Telegram Group Search
“ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም "

እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን አደሰችሁ ።

ጽሩይ እምወርቅ ወእምብሩር ንጡፍ ወኅሩይ እምአእላፍ ሀብተ ማርያም መልአክ ዘውገ ኪሩብ ቀሊለ ክንፍ አማን ስሙዐ ዜና እስከ አጽናፍ ፡፡

ሰላም ለፅንሰትከ እማህፀነ ቅድስት ዮስቴና በብሥራተ ጻድቅ ባሕታዊ ሠናየ ዜና ሐብተ ማርያም ጴጥሮስ ሐዋርያ ወልደ ዮና መሐረኒ ምግባረ ጽድቅ ወጸግወኒ ልቦና አፍቅሮ ቢጽ እኃሥሥ ዘምስለ ፍጽምት ትሕትና::

(መልክአ አቡነ ሀብተ ማርያም)

" እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና ::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና ::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ :: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል ::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል ::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው :: በእርምጃውም አይሰናከልም:: "
(መዝ 36፥28-31 )

ቅዱስ አባታችን ፅንሰታቸው ነሐሴ 26
ልደታቸው ግንቦት 26
ዕረፍታቸው ኅዳር 26 ነው ፡፡

ኦ አምላከ አቡነ ሀብተ ማርያም ዕቀቦ ወአድኅኖ ወባልሆ እመከራ ሥጋ ወነፍስ ወእምኩሉ ተቃራኒ ወእምኩልነ ክቡር ሀብተ ማርያም ለዓለም ዓለም አሜን ለይኩን ለይኩን ::

ወስብሐት ለእግዚአብሔር !

@ortodoxtewahedo
#ነሀሴ 26 በዓለ ፅንሰቱ ለወላዴ አእላፍ አቡነ ኢየሱስ ሞአ ዘ ሃይቅ እስጢፋኖስ ወ አቡነ ሀብተ ማርያም ጻድቅ

"+ እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና:: ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: +"+

(መዝ. 36:28-31)

"+ ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማሕበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ:: የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ:: እንዲሁም ጐበዞች ሆይ! ለሽማግሌዎች ተገዙ:: ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ:: እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና:: ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል::

+ (1ዼጥ. 5:3)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

@ortodoxtewahedo
መረጃ የአቡነ ጴጥሮስ ጉዳይ

(ግንቦት 26/ 2016 ዓ.ም ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ)

የአቡነ ጴጥሮስን ጉዳይ በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶሱ ዛሬ ዉዉይት ያደረገ ሲሆን በዚህ መሠረት ፦ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣
አቡነ አብርሃም ፣ አቡነ ኤርምያስ ፣ አቡነ ጎርጎርዮስ
፣ አቡነ ሳዊሮስ ፣ አቡነ ሄኖክ ፣ አቡነ ናትናኤል ዘሚኔንሶታ በመሆን መንግስትን እንዲያናግሩ፣ችግሩ እንዲፈታና ወደ አገራቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ ዛሬ ወስኗል ፣ ይሳካ ይሆን እሱን የምናየው ነው ዝርዝር መረጃውን በመደበኛ ፕሮግራማችን ይጠብቁን ::

@ortodoxtewahedo
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ምስለ ኖኅ
ኪዳነ ዘአቀምከ፤ ለደቂቀ እስራኤል መና ዘአውረድከ፤
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወሥነ
ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወከመ
ወሬዛ ኃየል መላትሒሁ ጉርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ
ዘወይጠል፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ሰማየ ወምድረ ዘአንተ
ፈጠርከ፤ ፀሐየ ወወርኀ ዘአስተዋደድከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ በከዋክብት ሰማየ ዘከለልከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ቀደሳ ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት፤ ወአልዓላ
እምኵሉ ዕለት፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወኵሉ ይሴፎ ኪያከ፤
#ትርጉም
ከኖኅ ጋር ቃል ኪዳን የገባህ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው
ለእስራኤል ልጆች መናን ያወረድክ፤ ምድርን በአበቦች
ያስጌጥክ፤ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው ? የምድረ በዳውን
አራዊት ከወዳጆችህ ጋር ያስማማህ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ
ማነው፤ ጉንጮቹ እንደ ዋልያ እንቦሳ ፈጣኖች ናቸው፤
አንደበቱ ጣፋጭ ነው፤ ተወዳጅነቱ እንደ ፌቆ ግልገል ነው፤
ሰማይና ምድርን የፈጠርክ፤ ፀሐይና ጨረቃን ያስማማህ፤
ሰማይን በከዋክብት የሸፈንክ፤ ምድርን በአበቦች ያሸበረቅህ፤
ሰንበትን ያከበርካት ከዕለታትም ለይተህ ከፍከፍያደረግኻት፤
አቤት!! እንዳንተ ይቅር ባይ ማንም የለምና ኹሉም አንተን
ተስፋ ያደርጋሉ።
#እንኳን_ለዓለም_ጌታ_ለፍጥረታት_አምላክ_ለነገስታት_ንጉስ_ልዑለ_ባህሪ_ለሆነው_ለአምላካችን_ለመድሐኒታችን_መድኃኒዓለም_ወርሀዊ_በዓል_አደረሰን !

@ortodoxtewahedo
🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔

ኦ አባይ  ሀገር በሀኪ ኢትዮጵያ 
ሀገረ  ነጎድጓድ ሀገረ እግዚአብሔር

ተንስኢ ወልበሲ ሀይለ እግዚአብሔር  እስመ ተንስኡ ፀላእትኪ ወአብቀዋ ኦሙ ላይለ ህዝብኪ

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

#መልካም እለተ ይሁንልን

ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ

ከ40 በላይ አብያተ ክርስቲያናትን አሰርተው ሀገረ ስብከታቸው በዘንድሮ ቀይረዋል በረከትዎ ትድረሰን ተጉህ እረኛ ብፁዕ አባታችን።

@ortodoxtewahedo
† ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል †

የደብረ ገሊላ አማኑኤል ካቴድራል የተተከለው በ1905 ዓ.ም በልጅ ኢያሱ ዘመነ መንግሥት ነው። የመጀመሪያውን መቃኞ ያሰሩት ፊት አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሲሆኑ ጽላቱም በጎንደር ክፍለ ሀገር የነበረና ከዚያ መጥቶም በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የተቀመጠ ነበር።

ታድያ ፊት አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ያሰሩት የመጀመርያው መቃኞ ለአገልግሎት ምቹ ስላልነበር ሁለተኛ መቃኞ ድጋሚ ተሰርቶ ታቦቱ እንዲገባ ተደርጓል።

ንግሥት ዘውዲቱ በግንቦት 28 በ 1914 ዓ.ም የአማኑኤል በዓል ተገኝተው ሲያስቀድሱ ምርጊቱ ተደርምሶ ሲወድቅ በማየታቸው ሦስተኛ መቃኞ እንዲሰራ አዘዙ። የደብሩ አስተዳዳሪ በጊዜው የተክለ ሃይማኖትን ቤተ ክርስትያንም አንድ ላይ ያስተዳድሩ የነበረ በመሆኑ ንግሥቲቷ የቤተ መንግስታቸውን አጣኝ የመጀመርያው አስተዳዳሪ ሆነው ደብሩን እንዲጠብቁ አደረጉ። አለቃው ሦስተኛውን መቃኞ አሰርተው ታቦቱ ወደ ተዘጋጀለት መቃኞ ገባ።

በ1920 ህዝቡ እየበዛ በመምጣቱ አገልግሎቱ እንዲሰፋ ስላስፈለገ በንግሥት ዘውዲቱ አማካኝነት አዲስ ሕንጻ ቤተ መቅደስ ግንባታ ተጀመረ። በ1931 ታህሳስ 28 ቀን ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ታቦቱ ወደ መንበሩ ገብቷል። ንግሥት ዘውዲቱ ፍጻሜውን ሳያዩ ያረፉ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ደግሞ ክብ ቅርጽ ነበረው።

አሁን ያለው ቤተ ክርስቲያን በጥር 28 ቀን 1969 ዓ.ም በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው የተጀመረ ሲሆን የወቅቱ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ በነበሩት በሊቀ ሊቃውንት ንቡረ ዕድ አባ ተፈራ መልሴ አስተባባሪነት በምእመናን ርብርብና በቅዱስ አማኑኤል አከናዋኝነት ግንቦት 28 ቀን 1978 ዓ.ም ተጠናቆ ታቦተ ህጉ ወደ ህንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብቷል።

@ortodoxtewahedo
2024/06/06 06:22:18
Back to Top
HTML Embed Code: