Telegram Group Search
"ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ" የተሰኘው ዐውደ ርእይ በቅዱስ ፓትርያርኩ ጉብኝትና ቡራኬ ተጠናቀቀ !

በሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት አዘጋጅነት የተሰናደው "ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ" የተሰኘው ልዩ ታሪካዊ ዐውደ ርእይ ከሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 9 ቀናት ለዕይታ ቀርቦ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ ጉብኝትና ቡራኬ በትናንትናው ዕለት ሚያዝያ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተጠናቋል።

ዐውደ ርእዩ የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊና ትውልዳዊ ሀብቶችን በትንናትናዊ ውበታቸው በአሁናዊ ቅኝት የቀረበበት ፣ ትውልዱን የሚመጥን ሥራዎች የታዩበት ነው ተብሏል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ከቅዱስነታቸው ጋር ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አባቶች ፣ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ኦርቶዶክሳውያን ተገኝተዋል።

@መረጃው የተዋሕዶ ሚዲያ ነው

@ortodoxtewahedo
#እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ

#እንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት ገዳም

በአዲስ አበባ ከተማ በስተሰሜን ምሥራቅ በጉለሌ ክፍለ ከተማ የምትገኝ ስመጥርና ታሪካዊ ገዳም ስትሆን በተራራ፣በሸለቆና በወንዞች የተከበበች በመሆኑዋ በተፈጥሮ አቀማመጧ አረንጓዴ የተላበሰች ናት፡፡ ይህም ለቤተክርስቲያኗ ውበትና ግርማ ሞገስ ከመስጠት አልፎ በሚያስደስት ፀጥታ የአዕዋፍ ዝማሬ ተሞልታ ጸጋን እንድትላበስ አድርጓታል፡፡
ይህች ቦታ የተቆረቆረችው በ484 ዓ/ም ሲሆን በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተቋቋመች፡፡ አባ ሊባኖስ ወደ ሌላ መንፈሳዊ ተልእኮ ለመሄድ መነኮሳቱን ሲሰናበቱ እንዲህ የሚል ትንቢት ተናግረው ነበር ‹‹ልጆቼ ሆይ በሉ ይህችን ቅድስት ቦታ አደራ ሰጥቻችኋለሁ በኋላ ዘመን ታላቅ ቦታ ትሆናለች' አጋንንት ይወገዱባታል' የብዙ ቅዱሳን አፅም ያርፍባታል' ነገስታት ጳጳሳት ይሰግዱባታል' ብዙ መናንያን መጠጊያ ያደርጋታል ቤተ መቅደሷም በወርቅ በብር ተጊጣ ትታነጻለች የአንድነቱም ገዳም ተሻሽሎ ይቋቋምባታል››፡፡ በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡
በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ለመነኮሳቱ እንዲህ ብለው ነበር ‹‹ይህች ገዳም ታላቅ ስመጥር ገዳም ትሆናለች ከእርሷ በታች የሚታየው ጫካና ዱር መናገሻ ከተማ ይሆናል፡፡››
አፄ ዘርዓ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ በንግስት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡
ይህች ቦታ እንደተነገረላት ትንቢት ብዙ ቅዱሳንና ነገሥታት መጥተው የሰገዱባት የባረኳት' ጸበሏ የአጋንንት ድል መንሻ' የብዙ መነኮሳት መጠጊያ 'የህሙማን መፈወሻ' የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎች አንዷ ናት፡፡ ይህች ደብር በ1957 ዓ/ም የተመሠረተ ሰንበት ት/ቤት ሲኖራት በ1984 ዓ/ም በብፁዓን ጳጳሳት ‹‹መርሶ ሕይወት›› /የሕይወት ወደብ/ የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡ የገዳሟ ስያሜ ሐመረ ኖኅ ( የኖኅ መርከብ ) እንደሆነ ሁሉ መርሶ ሕይወት ( የሕይወት ወደብ ) በመባሉ ሁለቱ ተዛማችነት አላቸው ፡፡ ይህ ሰንበት ት/ቤት ለየት የሚያደርገው በግል መኖሪያ ቤት በጋሞኛ ቋንቋ ይሰጥ የነበረውን ትምህርት ከ1986 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ ስር በማቀፍ የወንጌል ትምህርቱን ከመማር ባሻገር ለጋሞ ሕዝብ መንፈሳዊ እንቅስቃሴን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
አዘጋጅ፡- እህተ ማርያም (በሰ/ት/ቤታችን ሰሌዳ መጽሔት ቀርቦ የነበረ)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘለአለም ትኑር!!!

ሰው ሁሉ ለመናገር የዘገየ ለመስማት የፈጠነ ይሁን !
(ያዕቆብ 1፥19)

< ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@ortodoxtewahedo
​​👼 ቅዳሴ ማለት ምንም ማለት ነው?
🤔 በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ ምሥዋዕቶች ምን ምን ናቸው?
🥰 14ቱ ፍሬ ቅዳሴያት እነማን ይሆኑ?

😇 ካህናት በቅዳሴ ወቅት 2: 3: 4: 5: 7: 12: ወይም 24: ሆነው ከቀደሱ ምሳሌነቱ ምን ምን ይሆን?
🧎‍♂ እኛ ክርስቲያኖች ቅዳሴን ባስቀደስን ቁጥር 4 ነገሮች እናገኛለን ምን ይሆኑ?
👼 አምስቱ የስሜት ሕዋሳት በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ያስቀድሳሉ እንዴት?


            ይ🀄️🀄️ሉ ይማሩ
                  👇🏾👇🏾👇🏾

https://www.tg-me.com/addlist/AQPOMxHXz_42NDE0
"ሁላችንም የእግዚአብሔርን ድምፅ ሰምተን ባለመመለሳችን እስካሁን ድረስ መከራችን እንደቀጠለ ነው።" ብፁዕ አቡነ ዲሜጥሮስ

ብፁዕ አቡነ ዲሜጥሮስ የሊባኖስ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምህላ፣ የዕርቅ እና የጸሎት አዋጅ አውጀዋል።

ብፁዕነታቸው ያስተላለፉት ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ይቀርባል ።

በመላው ዓለም ለምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ

"ቅረቡ ኀቤሁ ወያበርኅ ለክሙ" ወደ እግዚአብሔር ቅረቡ ያበራላችሁማል:: መዝ 33፥5

የምሕላ፣ የዕርቅ እና የጸሎት አዋጅ።

በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም በየጊዜው ረኀብ፣ መከራ፣ የሰው ልጅ ዕልቂት ማስተናገድ የተለመደ እየሆነ መጥቷል። በሀገርም ሆነ በመላው ዓለም የሚደርሰው መከራ በሰው አለመታዘዝ ምክንያት ከእግዚአብሔር የተላከ የመቅሠፍት በትር መሆኑን አስተዋይ አእምሮ ያለው ሁሉ የሚገነዘበው ሀቅ ነው።

በመሆኑም እግዚአብሔር በምሕረቱ እንዲጎበኘን በቸርነቱ ይቅር እንዲለን ሁላችንም ወደ እግዚአብሔር በምህላ፣በዕርቅ፣ በጾም እና በጸሎት መቅረብ ይገባናል።

"ወደ እኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር" ዘካ 1፥3 "ኅሡ ሰላማ ለሀገር ወጸልዩ በእንቲአሃ ኀበ እግዚአብሔር እስመ በሰላመ ዚአሃ ይከውን ሰላምክሙ" ኤር 29፥7 ስለ ሀገር ሰላም ወደ እግዚአብሔር ጸልዩ በእርሷ ሰላም ሰላማችሁ ይሆናልና በማለት የሀገር ሰላም የሰው ሁሉ ሀሳብ መሆን እንዳለበትና ሁሉም ስለ ሰላም ወደ ፈጣሪው መቅረብ እንዲገባው ቅዱስ መጽሐፍ ያስረዳል።

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በወንጌል "በስሜ ብትሰባሰቡ በመካከላችሁ እሆናለሁ" ማቴ 18፥20 በሚለው አምላካዊ ቃል መሠረት በፍቅር ልንሰባሰብ ያስፈልጋል። ሰላም በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት እና በዕርቅ እንጂ በጦርነትና በእንቢተኝነት አይመጣምና ፍጹም ሰላም ለዓለም እንዲሆን በመላው ዓለም ያላችሁ ሰላምን የምትሹ ሁሉ ስለሀገር፣ ሰለዓለም መጸለይ ይገባናል።

ስለሆነም በመላው ዓለም እና በኢትዮጵያ በየጊዜው በሚከሰተው ረኀብ፣ ጦርነት፣ የሰው ልጅ ዕልቂት ምክንያት ሀገረ ስብከታችን በተደጋጋሚ የምህላ፣ የዕርቅ አዋጅ ሲያወጣ የቆየ ቢሆንም ነገርግን ሁላችንም የእግዚአብሔርን ድምፅ ሰምተን ባለመመለሳችን እስካሁን ድረስ መከራችን እንደቀጠለ ነው።

በሀገረ ስብከታችን እና በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ከእግዚአብሔር ቁጣ ለማምለጥ ከመከራውም ለመዳን ዛሬን እንጂ ነገን በሕይወት ለመኖራችን እርግጠኛ ባልሆንበት የሕይወት ዘመናችን ልዩነትን ትተን አንድነትን፣ ኃጢአትን ትተን ጽድቅን፣ ጦርነትን ትተን ሰላምን በመከተል አምላካችን እንዲታረቀን በቤተክርስቲያን ስም እናሳስባለን።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።

@ortodoxtewahedo
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#አምላካችን ሆይ
እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደበደላችን አይሁን::

@ortodoxtewahedo
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#አምላካችን ሆይ
እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደበደላችን አይሁን::

ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇
@ortodoxtewahedo
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#አምላካችን ሆይ
እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደበደላችን አይሁን::

ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇
@ortodoxtewahedo
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
#አምላካችን ሆይ
እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደበደላችን አይሁን::

ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇
@ortodoxtewahedo
#በውስጥ መስመር ለተጠየቀ ጥያቄ መልስ።

#እግዚኦ_መሐረነ_ክርስቶስ_ለምን _እንላለን ?.......

—————“ #ሚስጢሩ ”—————

በቤተክርስቲያናችን ስርዓት ሁል ጊዜ ካህኑ እግዚአብሔር ከታሰራችሁበት ኃጥያት ማሰሪያይፍታቹ ሲሉ

❖ 12 ጊዜ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስና
❖ 12 ጊዜ ደግሞ በእንተ እግዝትነ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ያስብላሉ ።

ካህናትና ምእመናን በጣቶቻችን እየቆጠርን ይህኑን 12 ጊዜ እንላለን ።
             ============
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ ማለት አቤቱ ክርስቶስ ማረን ሲሆን በእንተ እግዝእትነ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ ደግሞ ስለ እመቤታችን ማርያም ብለህ ክርስቶስ ሆይ ማረን ማለት ነው ።
        =============
አስራ ሁሉት ጊዜ መሐረነ መባሉ ለቀኑ 12 ሰዓት በእንተ እግዝእትነ ማርያም ደግሞ ለሊቱን
12 ሰዓት ሲሆን በአጠቃላይ በየሰዓቱ ለሰራነው ኃጥያት በሃያ አራቱ 24ቱ ሰዓት ምሕረት እናገኝ ዘንድ ነው።

🌼ሌላው አስራ ሁለት ጊዜ የሆነበት ምክንያት፦

☞ 1ኛ በስመ ሥላሴ ነው በእያንዳንዱ ፊደል•••

• አ ብ ወ ል ድ መ ን ፈ ስ ቅ ዱ ስ
፩ ፪ ፫ ፬ ፭ ፮ ፯ ፰ ፱ ፲ ፲፩ ፲፪

☞2ኛ የድህነታችን ምክንያት በሆነች በእመቤታችን ስም ፊደል ነው ።

• ቅ ድ ስ ት ድ ን ግ ል ማ ር ያ ም
፩ ፪ ፫ ፬ ፭ ፮ ፯ ፰ ፱ ፲ ፲፩ ፲፪

—————“እግዚኦ”————-

አቆጣጠረም እግዚኦ መሐረነ ሲባል በአውራ ጣት እየቆጠሩ ከጠቋሚ ጣት ወደ ታች ፣ቀጥሎ በመሐል ጣት ወደ ላይ ከዚያም በቀለበት ጣት ወደ ታች ተደርጎ በማርያም ጣት / በትንሿ/ ጣት ወደ ላይ ነው ።

ከጠቋሚ ጣት ወደ ታች ~ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማየ ሰማያት መውረዱን በዚህ ምድር መመላለሱን ሕማሙንና ሞቱን እናስባለን ።

=====================
መሐል ጣት ወደ ላይ ~ማረጉን ወደ ሰማይ መውጣቱን በቀለበት ጣት ወደ ታች ስንቆጥር ወደዚች አለም ለፍርድ መምጣቱን፤

• በትንሿ/ ጣት ወደ ላይ ስንወጣ ደግሞ በትንሳኤ ዘጉባኤ ይዞን ወደ ሰማይ እንደሚያወጣን እያሰብን ነው።

—————“ብእንተ”————-

በእንተ እግዝትነ ማርያም ስንል አቆጣጠሩ
•  ከትንሿ ጣት ወደ ታች ይጀመርና

• በጠቋሚ ጣት ወደ ላይ ይፈጸማል ይህም እመቤታችን ድንግል ማርያም ከትሕትና ወደ ልዕልና ከፍ ማለቷን
የሚያሳይ ምሥጢር ነው ።

• ብእንት ሲባል በትንሿ ጣት ወደ ታች የሚጀመር ራሷን ዝቅ አድርጋ የትህትናዋ ምሳሌ ስለሆነ ነው ከላይ ወደ ታች ሚጀመረው።
         ==============
“ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፥ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል” - የማት ወን23፣12

•  የበእንት ፍጻሜ ወደላይ የሚያልቀው ሚስጢሩ እመቤታችን በመቃብር አልቆየችም ወደላይ አረገች ማለት ነው።

“ አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት”- መዝ 132፡8

ስንዱዋ እመቤት ቅድስት ቤተክርስቲያን ማንኛውም ነገር ያለ ትርጉም አታደርግም።

   http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስተዋህዶንእንወቅ/com.ortodoxtewahedo
2024/04/25 04:07:55
Back to Top
HTML Embed Code: