Telegram Group Search
የ2016 ዓ.ም ሞዴል ፈተና በመሰጠት ላይ መሆኑ ተገለጸ።


ፈተናው ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት በሁሉም የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች በአማርኛ እና አፋን ኦሮሞ ስርአተ ትምህርት ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ለሚገኙ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች እየተሰጠ እንደሚገኝ ከቢሮው የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።


ሞዴል ፈተናው ተማሪዎቹ ለመደበኛው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል መልቀቂያ ክልላዊ ፈተና በአግባቡ መዘጋጀት እንዲችሉ ቢሮው ከክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤቶች ጋር በጋራ በመሆን ስታንዳርዱን የጠበቀ ፈተና ማዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ ገልጸው ሞዴል ፈተናው በአግባቡ እንዲሰጥ በየተቋማቱ ድጋፍና ክትትል የሚያደርጉ ባለሙያዎች መመደባቸውን አስታውቀዋል።


❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በመጪው ሰኔ ወር የሚሰጠው የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ን በድጋሜ ለሚወስዱ ተፈታኞች መልዕክት አስተላልፏል።

1ኛ. በሰኔ 2015 ዓ / ም እና በየካቲት 2016 ዓ / ም ተፈትነው የነበረና አሁን በድጋሜ ለመፈተን ማመልከት ለሚፈልጉ፤

2ኛ. ከሰኔ 2015 ዓ.ም በፊት #የሕግ_መውጫ_ፈተና ወስደው የማለፍያ ነጥብ ያለገኙ አሁን በድጋሚ ለመውሰድ ለሚፈልጉ ስም ዝርዝራቸው ከቀድሞ ዩኒቨርስቲያቸው ለትምህርት ሚኒስቴር የተላከላቸው አመልካቾች፤

ምዝገባው እስከ ግንቦት 25/ 2016 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ገልጿል።

ተፈታኞች በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ብቻ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቁ ተብሏል።

ሚኒስቴሩ ፦

➡️ ከላይ ከተገለጸው ጊዜ ውጭ የሚቀርቡ የምዝገባ ጥያቄዎች ተቀባይነት እንደማይኖራቸው አሳስቧል።

➡️ በሰኔ 2015 ዓ / ም እና በየካቲት 2016 ዓ / ም ተፈትነው የማለፊያ ውጤት ያልመጡ አሁን በድጋሜ መፈተን የሚፈልጉ አመልካቾች የሚጠበቅባቸውን የአገልግሎት ክፍያ በቴሌ ብር ብቻ መፈጸም አለባቸው ተብሏል።

➡️ ከሰኔ 2015 ዓ/ም በፊት ለሕግ መውጫ ፈተና ተቀምጠው በድጋሜ ለመፈተን የሚፈልጉ አመልካቾች ስም ዝርዝራቸው ከቀድሞ ዩኒቨርሲቲያቸው መላኩን በማረጋጥ የሚጠበቅባቸውን #የአገልግሎት_ክፍያ ለዚሁ ጉዳይ ብቻ በተከፈተው የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር ➡️1000553176097 ገቢ በማድረግ ደረሰኙን በግልፅ በሚታይ #ስካን_ኮፒ በማድረግ በ [email protected] ኢሜል አድራሻ እንዲልኩ ጥሪ ቀርቧል።

❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የመንግስትም ሆነ የግል ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ተፈታኝ ተማሪዎቹን በት/ቤታቸው ለማስፈተን ምን ማሟላት አለባቸው?

ግንቦት 24/2016 ዓ.ም ( የትምህርት ሚኒስቴር) በዚህ አመት በኦንላይን የተዘጋጅውን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ አገር አቀፍ ፈተናን ተማሪዎች በተማሩበት ትምህርት ቤት ለማስፈተን ፍላጎት ያለው ማንኛዉም የመንግስትም ሆነ የግል ትምህርት ቤት የተደራጀ የኮምፒዉተር ላብራቶሪ ሊኖረው ግድ ይለዋል። ይሄውም
1. ዴስክቶፕ ወይም ላፕቶፕ ኮምፒዉተሮች
2. የዉስጥ ኔትዎርክ ያለዉ (የገመድ) ኔትዎርክ/Local Area Network /
3. የኢንተርኔት መስመር ከበቂ ባንድዊድዝ ጋር እንደ የመፈተኛ ኮምፒዉተር ብዛት
4. የባክ አፕ ፓዎር (ጄኔሬተር)
ጋር አሟልተው መገኘትና ለትምህርት ቢሮዎች በማሳወቅ በቢሮዎች በኩል መሟላቱ ሲረጋግጥ የፈተና ማእከል በመሆን ተማሪዎቹን ማስፈተን እንደሚችሉ እያሳውቅን ለፈተና የሚዘጋጁት ዴስክቶፕ እና ላፕቶፕ ኮምፒዉተሮች ማሟላት ያለበቸዉ ትንሹ ስፔስፊኬሽን እንደሚከተለው ቀርቧል።
1. RAM --------------- 4GB or higher
2. Storage --------------250GB or higher
3. Processor Speed -------- 2.5GHZ or higher
4. Processors ---------- Intel Core i3 or higher
5. OS --------------- Windows 10
6. Browsers ---------------Safe Exam Browser and other
7. Accessories ---------- Keyboards and Mouse for desktop computers.

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🪙 Notcoin 🪙 እና USDT
የምትሸጡ ካለችሁ እገዛለሁ  (
@Creatoryona ) inbox
በተጨማሪ በአካል ለመገበያየት ከፈለጋችሁ
      📍አ.አ  📍ሐዋሳ
📍አማራ ክልል (ደሴ,ኮቻ)
📍ትግራይ (ዋና ዋና ከተሞች)


@creatoryona @creatoryona
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MoE

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተናን በኦንላይን የሚወስዱ ተፈታኞች በክላስተር የተዘጋጀ ማስፈንጠሪያ (URL) ላይ በመግባት እንዲለማመዱ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።

ከስር የተቀመጡት ማስፈንጠሪያዎች ተፈታኝ ተማሪዎች የሚለማመዱበት ሲሆን የፈተናው ዕለት ደግሞ መፈተኛ ይሆናሉ።

Note:

እስካሁን Username እና Password ያለገኛችሁ ተፈታኞች፤ ከትምህርት ቤት አስተባባሪዎች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ክላስተር አንድ

አዲስ አበባ፦ https://c2.exam.et
ሲዳማ ክልል፦ https://c2.exam.et
ትግራይ ክልል፦ https://c2.exam.et

ክላስተር ሁለት

ደቡብ ም/ኢ/ክልል፦ https://c3.exam.et
ጋምቤላ ክልል፦ https://c3.exam.et
አማራ ክልል፦ https://c3.exam.et

ክላስተር ሦስት

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፦ https://c4.exam.et
ሀረሪ ክልል፦ https://c4.exam.et
አፋር ክልል፦ https://c4.exam.et
ኦሮሚያ ክልል - 1
• አዳማ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• አጋሮ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• አምቦ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ አርሲ፦ https://c4.exam.et
• ምዕራብ አርሲ፦ https://c4.exam.et
• አሰላ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ባሌ፦ https://c4.exam.et
• ባቱ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቤሾፍቱ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቦረና፦ https://c4.exam.et
• ቡሌ ሆራ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ቡኖ በደሌ፦ https://c4.exam.et
• ዶዶላ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ባሌ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ቦረና፦ https://c4.exam.et
• ጉጂ፦ https://c4.exam.et
• ምሥራቅ ሐረርጌ፦ https://c4.exam.et
• ምዕራብ ሐረርጌ፦ https://c4.exam.et
• ሆለታ ከተማ፦ https://c4.exam.et
• ሆሮ ጉዱሩ፦ https://c4.exam.et
• ኢሉባቦር፦ https://c4.exam.et

ክላስተር አራት

ድሬዳዋ ከተማ፦ https://c5.exam.et
ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል - 2
• ጅማ፦ https://c5.exam.et
• ጅማ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ቄለም ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• ማያ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• መቱ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሞጆ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሞያሌ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ነጆ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ነቀምት ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሮቤ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሰንዳፋ በኬ፦ https://c5.exam.et
• ሻኪሶ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሻሸመኔ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሸገር ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ሸኖ ከተማ፦ https://c5.exam.et
• ምስራቅ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• ሰሜን ሸዋ (ኦሮሚያ)፦ https://c5.exam.et
• ደቡብ ምዕራብ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ሸዋ፦ https://c5.exam.et
• ምስራቅ ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ወለጋ፦ https://c5.exam.et
• መዕራብ ጉጂ፦ https://c5.exam.et
• ወሊሶ ከተማ፦ https://c5.exam.et

SHARE 👇👇👇
❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ተማሪዎች በበይነ መረብ መፈተናቸው ስህተትን መቀነስን ጨምሮ በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።

የበይነ መረብ ፈተና ለስህተት በር አይከፍትም

የበይነ መረብ ፈተና አንድ ጥያቄ ሳይመልሱ ወደ ፈለጉት ጥያቄ በአንድ Click የመሔድ እንዲሁም ተመልሰው መስራት የሚፈልጉትን ጥያቄ Flag በማድረግ ተመልሶ የመስራት ዕድልን ይሰጣል።

ጊዜ ቆጣቢ ነው

በአንድ Click የፈተና ጥያቄን መልስ ለመስጠት ያስችላል። እንዲሁም ምን ያህል ደቂቃ እንደተጠቀሙ ከመፈተኛ ስክሪን ላይ ማየት ስለሚቻል ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ያስችላል።

የተሻሻለ የመረጃ ቋት አለው

የበይነ መረብ ፈተናዎች በቂ የፈተና መረጃዎችን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በማከማቸት ለተፈታኞች አመጣጥኖ ያቀርባል፡፡

የተሰሩ ጥያቄዎችን መልስ በፍጥነት በራሱ ይልካል

በፈተና ወቅት ጥያቄዎቹን ሰርተው ሳያጠናቀቁ የተሰጠው ደቂቃ ካለቀ የሰሩትን በጠቅላላ በራሱ በፍጥነት ይልካል።

ፈጣን ግብረ መልስ ይሰጣል

በበይነ መረብ ፈተናዎች ሲሰጡ ውጤታቸው ከሌላው ጊዜ በተለየ ፈጥኖ የመታወቅ ዕድል ይሰጣል።

ተማሪዎች በቤታቸው እያደሩ እንዲፈተኑ ዕድል ይሰጣል

ትምህርት ቤቶች የተደራጀ የኮምፒውተር ቤተሙከራ ካላቸውና የመፈተኛ ክላስተር ለመሆን አስፈላጊውን መስፈርቶች ማሟላታቸው ከተረጋገጠ ተማሪዎች በተማሩበት ትምህርት ቤት ሆነው እንዲፈተኑ ዕድል ይፈጥራል። #MoE

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ይለማመዱ!

የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የኦንላይን የመፈተኛ ፕላትፎርም አጠቃቀምን ይለማመዱ!

ፕላትፎርሙን እንዴት መጠቀምና እንዴት ፈተናውን መውሰድ እንደሚቻል ለማሳየት በትምህርት ሚኒስቴር እና በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የተዘጋጀን የአራት ደቂቃ ገላጭ ቪዲዮ በተከታዩ ሊንክ በመግባት ይመልከቱ፡፡ ራስዎን ለፈተናው ያዘጋጁ!

ቪዲዮውን ይመልከቱ 👇
https://www.youtube.com/watch?v=PdAu-FI-Q5M

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

የሪሚዲያል ተማሪዎች የፈተና ጊዜን የተመለከቱ በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ደርሰዋል፡፡

ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የተመለከተው ጊዚያዊ የሪሚዲያል ተማሪዎች የፈተና መርግብር፤ ፈተናው ከሰኔ 3-10/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ያሳያል።

በዚህም የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከሰኔ 3 እስከ 6/2016 ዓ.ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሰኔ 6-10/2016 ዓ.ም ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ይጠበቃል። የፕሮግራም ለውጥ የሚኖር ከሆነ የምናሳውቃችሁ ይሆናል።

ፈተናው በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ብቻ የሚሰጥ ሲሆን፤ ተቋማቱ ስለፈተናው ገለፃ ለተፈታኞች መስጠት መጀመራቸውን ተመልክተናል።

ዘንድሮ 78 ሺህ የሪሚዲያል ተማሪዎች #ከባህርዳር_ዩኒቨርሲቲ ውጪ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ከታህሳስ ወር ጀምሮ ሲከታተሉ ቆይተዋል፡፡

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በበዓል ቀናት ሆነ ማግስት የሚወጡ የፈተና ሰሌዳ አግባብነት የሌለው ነው!»

የፌዴራል መጅሊስ ዋና ስራ አስኪያጅ


የ2016 E.C. የሪሚዲያል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመፈተኛ የጊዜ ሰሌዳ ከዒድ አል-አዽሓህ ዐረፋ በዓል ቀን ጋር በሚጋጭ መልኩ ከሰኔ 6 እስከ 10 ይሰጣል።


የተማሪዎች የመፈተኛ የጊዜ ሰሌዳ የሙስሊሙን በዓላት ታሳቢ አድርገው መውጣት አለባቸው ያሉት የፌዴራል መጅሊሱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ከማል ሃሩን የበዓል ቀናትን ታሳቢ ያላደረገ የፈተና የጊዜ ሰሌዳ አወጣጥ አግባብነት የሌለውና በተማሪዎች የስነልቦና አልፎም የፈተና ውጤታቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ብለዋል።


መጅሊሱ ባሳለፍነው አመት ጀምሮ በዚህ ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስትር ጋር መነጋገሩ የተገለፀ ሲሆን ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም ይሰራል ተብሏል። ሀሩን ሚዲያ በጉዳዩ ዙሪያ ከትምህርት ሚኒስቴር መረጃዎችን ለመጠየቅ ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካለት ዘግቧል።

©ሀሩን ሚዲያ

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ዛሬ ያበቃል!

በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) የተዘጋጀ "ብሔራዊ የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ" ፕሮግራም (National Cyber Talent Challenge Program) የምዝገባ ጊዜ ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡

በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ልዩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላችሁ ኢትዮጵያውያን በቻሌንጁ ላይ መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን፤ Cyber Security, Cyber Development, Embedded Systems, and Aerospace የታለንት መስኮች ናቸው፡፡

ምዝገባው ዛሬ ግንቦት 30/2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡

ለመመዝገብ፦ https://talent.insa.gov.et

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ዕለት ይሰጣል ተብሎ የነበረው የሬሚዲያል (የማካካሻ) ትምህርት የማጠቃለያ ፈተና ቀን ተለወጠ፡፡

የሬሚዲያል (የማካካሻ) ትምህርት የማጠቃለያ ፈተናን ከሰኔ 3-10/ 2016 ዓ.ም ድረስ ለመስጠት መዘጋጀቱን፤ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቆ እንደነበረ አይዘነጋም፡፡

ሆኖም ሰኔ 9/ 2016 ዓ.ም የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ስለሆነ በዕለቱ ይሰጣል ተብሎ የነበረውን ፈተና ሰኔ 11/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በአማራ ክልል የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 4/2016 ዓ.ም ጀምሮ ይሰጣል።

ፈተናዎቹን ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

ፈተናዎቹ ታትመው፣ ወደሚሰጥባቸው ትምህርት ቤቶች የማጓጓዝ ሥራ መጠናቀቁን የቢሮው ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

184,393 የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ 170,470 የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 13 እና 14/2016 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ።

ተማሪዎቹን ለፈተና ለማብቃት የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጥ መቆየቱን አስረድተዋል።

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች

➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡

❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡

➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡

❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡

❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡

❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡

❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡

❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።

❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡

➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
11. በእስኪብርቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ

12. ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ ነገር ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም

13. በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ነገ ሰኔ 3/2016 ዓ.ም መሰጠት ይጀምራል።

ፈተናው በተመረጡ የፈተና ማዕከላት በኦንላይን ይሰጣል።

የማጠቃለያ ፈተናው የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በሚፈተኑት የሒሳብ ትምህርት ይጀመራል።

ተፈታኞች ፈተናው መሰጠት ከሚጀምርበት ሰዓት 30 ደቂቃ ቀድመው መገኘት የሚጠበቅባቸው ሲሆን፣ የተከለከሉ ቁሳቁሶችን ወደ ፈተና ማዕከላት ይዘው መምጣት የለባቸውም ተብሏል።

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 701 ሺሕ 489 ተማሪዎች ይወስዳሉ - የትምህርት ሚኒስቴር

ሰኔ 4/2016 (አዲስ ዋልታ) የዘንድሮ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 701 ሺሕ 489 ተማሪዎች እንደሚወስዱ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ ዘንድሮ በሚሰጠው ድብልቅ የ12ኛ ክፍል መልቂያያ ፈተና ላይ መግለጫ ሰጥቷል።

ፈተናው በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ የተገለጸ ሲሆን እንደሀገር የአቅም ችግር በመኖሩ ምክንያት ፈተናውን ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት አለመቻሉን ተገልጿል።

በመሆኑም የዘንድሮ የፈተና አሰጣጥ በትምህርት ቤቶች አቅም የሚወሰን ይሆናል ነው የተባለው።

የኦንላይን ፈተና ውጤትን በቶሎ በማሳወቅ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ ፈተናን ለመስጠት፣ ስህተትን በመቀነስ እና በሌሎችም ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ላይ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተመላክቷል።

ከኢንተርኔት እና የመብራት መቆራረጥ ጋር ተያይዞ ያሉ ስጋቶችን ለመቀነስ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በትብብር በመስራትና የመብራት መቆራረጥ እንዳይኖር ጀነሬተሮችን በፈተና መስጫ ተቋማት ማሟላት መቻሉ ተገልጿል።

ተማሪዎች ለኦንላይን ፈተና የመፈተኛ ኮምፒውተር እንዲያመጡ ተገደዋል የሚባለው ወሬ እውነትነት የሌለውና ከትምህርት ሚኒስቴር እውቅና ውጪ እንደሆነም በመግለጫው ተነስቷል።

❤️ @temhert_bebete
❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በአማራ ክልል በቀጠለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከ180 ሺህ በላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና አለመቀመጣቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገለፀ፡፡

ዛሬ የሚጠናቀቀውን የ8ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና ክልል አቀፍ ፈተና በክልሉ ፈተናውን መውሰድ ከነበረባቸው 369,827 ግማሽ ያህሉ ወይም ከከ180 ሺህ በላይ የሚሆኑት ፈተናውን እንዳልወሰዱ የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ 99 ሺህ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና እንደማይቀመጡ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

ግጭቱ ባለባቸው የምዕራብ፣ ምስራቅ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች ያሉ ተማሪዎች ዓመቱን በሙሉ ያልተማሩና ጀምረው ያቋረጡ በመሆናቸው ለፈተናው መቀመጥ እንዳልቻሉ ነው ኃላፊው የገለፁት፡፡

ነሐሴ መጨረሻ ወይም በቀጣዩ ዓመት መስከረም ወር ላይ የይዘት ክለሳ ተደርጎና የማካካሻ ትምህርት ተሰጥቷቸው ተማሪዎቹ ለፈተና ሊቀመጡ እንደሚችሉ ገልፀዋል፡፡

❤️ @temhert_bebete
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2024/06/14 06:17:58
Back to Top
HTML Embed Code: