Telegram Group & Telegram Channel
የአራቱ ወንጌላት መልእክትና ይዘት፦

አራቱ ወንጌላት በየክፍላቸው መዝግበው የያዙት ስለአምላካችን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታሪክና ሥራ ነው። ሁሉም ይህንኑ ታሪክና ሥራ ቢናገሩም እያንዳንዳቸው ከሌሎቹ የሚለዩበት የአመዘጋገብና ያገላለጽ ሁኔታ አለ። ለምሳሌው ያህል ለመጥቀስ በአንዱ የወንጌል ክፍል ተመዝግበው በሦስቱ ወንጌላት ላይ ያልተመዘገቡና የማይገኙ፣ በሁለቱ ወንጌላት ተመዝግበው በተቀሩት በሁለቱ ላይ የማይገኙ፣ እንዲሁም በሦስቱ ወንጌላት ተመዝግበው በቀሪው አንድ ላይ ያልተመዘገቡና የማይገኙ አንዳንድ የጌታ ታሪኮችና ሥራዎች ስለሚገኙ ነው። ይህንን ጠንቅቆ ለመረዳት በእያንዳንዱ መጽሐፍት ግርጌ ባለው የኅዳግ ማመሳከሪያ በመጠቀም ፬ቱንም ወንጌላት ማነጻጸር ይቻላል።
የማቴዎስ፣ የማርቆስና የሉቃስ ወንጌላት <ሲኖፕቲክ> ተብለው ይጠራሉ።

<ሲኖፕቲክ> ማለት ተመሳሳይ ማለት ሲሆን ቃሉ የግሪክ ቃል ነው። ሦስቱ ወንጌላት በይዞታቸው በብዙ ክፍል ስለሚመሳሰሉ ይህንን መመሳሰላቸውን ለማስረዳት የተሰጣቸው ስያሜ ነው። ምክንያቱም ሦስቱም ወንጌላት አንድ ዓይነት መልእክታትን ጽፈው ይገኛሉና። ምንም እንኳን የጌታ ተመሳሳይ ታሪክና ሥራ በ፫ቱ ወንጌላት ጠቀስም የአንዱ ወንጌላዊ አገላለጽ ከሌሎቹ የተለየ ስለሚሆን ሁሉንም የወንጌል ክፍል ማንበቡ አስፈላጊ ነው።

የዮሐንስ ወንጌል ነው። ይህም ወንጌል የመዘገበው እንደ ሦስቱ ወንጌላት ስለጌታ ታሪክና ሥራ ቢሆንም በብዛት እነርሱ ያልመዘገቡትን አንዳንድ ታሪክና ሥራዎች መዝግቦ ይገኛል። ስለዚህ በይዞታው ከሦስቱ ወንጌላት ይለያል። ሦስቱ ወንጌላትና አራተኛው ወንጌል በሚከተሉት ሦስት ነገሮች ይለያያሉ።

እነርሱም፦
ሦስቱ ወንጌላት የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን ምድራዊውን ታሪክ (የትስብእቱን ማለት የሰውነቱን ነገር) አጉልተው ይጽፋሉ።

📗 ወንጌላዊው ማቴዎስ፦

አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፡ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፡…ማታንም ያዕቆብን ወለደ፡ ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ። ማቴ. ፩ ፡፩-፲፯ በማለት የጌታን የትውልድ ዝርዝር ጽፏል።

📒 ወንጌላዊው ማርቆስ፦

ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱም በፊልጶስ ቂሣርያ ወዳሉ መንደሮች ወጡ በመንገድም። ሰዎች እኔ ማን እንደ ሆንሁ ይላሉ? ብሎ ደቀ መዛሙርቱን ጠየቃቸው። እነርሱም። መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ከነቢያት አንዱ ብለው ነገሩት። እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። ጴጥሮስም አንተ ክርስቶስ ነህ ብሎ መለሰለት። ማር.፰፡፳፯-፳፱ በማለት የጌታን የሰውነቱን ነገር ጽፏል።

📕 ወንጌላዊው ሉቃስ፦

ኢየሱስም ሊያስተምር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ሆኖት ነበር፤ እንደመሰላቸው የዮሴፍ ልጅ ሆኖ የኤሊ ልጅ፡ የማቲ ልጅ፡…የሄኖስ ልጅ፡ የሴት ልጅ፡የአዳም ልጅ፡ የእግዚአብሔር ልጅ። ሉቃ.፫፡፳፫-፴፰። በማለት የጌታን የትውልድ ዝርዝር ጽፏል።

􀀩 አራተኛው ወንጌል ግን ጌታ ከሰማይ መውረዱንና የመለኮቱን ነገር አጉልቶ ይጽፋል።

ይኸውም፦ በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። ዮሐ. ፩፡፩-፫ ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።

ዮሐ. ፫ ፡፲፫፤ እንግዲህ አይሁድ ከሰማይ የወረደ እንጀራ እኔ ነኝ ስላለ ስለ እርሱ አንጐራጐሩና አባቱንና እናቱን የምናውቃቸው ይህ የዮሴፍ ልጅ ኢየሱስ አይደለምን? እንግዲህ። ከሰማይ ወርጃለሁ እንዴት ይላል? አሉ። ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እርስ በርሳችሁ አታንጐራጕሩ። የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል።
አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል። እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።

የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ። አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤ ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው። ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው። ዮሐ. ፮፡፵፩-፶፩፤
እናንተ ከታች ናችሁ፥ እኔ ከላይ ነኝ፤ እናንተ ከዚህ ዓለም ናችሁ፥ እኔ ከዚህ ዓለም አይደለሁም። ዮሐ.፰፡፳፫ እንግዲህ ከላይ በተገለጹት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ምክንያት ሦስቱ ወንጌላት ምድራውያን ወንጌላት ሲባሉ አራተኛው ወንጌል ደግሞ ሰማያዊ ወንጌል ይባላል።
.
.
.
#ይቀጥላል

@yetenantun_lenege



tg-me.com/yetenantun_lenege/345
Create:
Last Update:

የአራቱ ወንጌላት መልእክትና ይዘት፦

አራቱ ወንጌላት በየክፍላቸው መዝግበው የያዙት ስለአምላካችን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታሪክና ሥራ ነው። ሁሉም ይህንኑ ታሪክና ሥራ ቢናገሩም እያንዳንዳቸው ከሌሎቹ የሚለዩበት የአመዘጋገብና ያገላለጽ ሁኔታ አለ። ለምሳሌው ያህል ለመጥቀስ በአንዱ የወንጌል ክፍል ተመዝግበው በሦስቱ ወንጌላት ላይ ያልተመዘገቡና የማይገኙ፣ በሁለቱ ወንጌላት ተመዝግበው በተቀሩት በሁለቱ ላይ የማይገኙ፣ እንዲሁም በሦስቱ ወንጌላት ተመዝግበው በቀሪው አንድ ላይ ያልተመዘገቡና የማይገኙ አንዳንድ የጌታ ታሪኮችና ሥራዎች ስለሚገኙ ነው። ይህንን ጠንቅቆ ለመረዳት በእያንዳንዱ መጽሐፍት ግርጌ ባለው የኅዳግ ማመሳከሪያ በመጠቀም ፬ቱንም ወንጌላት ማነጻጸር ይቻላል።
የማቴዎስ፣ የማርቆስና የሉቃስ ወንጌላት <ሲኖፕቲክ> ተብለው ይጠራሉ።

<ሲኖፕቲክ> ማለት ተመሳሳይ ማለት ሲሆን ቃሉ የግሪክ ቃል ነው። ሦስቱ ወንጌላት በይዞታቸው በብዙ ክፍል ስለሚመሳሰሉ ይህንን መመሳሰላቸውን ለማስረዳት የተሰጣቸው ስያሜ ነው። ምክንያቱም ሦስቱም ወንጌላት አንድ ዓይነት መልእክታትን ጽፈው ይገኛሉና። ምንም እንኳን የጌታ ተመሳሳይ ታሪክና ሥራ በ፫ቱ ወንጌላት ጠቀስም የአንዱ ወንጌላዊ አገላለጽ ከሌሎቹ የተለየ ስለሚሆን ሁሉንም የወንጌል ክፍል ማንበቡ አስፈላጊ ነው።

የዮሐንስ ወንጌል ነው። ይህም ወንጌል የመዘገበው እንደ ሦስቱ ወንጌላት ስለጌታ ታሪክና ሥራ ቢሆንም በብዛት እነርሱ ያልመዘገቡትን አንዳንድ ታሪክና ሥራዎች መዝግቦ ይገኛል። ስለዚህ በይዞታው ከሦስቱ ወንጌላት ይለያል። ሦስቱ ወንጌላትና አራተኛው ወንጌል በሚከተሉት ሦስት ነገሮች ይለያያሉ።

እነርሱም፦
ሦስቱ ወንጌላት የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን ምድራዊውን ታሪክ (የትስብእቱን ማለት የሰውነቱን ነገር) አጉልተው ይጽፋሉ።

📗 ወንጌላዊው ማቴዎስ፦

አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፡ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፡…ማታንም ያዕቆብን ወለደ፡ ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ። ማቴ. ፩ ፡፩-፲፯ በማለት የጌታን የትውልድ ዝርዝር ጽፏል።

📒 ወንጌላዊው ማርቆስ፦

ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱም በፊልጶስ ቂሣርያ ወዳሉ መንደሮች ወጡ በመንገድም። ሰዎች እኔ ማን እንደ ሆንሁ ይላሉ? ብሎ ደቀ መዛሙርቱን ጠየቃቸው። እነርሱም። መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ከነቢያት አንዱ ብለው ነገሩት። እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። ጴጥሮስም አንተ ክርስቶስ ነህ ብሎ መለሰለት። ማር.፰፡፳፯-፳፱ በማለት የጌታን የሰውነቱን ነገር ጽፏል።

📕 ወንጌላዊው ሉቃስ፦

ኢየሱስም ሊያስተምር ሲጀምር ዕድሜው ሠላሳ ዓመት ሆኖት ነበር፤ እንደመሰላቸው የዮሴፍ ልጅ ሆኖ የኤሊ ልጅ፡ የማቲ ልጅ፡…የሄኖስ ልጅ፡ የሴት ልጅ፡የአዳም ልጅ፡ የእግዚአብሔር ልጅ። ሉቃ.፫፡፳፫-፴፰። በማለት የጌታን የትውልድ ዝርዝር ጽፏል።

􀀩 አራተኛው ወንጌል ግን ጌታ ከሰማይ መውረዱንና የመለኮቱን ነገር አጉልቶ ይጽፋል።

ይኸውም፦ በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ። ይህ በመጀመሪያው በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ። ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም። ዮሐ. ፩፡፩-፫ ከሰማይም ከወረደ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው።

ዮሐ. ፫ ፡፲፫፤ እንግዲህ አይሁድ ከሰማይ የወረደ እንጀራ እኔ ነኝ ስላለ ስለ እርሱ አንጐራጐሩና አባቱንና እናቱን የምናውቃቸው ይህ የዮሴፍ ልጅ ኢየሱስ አይደለምን? እንግዲህ። ከሰማይ ወርጃለሁ እንዴት ይላል? አሉ። ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። እርስ በርሳችሁ አታንጐራጕሩ። የላከኝ አብ ከሳበው በቀር ወደ እኔ ሊመጣ የሚችል የለም፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሁሉም ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ ተብሎ በነቢያት ተጽፎአል፤ እንግዲህ ከአብ የሰማ የተማረም ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል።
አብን ያየ ማንም የለም፤ ከእግዚአብሔር ከሆነ በቀር፥ እርሱ አብን አይቶአል። እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው።

የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ። አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤ ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው። ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው። ዮሐ. ፮፡፵፩-፶፩፤
እናንተ ከታች ናችሁ፥ እኔ ከላይ ነኝ፤ እናንተ ከዚህ ዓለም ናችሁ፥ እኔ ከዚህ ዓለም አይደለሁም። ዮሐ.፰፡፳፫ እንግዲህ ከላይ በተገለጹት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ምክንያት ሦስቱ ወንጌላት ምድራውያን ወንጌላት ሲባሉ አራተኛው ወንጌል ደግሞ ሰማያዊ ወንጌል ይባላል።
.
.
.
#ይቀጥላል

@yetenantun_lenege

BY ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/yetenantun_lenege/345

View MORE
Open in Telegram


ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram hopes to raise $1bn with a convertible bond private placement

The super secure UAE-based Telegram messenger service, developed by Russian-born software icon Pavel Durov, is looking to raise $1bn through a bond placement to a limited number of investors from Russia, Europe, Asia and the Middle East, the Kommersant daily reported citing unnamed sources on February 18, 2021.The issue reportedly comprises exchange bonds that could be converted into equity in the messaging service that is currently 100% owned by Durov and his brother Nikolai.Kommersant reports that the price of the conversion would be at a 10% discount to a potential IPO should it happen within five years.The minimum bond placement is said to be set at $50mn, but could be lowered to $10mn. Five-year bonds could carry an annual coupon of 7-8%.

Pinterest (PINS) Stock Sinks As Market Gains

Pinterest (PINS) closed at $71.75 in the latest trading session, marking a -0.18% move from the prior day. This change lagged the S&P 500's daily gain of 0.1%. Meanwhile, the Dow gained 0.9%, and the Nasdaq, a tech-heavy index, lost 0.59%. Heading into today, shares of the digital pinboard and shopping tool company had lost 17.41% over the past month, lagging the Computer and Technology sector's loss of 5.38% and the S&P 500's gain of 0.71% in that time. Investors will be hoping for strength from PINS as it approaches its next earnings release. The company is expected to report EPS of $0.07, up 170% from the prior-year quarter. Our most recent consensus estimate is calling for quarterly revenue of $467.87 million, up 72.05% from the year-ago period.

ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ from us


Telegram ማዕዶት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
FROM USA