tg-me.com/zena24now/33485
Last Update:
በኢትዮጵያ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች ለአይነስውነት ተጋላጭ መሆናቸው ተገለፀ
በኢትዮጵያ አይነ ስውርነት ወይንም የእይታ ችግር መጠነ ሰፊ የሆነ ቀዉስ እያስከተለ እንደሚገኝ የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታውቋል ።በሆስፒታሉ የአይን ህክምና ክፍል ሀላፊ ዶክተር ሰለሞን ቡሳ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩትአስራ አምስት አመት በፊት በተደረገ ሀገር አቀፍ ጥናት መሰረት 1 ነጥብ 6 በመቶው የኢትዮጵያ ህዝብ ለአይነ ስውርነት ተጋልጧል።
50 በመቶ የሚሆነው አይነስውርነት መነሻው የሞራ ግርዶሽ ነው ያሉት ዶክተር ሰለሞን እንደ ትራኮማ ያሉ ሌሎች የጤና እክሎች አሉታዊ ተጽእኖ እንዳላቸው ገልፀዋል።በአሁኑ ሰአት 2 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ለአይነ ስውርነት ተጋላጭ እንደሆኑ ገልፀው ከእነዚህ ውስጥ 7 ነጥብ 8 የሚሆኑት አነጣጥረው የማየት ችግር አለባቸው ብለዋል።
እንዲህ ባለው የእይታ ችግር የተጠቁ ሰዎች የእይታቸውን መጠን ተመርምረው ማወቅና መነፅርን በመጠቀም ማስተካከል የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር አንደሚችልም ተናግረዋል።በእይታ ችግር የሚሰቃዮ ዜጎችን ችግር ለመፍታት የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ያስገነባው የመነፅር ማምረቻና መሸጫ ክፍል ስራ መጀመሩን ዶክተር ሰለሞን ገልፀዋል።
ሆስፒታሉ CBM ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባውን የመነፅር ማምረቻና መሸጫ ክፍል ርክክብ አድርጎ መነፅሩን ለማምረት የሚያስፈልጉ የተለያዩ ግብዓቶችን ሲያሟላ መቆየቱ ተገልጿል። ከዚህ ቀደም የሆስፒታሉ ተገልጋይ ማህበረሰቦች አስፈላጊውን የአይን ህክምና ምርመራ ካደረጉ በሗላ መነፅርን ከግቢ ውጭ የሚገዙ በመሆናቸው ለአላስፈላጊ ወጪ ሲዳረጉ ቆይተዋል በማለት የህክምና ባለሙያው አስረድተዋል።
በቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል
BY ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/zena24now/33485