tg-me.com/yenetube/54860
Last Update:
የኤርትራ መንግስት በሀገሪቱ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን እንዲያጣራ የተቋቋመው ቡድን የስራ ግዜ እንዲያበቃ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተገለጸ!
- አምነስቲ እና ሂዩማን ራይትወች የኤርትራ መንግስትን ኮንነዋል፣ የቡድኑ የስራ ግዜ እንዲራዘም ጠይቀዋል
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኤርትራ የተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን እንዲያጣራ የተቋቋመው የባለሙያዎች ቡድን የስራ ግዜ እንዲያበቃ ለማድረግ የኤርትራ መንግስት ጥረት አያደረገ እንደሚገኝ ተገለጸ።
በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም መጀመሪያ ቀናት በሲዊዘርላንድ ጀኔቫ በተካሄደው የመሪዎች ጉባኤ ላይ የኤርትራ የተባበሩት መንግሥታት ልዩ የሰብዓዊ መብት ተከታታይ ራፖርተር ሞሐመድ አብደልሰላም በኤርትራ የሚካሄዱት የሰብአዊ መብተት "ጥሰቶች ስልታዊ ናቸው፤ የተጠያቂነት አስፈላጊነት እጅግ በጣም አጣዳፊ ነው" ሲሉ መግለጻቸው ይታወሳል።
የኤርትራ መንግስት ለመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ያስገባውን ዶክመንት መመልከቱን ጠቅሶ ሮይተርስ የዜና ወኪል ባሰራጨው ዘገባው ኤርትራ የባለሞያዎቹ ቡድን የስራ ግዜ እንዳይራዘም በመጠየቅ ላይ ትገኛለች።
“የአጣሪ ቡድኑ በኤርትራ ያለው ስራ ገና አልተጠናቀቀም፣ ብዙ ይቀረዋል፤ የምክር ቤቱ አባል ሀገራት የቡድኑን የስራ ግዜ እንዲራዘም ድምጻቸውን ሊሰጡት ይገባል፤ በኤርትራ በመካሄድ ላይ ላሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፤ ከዚህ በፊት ለተፈጸሙ እና አሁንም በመፈጸም ላይ ላሉ ጥሰቶች ተጠያቂ እንዲሆን ማድረግ ይገባዋል” ሲሉ የአምነስቲ የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ዋና ዳየሬክተር ቲገረ ቻጉታህ ገልጸዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
BY YeneTube

Share with your friend now:
tg-me.com/yenetube/54860