Department reported an unexpected increase in U.S. new home sales in August.Crude oil prices climbed Friday and front-month WTI oil futures contracts saw gains for a fifth straight week amid tighter supplies. West Texas Intermediate Crude oil futures for November rose $0.68 or 0.9 percent at 73.98 a barrel. WTI Crude futures gained 2.8 percent for the week.

How Does Telegram Make Money?

Telegram is a free app and runs on donations. According to a blog on the telegram: We believe in fast and secure messaging that is also 100% free. Pavel Durov, who shares our vision, supplied Telegram with a generous donation, so we have quite enough money for the time being. If Telegram runs out, we will introduce non-essential paid options to support the infrastructure and finance developer salaries. But making profits will never be an end-goal for Telegram.

አርማጌዶን from us


Telegram አርማጌዶን
FROM USA