Telegram Group & Telegram Channel
"የተኛህበትን ሳታመላክተኝ
ስታዞረኝ አደርክ ስታንከራትተኝ።"
.
.
.
ሄዷል። ድንገት። ድንገቴው ለኔ ነው። የት እንደሄደ፣ ለምን እንደሄደ ምኑም አልገባኝም። ሳይገባኝ ልፈልገው ጣርኩ። እየኖረ እንዴት ይሄዳል ሰው? መኖርም መሄድም እንዴት በኩል አፍታ ይገለጣሉ? ባንድ ሰውነት ላይ እኩል? ስሄድ ጭልጥ፣ ግንጥል ብሎ መሄድን፤ ስኖር ጥግት፣ ጥብቅ ብዬ መኖርን ነው የማውቅና ግራ ገባኝ።

አስራ አምስት አመታት የጎነጎነው በሱ በኩል ለቆት ኖሮ ያለመልኩ ብትንትን፣ ጭብርር፣ ስብርብር አለ። ልብና አይምሮዬ ላይ አለ እና ሄደ ተደራረበ። እንኖራለን እያልኩ መኖርን ስሸምን መለያዬት ተከናነብኩ። ደህና መሆኔን፣ ሰላሜን፣ ቀጥና ቀና ብዬ መራመዴን የሄደ ቀን ይዞት ሄደ። ቀነጣጥሶኝ። እኔ እኔን አልሰማ አለች። አይቻት የማላውቃት ሌላ ሴትዮ ተፈለቀቀች። ያለመድኳትን ሴት ተሸከምኩ። የጎበጠች፣ አንገቷን የደፋች፣ ሰው የፈራች፣ ችላ ብትጠጋም የማትላተም። መውደድ የሚያስበረግጋት። መጠጋት እንዳያፍነከንካት በዛው አፍታ የመለየት ሃሳብ የሚያስፈራት ፈሪ ተፈጠረች።

መሄዱን ሂድ ግን እኔን መልስልኝ አልኩት የሆነ ቀን ሳወራው። ሌላ አላለም፣ ሙቭ ኦን እናድርግ ለሁለታችንም እሱ ነው የሚሻለን አለኝ። ቀድሞኝ ትቶኝ ተሻግሯል አውቃለሁ። እኔ ግን ወዴት እንደምሻገር ማወቅ ተሳነኝ። ድልድዬን ሰብረኸዋልኮ ልለው ነበር ይከፋዋል ብዬ ዝም አልኩ።

"እህህ ጠዋት ማታ እህህ ሌሊት
ይሄ ሆኗል ትርፌ ካንተ ያገኘሁት"
.
.
.
ሁሉም ይሄዳልኮ። መሄድ ሰውኛ ነው ማንም የሚሄደው። ልንሄድ ነው የመጣነው። የሚለዬው አካሄዱ ነው። የሄደው ሰው ዓይነት ነው። የቀረብን፣ ያጣነው ነገር ነው። ለዛ ነው የከበደኝ። ለዛ ነው እንዳዲስ ጉዳይ እያደር መሄዱን የማያምን ልቤ። ለዚሁ ነው እረሳሁት ባልኩ ማግስት ከሲናፍቀኝ ስሜት ጋር ግብ ግብ ገጥሜ ከራሴ የምጣላ።

ስነቃ ከሄደበት አፍታ መገረምና አለማመን ጋር እነቃለሁ። እውነት ሄዷል? በእህህታ ሳብሰለስል እውልና እንቅልፍ ዓይኔን ከመክደኑ ፊት በህቅታ እንዲወጣልኝ ከእንባዬ ጋር እንዳንገዋለልኩት ሽፋሽፍቴ እንደራሰ እንቅልፍ ይጥለኛል። ስነቃም ሃሳቤ ውስጥ ይኖራል። እንዲያ ሆነ የኑሮዬ ድግግሞሹ። በሆነ ባልሆነው ተነጫነጭኩ። ራሴ ላይ፣ ሃሳቤ ላይ፣ እቅዴ ላይ፣ ህልሜ ላይ፣ ቁጭቴ ላይ፣ ትላንቴ ላይ፣ ዛሬዬ ላይ፣ ነገዬ ላይ፣ ህይወት ላይ፣ እግዜሩ ላይ።

ለምን እንደሄደ፣ ለምን እንደበቃሁት፣ ባይለውም ለምን እንደጠላኝ እንዲገባኝ ስዳክር ስድስት አመታት ተሻገርኩ ከህመሜ ጋር። እሱ እንዳለውም ተሻግሯል። አስራአምስት አመት የቆዬ አብሮነታችንን እንደዋዛ ጥሎ፣ ከራሱ ጋር ከነፍሱ ጋር ይደልቃል፣ በዝምታ።

በነዚህ ሁሉ ጊዜያት ለምን ግን እለዋለሁ እግዜሩን። በአካል የተገለጠ ሰው ሲያምረኝ። የሚያወራኝ፣ ምኑንም ምኑንም የሚቀባጥርልኝ። ያለመስመር፣ ያለመጠንቀቅ ሁሉን። ሳቅ የሚወልድልኝ። ወሬ አልቆብንም ዝም ብለን የምንቆይ። ዝምታችንም የሚያወራ። እንደገና የምንቀጥል። እሱን የሚያስረሳኝ። ሰው በሰው ነው የሚረሳው ይሉ የለ? የምረሳበትንም ባይሆን የሚተካልኝን ሰው አምጣው እንጂ እያልኩ ንጭንጭ እግዜሩ ላይ። ከትላንቴ ተጣብቄ አረጀሁኮ፣ አዲስ ዛሬ ስጠኝ እንጂ ንትርክ። ለምን እኔ ማንም የሌለኝ? ለምን እኔ ፍቅሬን የተነጠኩ? ለምን እኔን ከሰው አጥንት አልፈለቀከኝም? ከሰው ግራ ጎን አልሸለቀከኝም? ናፍቀሽኛል መባል አያምረኝም? አውሪኝ ትንሽ አትሂጂ መባል አይጎበኘኝም? ለምን እኔ? መች ነው የኔ ወረፋ? መች ነው ልቤ የሚሞላ ዳግም?

"ስሄድ ስሄድ ውዬ ስሄድ ስሄድ ነጋ
ጅብ አይበላም ብዬ የናፋቂን ስጋ"
.
.
.
ዛሬ ሌሊት በጣም ናፈቅኸኝ። ሁሌም ነው የምትናፍቀኝ፣ ሄዷል በቃ ብዬ አልተውኩህም። ትቶኛል በቃ ብዬ አልተቀየምኩህም። ትናፍቀኛለህ። እያለህ እንደምናደርገው በእኩለ ሌሊት ንፋስ ስልክ ጎዳና ላይ እንራመድ ብዬ ወጣሁ። አብረኸኝ ነበርክ። እያወራኸኝ፣ እያሳቅኸኝ፣ ያቺን ምላስህን አውጥተህ ትልልቅ ዓይንህን ለማጥበብ የምትታገልባትን ፊትህን እያሳየኸኝ። እየተራመድን ትተኸኝ ሮጥክ ልይዝህ ተከተልኩህ። አጥሩ የፈረሰው ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ ተከትዬ ዘልዬ ገባሁ።

" እስኪ እናንተ ተኙ እኔ ስራ አለብኝ
ግንብ እገነባለሁ ፍቅር ተንዶብኝ"
.
.
.
አቅፌህ ካሸለብኩበት የጎረነነ ድምጽ ቀሰቀሰኝ። 'የኔ እህት እባክሽ ትለከፊያለሽ በዚህ ሌሊት አትምጪ፣ ብርዱም አይቻልም' መቃብር የሚቆፍር ጎልማሳ ቁልቁል እየተመለከተኝ። አያውቅም ቤቴ አንተ እንደሆንክ። አያውቅም የተናደ ፍቅሬን እዚህ እየመጣሁ ልገነባ እንደምጥር። አያውቅም ማንም እንደሌለኝ። አያውቅም ልክፍቴ ወዳንተ መምጣት እንደሆነ። አያውቅም የሚሞቀኝ እዚህ እንደሆነ። አያውቅም ምንም። ናፍቀኸኛል......

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Martha Haileyesus



tg-me.com/wegoch/5214
Create:
Last Update:

"የተኛህበትን ሳታመላክተኝ
ስታዞረኝ አደርክ ስታንከራትተኝ።"
.
.
.
ሄዷል። ድንገት። ድንገቴው ለኔ ነው። የት እንደሄደ፣ ለምን እንደሄደ ምኑም አልገባኝም። ሳይገባኝ ልፈልገው ጣርኩ። እየኖረ እንዴት ይሄዳል ሰው? መኖርም መሄድም እንዴት በኩል አፍታ ይገለጣሉ? ባንድ ሰውነት ላይ እኩል? ስሄድ ጭልጥ፣ ግንጥል ብሎ መሄድን፤ ስኖር ጥግት፣ ጥብቅ ብዬ መኖርን ነው የማውቅና ግራ ገባኝ።

አስራ አምስት አመታት የጎነጎነው በሱ በኩል ለቆት ኖሮ ያለመልኩ ብትንትን፣ ጭብርር፣ ስብርብር አለ። ልብና አይምሮዬ ላይ አለ እና ሄደ ተደራረበ። እንኖራለን እያልኩ መኖርን ስሸምን መለያዬት ተከናነብኩ። ደህና መሆኔን፣ ሰላሜን፣ ቀጥና ቀና ብዬ መራመዴን የሄደ ቀን ይዞት ሄደ። ቀነጣጥሶኝ። እኔ እኔን አልሰማ አለች። አይቻት የማላውቃት ሌላ ሴትዮ ተፈለቀቀች። ያለመድኳትን ሴት ተሸከምኩ። የጎበጠች፣ አንገቷን የደፋች፣ ሰው የፈራች፣ ችላ ብትጠጋም የማትላተም። መውደድ የሚያስበረግጋት። መጠጋት እንዳያፍነከንካት በዛው አፍታ የመለየት ሃሳብ የሚያስፈራት ፈሪ ተፈጠረች።

መሄዱን ሂድ ግን እኔን መልስልኝ አልኩት የሆነ ቀን ሳወራው። ሌላ አላለም፣ ሙቭ ኦን እናድርግ ለሁለታችንም እሱ ነው የሚሻለን አለኝ። ቀድሞኝ ትቶኝ ተሻግሯል አውቃለሁ። እኔ ግን ወዴት እንደምሻገር ማወቅ ተሳነኝ። ድልድዬን ሰብረኸዋልኮ ልለው ነበር ይከፋዋል ብዬ ዝም አልኩ።

"እህህ ጠዋት ማታ እህህ ሌሊት
ይሄ ሆኗል ትርፌ ካንተ ያገኘሁት"
.
.
.
ሁሉም ይሄዳልኮ። መሄድ ሰውኛ ነው ማንም የሚሄደው። ልንሄድ ነው የመጣነው። የሚለዬው አካሄዱ ነው። የሄደው ሰው ዓይነት ነው። የቀረብን፣ ያጣነው ነገር ነው። ለዛ ነው የከበደኝ። ለዛ ነው እንዳዲስ ጉዳይ እያደር መሄዱን የማያምን ልቤ። ለዚሁ ነው እረሳሁት ባልኩ ማግስት ከሲናፍቀኝ ስሜት ጋር ግብ ግብ ገጥሜ ከራሴ የምጣላ።

ስነቃ ከሄደበት አፍታ መገረምና አለማመን ጋር እነቃለሁ። እውነት ሄዷል? በእህህታ ሳብሰለስል እውልና እንቅልፍ ዓይኔን ከመክደኑ ፊት በህቅታ እንዲወጣልኝ ከእንባዬ ጋር እንዳንገዋለልኩት ሽፋሽፍቴ እንደራሰ እንቅልፍ ይጥለኛል። ስነቃም ሃሳቤ ውስጥ ይኖራል። እንዲያ ሆነ የኑሮዬ ድግግሞሹ። በሆነ ባልሆነው ተነጫነጭኩ። ራሴ ላይ፣ ሃሳቤ ላይ፣ እቅዴ ላይ፣ ህልሜ ላይ፣ ቁጭቴ ላይ፣ ትላንቴ ላይ፣ ዛሬዬ ላይ፣ ነገዬ ላይ፣ ህይወት ላይ፣ እግዜሩ ላይ።

ለምን እንደሄደ፣ ለምን እንደበቃሁት፣ ባይለውም ለምን እንደጠላኝ እንዲገባኝ ስዳክር ስድስት አመታት ተሻገርኩ ከህመሜ ጋር። እሱ እንዳለውም ተሻግሯል። አስራአምስት አመት የቆዬ አብሮነታችንን እንደዋዛ ጥሎ፣ ከራሱ ጋር ከነፍሱ ጋር ይደልቃል፣ በዝምታ።

በነዚህ ሁሉ ጊዜያት ለምን ግን እለዋለሁ እግዜሩን። በአካል የተገለጠ ሰው ሲያምረኝ። የሚያወራኝ፣ ምኑንም ምኑንም የሚቀባጥርልኝ። ያለመስመር፣ ያለመጠንቀቅ ሁሉን። ሳቅ የሚወልድልኝ። ወሬ አልቆብንም ዝም ብለን የምንቆይ። ዝምታችንም የሚያወራ። እንደገና የምንቀጥል። እሱን የሚያስረሳኝ። ሰው በሰው ነው የሚረሳው ይሉ የለ? የምረሳበትንም ባይሆን የሚተካልኝን ሰው አምጣው እንጂ እያልኩ ንጭንጭ እግዜሩ ላይ። ከትላንቴ ተጣብቄ አረጀሁኮ፣ አዲስ ዛሬ ስጠኝ እንጂ ንትርክ። ለምን እኔ ማንም የሌለኝ? ለምን እኔ ፍቅሬን የተነጠኩ? ለምን እኔን ከሰው አጥንት አልፈለቀከኝም? ከሰው ግራ ጎን አልሸለቀከኝም? ናፍቀሽኛል መባል አያምረኝም? አውሪኝ ትንሽ አትሂጂ መባል አይጎበኘኝም? ለምን እኔ? መች ነው የኔ ወረፋ? መች ነው ልቤ የሚሞላ ዳግም?

"ስሄድ ስሄድ ውዬ ስሄድ ስሄድ ነጋ
ጅብ አይበላም ብዬ የናፋቂን ስጋ"
.
.
.
ዛሬ ሌሊት በጣም ናፈቅኸኝ። ሁሌም ነው የምትናፍቀኝ፣ ሄዷል በቃ ብዬ አልተውኩህም። ትቶኛል በቃ ብዬ አልተቀየምኩህም። ትናፍቀኛለህ። እያለህ እንደምናደርገው በእኩለ ሌሊት ንፋስ ስልክ ጎዳና ላይ እንራመድ ብዬ ወጣሁ። አብረኸኝ ነበርክ። እያወራኸኝ፣ እያሳቅኸኝ፣ ያቺን ምላስህን አውጥተህ ትልልቅ ዓይንህን ለማጥበብ የምትታገልባትን ፊትህን እያሳየኸኝ። እየተራመድን ትተኸኝ ሮጥክ ልይዝህ ተከተልኩህ። አጥሩ የፈረሰው ዮሴፍ ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ ተከትዬ ዘልዬ ገባሁ።

" እስኪ እናንተ ተኙ እኔ ስራ አለብኝ
ግንብ እገነባለሁ ፍቅር ተንዶብኝ"
.
.
.
አቅፌህ ካሸለብኩበት የጎረነነ ድምጽ ቀሰቀሰኝ። 'የኔ እህት እባክሽ ትለከፊያለሽ በዚህ ሌሊት አትምጪ፣ ብርዱም አይቻልም' መቃብር የሚቆፍር ጎልማሳ ቁልቁል እየተመለከተኝ። አያውቅም ቤቴ አንተ እንደሆንክ። አያውቅም የተናደ ፍቅሬን እዚህ እየመጣሁ ልገነባ እንደምጥር። አያውቅም ማንም እንደሌለኝ። አያውቅም ልክፍቴ ወዳንተ መምጣት እንደሆነ። አያውቅም የሚሞቀኝ እዚህ እንደሆነ። አያውቅም ምንም። ናፍቀኸኛል......

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Martha Haileyesus

BY ወግ ብቻ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/wegoch/5214

View MORE
Open in Telegram


ወግ ብቻ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Launched in 2013, Telegram allows users to broadcast messages to a following via “channels”, or create public and private groups that are simple for others to access. Users can also send and receive large data files, including text and zip files, directly via the app.The platform said it has more than 500m active users, and topped 1bn downloads in August, according to data from SensorTower.

What is Telegram?

Telegram is a cloud-based instant messaging service that has been making rounds as a popular option for those who wish to keep their messages secure. Telegram boasts a collection of different features, but it’s best known for its ability to secure messages and media by encrypting them during transit; this prevents third-parties from snooping on messages easily. Let’s take a look at what Telegram can do and why you might want to use it.

ወግ ብቻ from us


Telegram ወግ ብቻ
FROM USA