tg-me.com/wegoch/5207
Last Update:
ምን ጊዜም ከልክ ያለፈ ጨዋነት ጀርባ የሆነች እየተካሄደች ያለች ጨዋታ አለች ብለን እንጠርጥር እንዴ !?
.
አያቴ እንዲህ ይል ነበር "ስቲንጃ ሲበዛ ትርፉ መነጀስ !" ነው።
የሆነ ግዜ እንዲህ ሆነ ባል ስራ ውሎ ወደ ቤቱ ሲመለስ ሚስቱ ስታለቅስ ያገኛታል። ይሄኔ ይደነግጥና ለምን እንደምታለቅስ ይጠይቃታል።
እሷም "እዚህ ዛፍ ላይ ያለው አሞራ ያለ ሂጃብ ሆኜ ሲያየኝ ጊዜ ወንጅል ሆኖ ታየኝ። ለዛ ነው ማለቅሰው..." ስትል ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች መለሰችለት።
ባልም በዚህ ቁጥብነቷ ተደስቶ እቅፍ አደረጋትና ግንባሯን
ሳማት። ወዲያውም መፍለጫ ይዞ ወጣ'ና አሞራው ሚያርፍበትን ዛፍ እንዳልነበረ አድርጎ ቆረጠው !
እናላችሁ ከዕለታት አንድ ቀን ባል ስራ በግዜ ጨርሶ ቤት ከች ሲል....
ያችን ቁጥቧን ሚስቱን ፣ ያችን አሞራ አየኝ ብላ ቂያማ
ምታቆመውን ሚስቱን ከውሽማዋ ጋር
ተኝታ ያገኛታል።
ምንም አላደረገም ትቶ ወጣ። ወደ ሩቅ ሀገርም ሄደ።
እና የሆነ ከተማ ሲገባ በጣም ብዙ ሰዎች ቤተ መንግስት በር ላይ ተሰብስበው ያገኛቸው'ና ለምን እንደተሰበሰቡ ይጠይቃቸዋል።
ሰዎቹም "የንጉሱ ወርቅ ማስቀመጫ ተዘርፎ ነው" ሲሉ ይመልሱለታል።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ የሆነ ሰውዬ ጤነኛ ሆኖ
በእንብርክኩ ሲንፏቀቅ ያየው'ና....
"ይህ ሰው ለምን ቆሞ አይራመድም?" ብሎ ይጠይቃቸዋል።
እነሱም "አይ ይህማ የከተማችን ትልቅ ሸይኽ ነው ! .. በእግሩ ማይራመደው ምናልባት ሳያውቅ በእግሩ ጉንዳን እንዳይገድል ሰግቶ ነው" ብለው ይመልሱልታል።
አአአዎ በቃ እዝች'ጋ ተነቃቁ.....
ሰውየውም በፍጥነት "ወላሂ ሌባውን አገኘውት...."ብሎ ጮኸ።
ንጉሱም ጋር በፍጥበት ገባ'ና "ያኛው ሸይኽ ተብዬ ነው
ንብረትህን የሰረቀህ ከፈለግክ አስፈትሸው'ና ውሸቴን ከሆነ አንገቴን ቁረጠው...." አለ።
ወታደሮችም በንጉሱ ትዕዛዝ ሸይኽ ተብዬውን ፈትሸው የተሰረቀውን የወርቅ ማስቀመጫ ተቀምጦበት አገኙት። ሁሉም ተገረሙ ፣ ደነገጡ።
ንጉሱም ለሰውዬው "እንዴት እሱ እንደሰረቀ ልታውቅ ቻልክ?" አለው ግራ በመጋባት። ሰውዬውም ሚስቱን እያስታወሰ "ቁጥብነት እና መልካምነትን እንዲህ {ድንበር
ባለፈ ሁኔታ} ስታገኘው
ከጀርባው ትልቅ ክህደት እንዳለ ያመላክታል" ብሎ መለሰለት ።
@wegoch
@wegoch
@paappii
By mustejan
BY ወግ ብቻ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/wegoch/5207