Telegram Group Search
                     አስተውሉ!!

▧ قَـالَ الشَّـيخ العلّامـة ابنُ بَاز -رَحِمَهُ الله-

قـراءة القـرآن من دون تحريك الـشفتين

« لا يعـتبر قـارئا ولا يحصل لـه فضل قـراءة الـقرآن إلا إذا تلفظ »
| [ الفتاوى (8/363) ] |

❖አንድ ሰዉ ቁርአንን ሲቀራ ከንፈሮቹን እያንቀሳቀሰ ሊቀራ ግድ ነዉ ይህ ካልሆነ ቁርአንን ቀርቷል ሊባል እንዲሁም የመቅራት ቱሩፋት ሊያገኝ አይችልም፡
          [አልፈታዋ ኢብነ ባዝ 8/363]
📖🔊
https://www.tg-me.com/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት የሚባል

اَللَّهُمَّ صَيِّبًا نَافِعًا.

‘አልሏሁምመ ሰይበን ናፊዐን

👉 አላህ ሆይ! ጠቃሚ ዝናብ (አድርገው)፡፡


ዝናብ ከዘነበ በኋላ የሚባል ዚክር

مُطِرْنَا بِفَضْلِ اللهِ وَرَحْمَتِهِ.

‘ሙጢርና ቢፈድሊልላሂ ወራሕመቲሂ

👉 በአላህ ትሩፋትና እዝነት ዝናብ ለማግኘት በቃን፡፡
@alfiqhulmuyser
ዐሹራ (عاشوراء)
.
➊ አሹራ ሚባለው ምን ቀን ነው?
.
➪ አብዛኛዎቹ ኡለሞች ባሉበት አቋም መሰረት አሹራ የሚባለው ከሙሀረም አስረኛው ቀን ነው። አሹራም የተባለበት ምክንያት አስረኛው ቀን ለማለት ተፈልጎበት ነው።ልክ እንደዚሁ ዘጠናኛው ቀን ታሱአ ይባላል።
.
➦አንዳንድ ኡለሞች የሙሀረምን ዘጠነኛው ቀን ነው አሹራ ሚባለው ቢሉም ከቋንቋ አንፃር እንኳን ስናየው ትክክል አለመሆኑን እንረዳለን።

.🏷 የዘንድሮ የዐሹራ ቀን (ሙሐረም 10) ነገ እሁድ 9 ሲሆን ሰኞ 10 ነው በመሆኑም ዓሹራእ ሰኞ ስለሆነ እሁድና ሰኞን መፆሙ የተወደደ ነው አላህ ይወፍቀን ።አሏህ በሰላም ያድርሰን።
.
❷ አሹራ ሚፆመው ለምንድነው?
.
➪ የአሹራ ቀን የሚፆምበት ዋነኛ ምክንያት አላህ ሙሳን እና በኒ ኢስራኢሎችን ከፊርአው ነፃ ያወጣበት ቀን ስለሆነ ነው።
.
▩ ማስረጃው
.
ኢብን አባስ እንዲህ ይላል
(( የአላህ መልእክተኛ ﷺ መዲና ሲገቡ አይሁዶች የአሹራን ቀን ሲፆሙ አዯቸውና
"ይህ ምንድነው?" ብለው ጠየቋቸው
ከዛም የሁዶች ሲመልሱ
" ይህ ደግ ቀን ነው አላህ በኒ ኢስራኢሎችን ከጠላታቸው ነፃ ያወጣበት ቀን ነው። ሙሳ ለምስጋና ፆሞታል" አሉ
የአላህ መልእክተኛም ﷺ
"እኔ በሙሳ ከናንተ ይበልጥ ተገቢ ነኝ" አሉና ፆሙት በመፆምም አዘዙ
📚(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
.
❸ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ፆመውታል?
.
➩ አዎ የአላህ መልእክተኛ ﷺ የአሹራ ፆምን ይፆሙት ነበር
.
▩ ማስረጃው
.
አኢሻ እንዲህ ትላለች
(የአሹራ ቀን ቁረይሾች በጃሂሊያ ግዜ ይፆሙት ነበር የአላህ መልእክተኛም ﷺ ይፆሙት ነበር...)
📚ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
.
❹ ከሙስሊሞች ውጪ ይህን ቀን ሚፆሙት አሉ?
.
➪ አዎ ከሙስሊሞች ውጪም ይህን ቀን ሚፆሙት ነበሩ እነሱም
.
➀ ሙሽሪኮች ፦ማስረጃው ከላይ በተራ ቁጥር ❸ ላይ ያሳለፍነው የአኢሻ ሀዲስ ነው
.
➁ አይሁዶች ፦ማስረጃው ከላይ በተራ ቁጥር ❷ ላይ ያሳለፍነው የኢብን አባስ ሀዲስ ነው
❺ ግዴታ ነው ወይስ ሱና?
.
➪ ረመዳን ከመደንገጉ በፊት የአሹራ ፆም ሙስሊሞች ላይ በግዴታነት መልኩ ተደንግጎ እንደነበር የሚጠቁሙ ሀደሶች አሉ ከነዛህ መሀከል ኢማም ቡኻሪ የዘገቡት የሰለማ ቢን አውከአ ሀዲስ አንዱ ነው። በዛ ሀዲስ ላይ መልእክተኛው ﷺ ሳያቅ ጠዋቱን የበላ ሰው የተቀረውን የቀን ክፍለ ግዜ እንዲፆም አዘዋል።
.
➪ ይህ የግዴታነት ትእዛዝ ግን በሗላ ላይ ተሽሮ በበርካታ ሀዲሶች ላይ እንደመጣው የአላህ መልእክተኛ ﷺ የፈለገ ሰው ይፁም ብለው ተናግረዋል።
.
▩ በመሆኑም የአሹራ ፆም የጠነከረ ሱና እንጂ ግዴታ አደለም።
.
❻ አስረኛው ቀን ብቻ ነው ሚፆመው?
.
➪ የአሹራን ቀን ብቻውን ነጥሎ ከመፆም ይልቅ ከሱ በፊት አንድን ቀን አስቀድሞ ፆሞ የአሹራንም ቀን አንድ ላይ መፆሙ የተወደደ ነው።
.
➦ ይህ ማለት ዘጠነኛውንና አስረኛውን ቀን ማለት ነው።
.
➦ ወይ ደግሞ አስራ አንደኛውንም ቀን አስከትሎ መፆሙ ይወደዳል።
.
▩ ማስረጃውም
.
አብደላህ ኢብን አባስ ባወራው ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል
"አላህ ካለ የሚመጣው አመት ዘጠነኛውን ቀን እንፆማለን"
ነገር ግን የሚቀጥለው አመት ሳይመጣ መልእክተኛው ሞቱ
📚 ሙስሊም ዘግቦታል
.
▤ አንድ ቀን አስቀድሞ ወይም ደግሞ አንድ ቀን አስከትሎ መፆሙ የተደነገገበት ምክንያትን ኡለሞች ሲያብራሩ ብዙ የሚጠቅሷቸው ነገሮች ቢኖሩም በዋነኝነት ግን ከአህለል ኪታቦች ለመለየት ሲባል የሚለው ይበልጥ ሚዛን ይደፍል።ምክንያቱም የአላህ መልእክተኛ ሚቀጥለው አመት ብደርስ ዘጠነኛውን ቀን ጨምሬ እፆማለው ያሉት አስረኛውን ቀን አህለል ኪታቦች እንደሚያልቁት ሲነገራቸው ነው።
.
➪ አንዳንድ ኡለሞች አስረኛውን ቀን ብቻ ነጥሎ መፆሙ የተጠላ እንደሆነ ይገልፃሉ።
.
➦ ነገር ግን ሸይኹል ኢስላም ዘጠነኛውን ወይም አስራ አንደኛውም መፆም ላልቻለ ሰው አስረኛውን ብቻ ቢፆምም እንደማይጠላ ይገልፃል። የሚችል ሰው ግን አስረኛውን ብቻ መነጠሉ ተገቢ እንዳልሆነ ይጠቅሳል።
.
❼ የሚወደደው አፇፇም
.
➪ የሚወደደው አፇፇም በቅደም ተከተል ሲቀመጥ
.
⓵ ዘጠነኛውን አስረኛውንና አስራ አንደኛውን ቀን ሶስቱን በተከታታይ መፆም (3 ቀኖች)
.
⓶ ዘጠነኛውንና አስረኛውን መፆም (2 ቀኖች)
.
⓷ አስረኛውን ቀን ብቻ መፆም (1 ቀን)
.
📚ይህንን ቅደም ተከተል ኢብኑል ቀይም ዛደል መአድ ላይ እንዲሁም ኢብን ሀጀር ፈትሀል ባሪ ላይ መርጠውታል። ኢብን ተይሚያም ኢቅቲዳ ኪታቡ ላይ ከኢማም አህመድ የዚህን አምሳያ ጠቅሷል።
.
➦ በርግጥ ሌሎች ኡለሞች የመረጣቸው ሌሎች ቅደም ተከተሎች ቢኖሩም ከመጡ ሀዲሶች አንፃር ከላይ የጠቀስነው ቅደም ተከተል ይበልጥ አመዛኙ አቋም ነው።
.
❽ የአሹራ ፆም ያለው ትሩፍት
.
➪ ኢማሙ ነሳኢ በዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ የአሹራ ፆም ያለፈውን አመት ወንጀል ያስምራል ብለዋል።
.
✍🏾 ኻሊድ ሙሀመድ (አቡ ሱለይማን)

#ሼር
https://www.tg-me.com/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
ጁምዓ ላይ መድረስ የሚቻለው በምንድን ነው?

ከኢማሙ ጋር አንድ ረከዓ ከደረሰ ጁምዓን በማግኘቱ የቀረውን አንድ ረከዓ ይጠበቅበታል:: ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ከጁምዓ አንድ ረከዓን የደረሰ ሰላት ላይ ደርሷል›› ኢማሙ ላይ የደረሰው ግን ከአንድ ረከዓ ባነሰ ከሆነ መሙላት ያለበት ዙህር ሰላትን ነው፡፡

የጁምዓ ሱና ሰላት
ከጁምዓ በፊት የሚሰገድ መደበኛ ሱና የለም፡፡ ነገር ግን ወቅቱ ከመድረሱ በፊት መደበኛ ያልሆነ ሱና ቢሰግድ ምንም ችግር የለውም ምክንያቱም ነብዩ (ﷺ) በጥቅሉ ሱና መስገድን አበረታተዋል፡፡ ከጁምዓ በኋላ ግን መደበኛ የሆኑ ሁለት፣ አራት ረከዓ ወይም ስድስት ረከዓ ሱናዎችን እንደሁኔታው ሊሰገድ ይችላል፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም ባስተላለፉት ሀዲስ ‹‹ነብዩ (ﷺ) ከጁምዓ በኋላ ሁለት ረከዓ ይሰግዱ ነበር››ቡኻሪ 937 ሙስሊም 882 በሌላ ሀዲስ ደግሞ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ ከጁምዓ በኋላ አራት ረከዓ ሱናዎችን ስገዱ››ሙስሊም 881 ኢብን ዑመርም ከጁምዓ በኋላ ስድስት ረከዓዎችን ይሰግዱ እንደነበር ‹‹ነብዩ ይፈፅሙት ነበር››አቡዳውድ 113ዐ እንዳሉ አቡዳውድ ዘግበዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከጁምዓ በኋላ የሚሰገድ መደበኛ ሱና ከፍተኛው ስድስት አነስተኛው ሁለት መሆኑን እንረዳለን::

የጁምዓ ሰላት አሰጋገድ
የጁምዓ ሰላት ድምፅ ከፍ በመደረግ የሚሰገዱ ሁለት ረከዓዎች እንደሆኑ በነብዩ (ﷺ) ተግባርና በዑለማዎች ስምምነት የተረጋገጠ ነው፡፡ በመጀመሪያው ረከዓ ከፋቲሃ በኋላ ሱረቱል ጁምዓ በሁለተኛው ረከዓ ደግሞ ሱረቱል ሙናፊቁንሙስሊም 877 ወይም በመጀመሪያው ረከዓ ከፋቲሃ በኋላ ሱረቱል አዕላ በሁለተኛው ሱረቱል ጋሺያ እንደሚነበብም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በተግባር አስተምረዋል፡፡ሙስሊም 878
በጁምዓ ዕለት የሚሰሩ ሱና ስራዎች
1. ከፍተኛ ምንዳ ለማግኘት በግዜ ወደ ጁምዓ መስጂድ መሄድ አቡ ሑረይራ ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ የጁምዓ ሰላት ገላውን ታጥቦ በመጀመሪያው ሰዓት የተጓዘ ግመል እንዳቀረበ ነው፣ በሁለተኛው ሰዓት የተጓዘ ከብት እንዳቀረበ ነው፣ በሶተኛው ሰዓት የተጓዘ ቀንዳማ በግ እንዳቀረበ ነው፣በአራተኛው ሰዓት የተጓዘ ዶሮ እንዳቀረበ ነው፤ በ አምስተኛው ሰዓት የሄደ እንቁላል እንዳቀረበ ነው፤ ኢማሙ ሚንበር ላይ ሲወጣ መላእክት ኹጥባ ለማድመጥ ይቀመጣሉ››ቡኻሪ 881 ሙስሊም 85ዐ 1. ገላን መታጠብ
2. ከላይ ባሳለፍነው ሀዲስ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ የጁምዓን ዕለት ገላውን ታጥቦ ….›› በየሳምነት ጁምዓ ገላ መታጠብ ሱና ሲሆን በተለይ የሠውነት ጠረን ባለበት ሰው ይበረታል፡፡ አንዳንድ ዑለማዎች ‹‹ጁምዓን ዕለት መታጠብ እያንዳንዱ አቅመ አዳም የደረሰ ሰው ላይ ግዴታ ነው››ቡኻሪ 879 ሙስሊም 486 የሚለውን ሀዲስ መሰረት በማድረግ በጁምዓ ገላ ትጥበት ግዴታ (ዋጂብ) ነው ይላሉ፡፡
3. ከትጥበት ውጭ ያሉ ሌሎች ፅዳቶችንም ማከናወን፡፡ ለምሳሌ፡- ሽቶ መቀባት ጥፍርን መቁረጥ፣ የብብትና የሀፍረተ ገላ አካባቢ ፀጉርን ማፅዳት፣ ቀድሞ ቀመስን ማሳጠር እና የመሳሰሉት፡፡
4.ከልብሶቹ ጥሩውን መልበስ: ኢብን ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ‹‹ዑመር ኢብን ኸጣብ መስጂድ በር ላይ ከሰይራዕ የመጣ ካባ ተመልክተው ‹‹ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ ይህንን ካባ ገዝተው ለጁመዐና እንግዶች ሲመጡ ቢለብሱት?›› ም አል ቡኻሪ ይህንን ሀዲስ በጁምዓ ዕለት ጥሩን ልብስ መልበስ ሱና ስለ መሆኑ መረጃ አድርገው የተጠቀሙበት ሲሆን አልሃፊዝ ኢብን ሀጀር መረጃ ሊሆን የቻለው ነብዩ (ﷺ) የዑመርን ሀሳብ ባለመቃወም ስለተቀበሉት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ነብዩም (ﷺ) ‹‹ለስራ ከምትለብሷቸው ሁለት ልብሶች(ሁለት ልብሶች ማለት ከወገብ በታችና ከወገብ በላይ አንድ ጊዜ የሚለብሱትን ማለት ነው) ውጪ ለጁምዓ የሚለበሱ ሁለት ልብሶችን መልካም ነው›› ብለዋል::አቡዳውድ 1ዐ78 ኢብን ማጃህ 1ዐ95
5. በነብዩ (ﷺ) ላይ ሰላትና ሰላም ከሌላው ቀን በበለጠ መልኩ ማስፈን ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ በጁምዓ ዕለት በይበልጥ እኔ ላይ ሰላት አውርዱ››አቡዳውድ 1ዐ47 ነሳኢይ 3/91
6. የጁምዓ ሱብሂ ሰላት ላይ በመጀመሪያው ረከዓ ሱረቱ ሰጅዳህ በሁለተኛው ሱረቱል ኢንሳን ማንበብ የነብዩ (ﷺ) ተደጋጋሚ ተግባር ስለነበር ሱና ነው፡፡ በቀኑ ክፍለ ጊዜ ደግሞ ሱረቱል ከህፍን ማንበብ፡፡ቡኻሪ 891ነ ብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል‹‹በጁምዓ ዕለት ሱረቱል ከህፍን ያነበበ ዕለተ ቂያማ ከእግሩ እስከ ሰማይ ጫፍ የሚያበራ ብርሐን ይኖረዋል፡፡ እንዲሁም ከዕለቱ ጁምዓ እስከ ቀጣዩ ጁምዓ የሚፈፀም ኃጢአት ይማርለታል››ሃኪም 2/368
7. መስጂድ ገብቶ ከመቀመጡ በፊት ሁለት ረከዓ መስገድ ነብዩ (ﷺ) ያዘዙትቡኻሪ 93ዐ ተግባር ሲሆን ኢማሙ ኹጥባ ላይ ከሆነ ግን ሰላቱን ቀልጠፍ አድርጎ መስገድ አለበት::
8. ጁምዓ ዱዓ ይበልጥ ተቀባይነት ያለው ወቅት በመሆኑ ዱዓ ማብዛት፡ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል ‹‹በጁምዓ ዕለት አንድ ሰው እየሰገደ ሊገጥመው የሚችል ልዩ ሰዓት አለ፡፡ በዚያ ሰዓት አንድ ሰው አላህን አንድ ነገር ቢጠይቅ ወዲያው ይሰጠዋል፡፡››ቡኻሪ 935 ሙስሊም 852


ቻናላችን ይቀላቀሉ
ለሌሎችም ያስተዋውቁት
@alfiqhulmuyser
ጥያቄ፦ በምክንያትም ይሁን ያለ ምክንያት የጀናባን ትጥበት ማዝግየት ብይኑ ምንድነው?

መልስ፦ የሶላት ወቅት እስካልደረሰ ድረስ ችግር የለውም። የሶላት ወቅት ከደረሰ ታጥቦ ሶላቱን መፈፀም ግድ ይለዋል። ለምሳሌ ዙህርና 0ስርን ይመስል። ረፋድን በተመለከተ ግን ለምሳሌ ዙህር ላይ እስከሚታጠብ ድረስ ቢዘገይ (ችግር የለውም።) ሶሒሕ አልቡኻሪና ሙስሊም ላይ ሑዘይፋና አቡ ሁረይራ ባስተላለፉት ሐዲሥ እነሱ ነብዩን ﷺ ሲያገኙ ይሰወራሉ። ነብዩ ﷺ "ምንድነው ነገራችሁ?" ሲሏቸው "ጀናባ ላይ ነበርንና ጦሀራ ላይ ሳንሆን አብረንህ መቀመጥን ስለጠላን ነው" አሉ። በዚህን ጊዜ ነብዩ ﷺ "ሙስሊም አይነጀስም" አሉ። እና ያለ ጦሀራ መቆየታቸውን አልነቀፉም። አላህ ሆይ! በሳቸው ላይ ሶላትህን አውርድ።

ከሸይኽ ኢብኑ ባዝ ረሒመሁላህ ፈትዋ የተወሰደ
ምንጭ፦ https://binbaz.org.sa/fatwas/15618/%D9%85%D8%A7-%D8%AD%D9%83%D9%85-%D8%AA%D8%A7%D8%AE%D9%8A%D8%B1-%D8%BA%D8%B3%D9%84-%D8%A7%D9%84%D8%AC%D9%86%D8%A7%D8%A8%D8%A9


#ሼር ያድርጉ♻️
Join ይበሉ👇
••••••••••📚📚•••••••••••
www.tg-me.com/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
••••••••••📚📚•••••••••••
🏷በሶላት ላይ እጅ የሚነሳባቸው ቦታዋች
ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር - ረዲየሏሁ ዐንሁማ - ስለ ነብዩ - ﷺ - አሰጋገድ ሲያወራ እንዲህ ይላል ፦ [ ከሁለት ረከዓዎች ሲነሱ እጃቸውን ያነሱ ነበር። ] (ቡኻሪ ፥ 739).

♦️በጥቅሉ እጅ የሚነሳባቸው ቦታዎች አራት ናቸው ፦
1.ተክቢረተል ኢሕራም ሲያደርግ
2.ወደሩኩዕ ሊወረድ ሲል
3.ከሩኩዕ ሲነሳ እና
4.ከመጀመሪያው ተሸሁድ ሲነሳ. ከነዚህ ውጭ እጅ የሚነሳበት ቦታ የለም።

💢የእጅ አነሳስ💢

🛑ሶላት ስንጀምር በተክቢረተል ኢሕራም ጊዜ (አላሁ አክበር በምንል ጊዜ)፤
እጃችንን በትከሻችን ወይም በጆሯችን ትክክል በምናደርግ ጊዜ፤
የእጆቻችን ውስጣዊ ክፍል (መዳፎቻችን) የሚዞሩት ወደ ፊታችን ሳይሆን፣
ወደ ቂብላ አቅጣጫ ነው።

🛑ብዙዎቻችን ግን ሳናውቅም ይሁን ሳናስበው በመርሳት፤
ብዙ ጊዜ የእጆቻችን መዳፍ ወደ ቂብላ ፊት ለፊት የተቅጣጨ ሳይሆን፣
ወደ ፊታችን የተገለበጠ ነው።

🛑 እጆች ሲነሱ ጣቶች ተጠጋግተው መሆን እንዳለባቸው የሚያስገነዝብ ትክክለኛ ሀዲስ ተዘግቧል።

🛑ሴቶችም እንደ ወንዶች በተመሳሳይ መልኩ እስከ ትከሻቸው ወይም እስከ ጆሯቸው ድረስ እጆቻቸውን ማንሳታቸው ሱንና ነው። ከዚህ በተቃራኒ ያሉ እይታዎች "እኔ ስሰግድ እንዳያችሁኝ አስመስላችሁ ስገዱ" ከሚለው ወሳኝ ነብያዊ መርህ ጋር የሚጣረስ አቋም ነው። ኡሙ ደርዳእ እስከ ትክሻዋ ድረስ እንደምታነሳም ተዘግቧል።

🛑 እጆችን እስከ ደረት/ጡቶች ድረስ ብቻ ከፍ ማድረግ፣ በራስ ቅል ትይዩ እስከሚሆኑ ከፍ ማድረግ፣ እጆችን ወደ ጎን አራርቆ ማንሳት፣ ጣቶችን በታትኖ ወይም ጣቶችን ጨብጦ ከፍ ማድረግ፣ መዳፍን ወደጆሮ ወይም ወደ ፊት ማዞር እነዚህ ሁሉ ሱንናውን የሚጻረሩ ተግባራቶች ናቸው።


#ሼር ያድርጉ
••••••••••📚📚•••••••••••
Https://www.tg-me.com/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser/181
••••••••••📚📚•••••••••••
•ወዱእ ያለው መስሎት ያለ ውዱእ የሰገደ ሰው ሶላቱን እንደገና መስገድ አለበት። ያለ ውዱእ ሶላት የለምና። ያስታወሰው ወቅት ካለፈ ቢሆን እንኳ ሶላቱን መመለስ አለበት።
ኢማሙ ረስቶ ያለ ውዱእ ካሰገደስ? የተከታዮቹ ሶላት ይበላሻል?
* ሶላቱ ሳይጠናቅቅ ካስታወሰ መቀጠል የለበትም። ይልቁንም ሌላ ሰው ተክቶ ይወጣል። የተተካው ሰው ከመጀመሪያ መጀመር ሳይጠበቅበት የቀረውን ያሰግዳል።
* ኢማሙ ውዱእ እንዳልነበረው ያስታወሰው ሶላቱን ካጠናቀቀ በኋላ ከሆነ ግን የተከታዮቹ ሶላት ትክክል ስለሆነ መመለስ (ዳግም መስገድ) አይጠበቅባቸውም። ይህንን የኢብኑ ዑሠይሚን ፈትዋ ማየት ትችላላችሁ። https://binothaimeen.net/content/7883


•ኹፍ ወይም ካልሲ በጦሀራ የለበሰ መስሎት አብሶ የሰገደ ሰው ኋላ ላይ በጦሀራ ሆኖ እንዳልለበሰው ካስታወሰ ውዱኡንም ሶላቱንም መመለስ አለበት። ማለትም እንደገና ውዱእ አድርጎ መስገድ ይኖርበታል።
Forwarded from HUDA SOFT
📖እነሆ የቁርአን ወር ረመዷን ደጃችን ደርሷል  በረመዷን ምንያህል ግዜ ቁርአንን ለመጨረስ አቅደሀል/አቅደሻል?

شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِّنَ الْهُدَىٰ وَالْفُرْقَانِ

“(እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዷን ወር ነው።” (አል-በቀራ 2፤185)

አንድን የቁርዓን ሐርፍ የቀራ በአስር እጥፍ እንደሚባዛለት በሚከተለው የነብዩ ሐዲስ ተነግሯል-
"من قرأ حرفا من كتاب الله فله به حسنة والحسنة بعشر أمثالها لا أقول الم حرف ولكن الف حرف ولام حرف وميم حرف" الترمذي: ٢٩١٠، الدارمي: ٣٣٥١

“ከአላህ ኪታብ አንድ ሀርፍ የቀራ አንድ ሀሰና (መልካም አጅር) አለው አንዱ ሀሰና በአስር አምሳያ ይባዛል፡፡ አሊፍ ላም ሚም የሚለው እንደ አንድ ሀርፍ ነው ብየ አልልም፡፡ ግን አሊፍ ሀርፍ ነው ላም ሀርፍ ነው ሚም ሀርፍ ነው፡፡” (ቲርሚዚይ: 2910, ዳሪሚይ፡ 3351)
በዚህ ስሌት ቁርዓን የቀራ ሰው በርካታ ሀሰናቶችን ያገኛል፡፡
እያንዳንዱ ሙስሊም በተለይ በረመዷን ወር ፕሮግራም አውጥቶ የተወሰኑ ጁዝኦችን በቀንም ይሁን በሌሊት ሊቀራ ይገባዋል፡፡

በቀላሉ ለመጨረስ ከላይ ያለው ፕሮግራም በየቀኑ ተጠቀሙት። ምናልባት በምክንያት ፕሮግራማቹሁን ባትፈፅሙ ሰዓት አመቻችታችሁ ቀዷ አውጡ። ኢንሻአላህ በመጨረሻም አላማችሁን ታሳካላችሁ!

ለሁሉም እንዲደርስ ሼር አድርጉ
#ሼር🔂 #ሼር 🔂
📖ረመዷን የቁርአን ወር📖
-
--------------------------------

©HUDA SOFT
https://www.tg-me.com/HUDASOFT
¶ ፊቅሁል ኢስላም ¶
Photo
#ፆምን_የሚያበላሹ_ነገራትን_የተመለከተ_አጠር_አጠር_ያሉ_ተከታታይ_ትምህርቶች
━━━━━━━━━━━━━━━━
فتاوى الصيام
🔰لفضيلة الشيخ العلامة عبد العزيز ابن باز رحمه الله الرسالة رقم ( 53 )
مفسدات الصوم
⭕️ፆምን ከሚያበላሹ ነገራት መካከል
🔰الحكم الأول
🔰{ حكم الإبر المغذية }

#ክፍል_አንድ
⭕️የቫይታሚንና የምግብነት ይዘት ያላቸው መርፌ መወጋት ፆም ስለማጥፋቱና የምግብነት ይዘት የሌላቸው ማናቸውም መርፌዎች ፆምን የማያጠፋ ስለመሆኑ
🔰السؤال رقم - 1 :
⭕️ጥያቄ አንድ
⭕️ጠያቂው
🔰《ﻗﺮﺃﺕ ﻓﻲ ﺑﻌﺾ اﻟﻜﺘﺐ اﻟﻔﻘﻬﻴﺔ ﻭﻣﻨﻬﺎ ﻛﺘﺎﺏ (ﻓﻘﻪ اﻟﺴﻨﺔ) ﻟﻤﺆﻟﻔﻪ اﻟﺸﻴﺦ ﺳﻴﺪ ﺳﺎﺑﻖ ﺃﻥ اﻹﺑﺮ اﻟﻤﻐﺬﻳﺔ ﻭﻏﻴﺮﻫﺎ اﻟﺘﻲ ﻻ ﺗﺪﺧﻞ ﻋﻦ ﻃﺮﻳﻖ اﻟﺠﻮﻑ ﺃﻭ اﻟﻔﻢ ﻟﻴﺴﺖ ﻣﻔﻄﺮﺓ،

⭕️ዐብድል ዓዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና…
《በሰይድ ሳቢቅ የተፃፈውን ፊቅሂ ሱና ሚባለውን ኪታብ ሳነብ የምግብነት ይዘት ያላቸው መርፌዎች በአፍ በኩል ወደ ሆድ ካልገባ በቀር በመርፌ መልክ መወጋት ፆምን አያበላሽም ሚልን ነገር አንብቤ ነበር》ይህ እንዴት ይታያል???? ተብለው ተጠይቀው
ሲመልሱ…… 》
🔰الجواب :
🔰《 اﻟﺼﻮاﺏ ﺃﻥ اﻹﺑﺮ اﻟﻤﻐﺬﻳﺔ ﺗﻔﻄﺮ اﻟﺼﺎﺋﻢ ﺇﺫا ﺗﻌﻤﺪ اﺳﺘﻌﻤﺎﻟﻬﺎ، ﺃﻣﺎ اﻹﺑﺮ اﻟﻌﺎﺩﻳﺔ ﻓﻼ ﺗﻔﻄﺮ اﻟﺼﺎﺋﻢ، ﻭاﻟﻠﻪ ﻭﻟﻲ اﻟﺘﻮﻓﻴﻖ.
⭕️《የምግብነት ይዘት ያለውን መርፌ አውቆ መወጋት ፆምን ያበላሻል።
ምግብነት የሌላቸው ነገር ግን ፈዋሽ መድሀኒቶችን በመርፌ መልክ (መውሰድ)መወጋት ፆምን አያበላሽም።》ብለዋል
📚 المصدر: مجموع الفتاوى (15/258 )
📚ምንጭ የሼኹ
መጅሙዕል ፈታዋ(15/258)

#ረመዳን_ከመድረሱ_በፊት_በእውቀት_ለመፆም_እንዘጋጅ!
#ክፍል_2 ይቀጥላል
🔂ሼር #ሼር

•••••••••••••✎••••••••••••
https://www.tg-me.com/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
•••••••••••••✎••••••••••••
#ፆምን_የሚያበላሹ_ነገራትን_የተመለከተ_አጠር_አጠር_ያሉ_ተከታታይ_ትምህርቶች
ክፍል 2
━━━━━━━━━━━━━━━━
🔰{ ﺣﻜﻢ ﺇﺑﺮﺓ اﻟﺘﺨﺪﻳﺮ (اﻟﺒﻨﺞ) ﻭﺗﻨﻈﻴﻒ اﻟﺴﻦ ﺃﻭ ﺣﺸﻮﻩ ﺃﻭ ﺧﻠﻌﻪ ﻋﻨﺪ اﻟﻄﺒﻴﺐ }
⭕️የማደንዘዣ መርፌ መወጋት፣ጥርስ ማሳጠብ፣ጥርስ ማስሞላትና ጥርስ የማስነቀል
ብይን(ሁክም)
🔰 السؤال رقم - 2 :
🔰 ﺇﺫا ﺣﺼﻞ ﻟﻹﻧﺴﺎﻥ ﺃﻟﻢ ﻓﻲ ﺃﺳﻨﺎﻧﻪ، ﻭﺭاﺟﻊ اﻟﻄﺒﻴﺐ، ﻭﻋﻤﻞ ﻟﻪ ﺗﻨﻈﻴﻔﺎ ﺃﻭ ﺣﺸﻮا ﺃﻭ ﺧﻠﻊ ﺃﺣﺪ ﺃﺳﻨﺎﻧﻪ، ﻓﻬﻞ ﻳﺆﺛﺮ ﺫﻟﻚ ﻋﻠﻰ ﺻﻴﺎﻣﻪ؟ ﻭﻟﻮ ﺃﻥ اﻟﻄﺒﻴﺐ ﺃﻋﻄﺎﻩ ﺇﺑﺮﺓ ﻟﺘﺨﺪﻳﺮ ﺳﻨﻪ، ﻓﻬﻞ ﻟﺬﻟﻚ ﺃﺛﺮ ﻋﻠﻰ اﻟﺼﻴﺎﻡ؟
⭕️ዓብድል ዐዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና
⭕️《አንድ ሰው ጥርሱን አሞት የጥርስ ሀኪም ቤት ሲሂድ የህክምና ጠበብቶች ጥርሱ እንዲታጠብ፣ወይም የተቦረቦረ ጥርሱ እንዲሞላ፣ወይም በእጅጉ የተጎዳ ጥርሱ እንዲነቀል ቢያዙና ለዚህም ሲሉ የማደንዘዣ መርፌ ቢወጉት ከእነዚህ ከተሰጡት ነገራት መካከል ፆሙን የሚያበላሹበት ነገራት አሉ???》ተጠይቀው ሲመልሱ……》
🔰الجواب :
🔰《ﻟﻴﺲ ﻟﻤﺎ ﺫﻛﺮ ﻓﻲ اﻟﺴﺆاﻝ ﺃﺛﺮ ﻓﻲ ﺻﺤﺔ اﻟﺼﻴﺎﻡ، ﺑﻞ ﺫﻟﻚ ﻣﻌﻔﻮ ﻋﻨﻪ،》
⭕️《ከላይ ከተጠቀሱት መድሀኒቶችም ሆነ የህክምና ተግባራት መካከል አንድም የታማሚውን ፆም ሊያበላሽ የሚችል ነገር የለም።》
🔰《ﻭﻋﻠﻴﻪ ﺃﻥ ﻳﺘﺤﻔﻆ ﻣﻦ اﺑﺘﻼﻉ ﺷﻲء ﻣﻦ اﻟﺪﻭاء ﺃﻭ اﻟﺪﻡ،》
⭕️《ይሁንና ታካሚው የጥርስ ህክምና በሚያካሄድበት ወቅት ምንም አይነት መድሀኒት ወይም ደም ወደ ሆዱ እንዳይገባ በሚችለው ሁሉ መጠንቀቅ አለበት።》
🔰《ﻭﻫﻜﺬا اﻹﺑﺮﺓ اﻟﻤﺬﻛﻮﺭﺓ ﻻ ﺃﺛﺮ ﻟﻬﺎ ﻓﻲ ﺻﺤﺔ اﻟﺼﻮﻡ؛ ﻟﻜﻮﻧﻬﺎ ﻟﻴﺴﺖ ﻓﻲ ﻣﻌﻨﻰ اﻷﻛﻞ ﻭاﻟﺸﺮﺏ. ﻭاﻷﺻﻞ ﺻﺤﺔ اﻟﺼﻮﻡ ﻭﺳﻼﻣﺘﻪ.》
⭕️《ከላይ የተጠቀሰው የማደንዘዣ መርፌም ፆሙን አያበላሽም ምክንያቱም እንደ ምግብና መጠጥ ሆኖ ሊያገለግል አይችልምና።》
📚 المصدر :
مجموع فتاوى (15/258 )
📚ምንጭ
የሼኹ መጅሙዕል ፈታዋ(15/258)


#ረመዳን_ከመድረሱ_በፊት_በእውቀት_ለመፆም_እንዘጋጅ!
#ክፍል_3 ይቀጥላል
🔂ሼር #ሼር

•••••••••••••••✎•••••••••••••••
https://www.tg-me.com/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
•••••••••••••••✎•••••••••••••••
#ፆምን_የሚያበላሹ_ነገራት
ክፍል3
━━━━━━━━━━━━━━━━
🔰فتاوى الصيام

🔰لفضيلة الشيخ العلامة عبد العزيز ابن باز رحمه الله ا
مفسداتالصوم

#ፆምና_የጥርስ_ሳሙና

🔰السؤال رقم 1 :
《ما حكم استعمال معجون الأسنان》
ዓብድል ዓዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና
⭕️《ፇሚዎች በፆማቸው እለት የጥርስ ሳሙናን በመጠቀም ጥርሳቸውን ቢያፀዱስ???》ተብለው ተጠይቀው ሲመልሱ…
🔰 الجواب :
《ﺗﻨﻈﻴﻒ اﻷﺳﻨﺎﻥ ﺑﺎﻟﻤﻌﺠﻮﻥ ﻻ ﻳﻔﻄﺮ ﺑﻪ اﻟﺼﺎﺋﻢ ﻛﺎﻟﺴﻮاﻙ، ﻭﻋﻠﻴﻪ اﻟﺘﺤﺮﺯ ﻣﻦ ﺫﻫﺎﺏ ﺷﻲء:ﻣﻨﻪ ﺇﻟﻰ ﺟﻮﻓﻪ، ﻓﺈﻥ ﻏﻠﺒﻪ ﺷﻲء ﻣﻦ ﺫﻟﻚ ﺑﺪﻭﻥ ﻗﺼﺪ ﻓﻼ ﻗﻀﺎء ﻋﻠﻴﻪ. 》
⭕️መልስ…
《ፆመኞች በፆማቸው እለት በጥርስ ሳመና ጥርሳቸውን ማፅዳት ይችላሉ ይህን ማድረጋቸው ፆማቸውን በፍፁም አያበላሽባቸውም ልክ እንደ ሲዋክ(መፋቂያ) ነውና።
ይሁንና የጥርስ ሳሙናው ወደ ሆዳቸው ሾልኮ እንዳይገባ ይጠንቀቁ።》ብለዋል
📚 المصدر : مجموع فتاوى (15/260 )
📚ምንጭ:
📚የሼኹ መጅሙዕል ፈታዋ(15/260)

☑️ሼር
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
T.me/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
#ፆምን_የሚያበላሹ_ነገራት
ክፍል4
#ፆምና_የአይን_ወይም_የጆሮ_ጠብታ(የአይንና የጆሮ ፈሳሽ መድሀኒቶችን መጠቀም)
━━━━━━━━━━━━━━━━

🔰السؤال رقم 2 :
《 ما حكم استعمال قطرة العين والأذن 》
⭕️ዐብድልዐዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና
《ፆመኞች በመፆም ላይ እያሉ የአይን አለያም የጆሮ ጠብታ መጠቀም ይችላሉን???》 ተብለው ተጠይቀው ሲመልሱ…
🔰 الجواب :
《 ﻗﻄﺮﺓ اﻟﻌﻴﻦ ﻭاﻷﺫﻥ ﻻ ﻳﻔﻄﺮ ﺑﻬﻤﺎ اﻟﺼﺎﺋﻢ ﻓﻲ ﺃﺻﺢ ﻗﻮﻟﻲ اﻟﻌﻠﻤﺎء. 》
⭕️መልስ:
《አዎ መጠቀም ይችላሉ የአይንና የጆሮ ጠብታ ፆምን አያጠፉም
📚 المصدر : مجموع الفتاوى  (15/260 )
📚ምንጭ:
📚የሼኹ መጅሙዕል ፈታዋ(15/260)

#ክፍል5 ይ ቀ ጥ ላ ል

☑️ሼር
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
   T.me/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
#ፆምን_የሚያበላሹ_ነገራት
ክፍል5
#ፆምና_የአፍንጫ_ጠብታ
━━━━━━━━━━━━━━━━

🔰السؤال رقم 3 :
🔰《 ما حكم استعمال قطرة الأنف في نهار رمضان وهل تفطر 》
⭕️ዐብድዓዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና :
《ፃሚዎች በፆማቸው እለት የአፍንጫ ጠብታ መድሀኒት መጠቀም ይችላሉን????》ተብለው ተጠይቀው ሲምልሱ…
🔰 الجواب :
《ﺃﻣﺎ اﻟﻘﻄﺮﺓ ﻓﻲ اﻷﻧﻒ ﻓﻼ ﺗﺠﻮﺯ؛ ﻷﻥ اﻷﻧﻒ ﻣﻨﻔﺬ، 》
⭕️《በአፍንጫ የሚወሰዱ ጠብታ(ፈሳሽ) መድሀኒቶች ወደ ሆድ ስለሚደርሱ ፆምን ያበላሻሉ።》
🔰《ﻭﻟﻬﺬا ﻗﺎﻝ اﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ اﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ: «ﻭﺑﺎﻟﻎ ﻓﻲ اﻻﺳﺘﻨﺸﺎﻕ ﺇﻻ ﺃﻥ ﺗﻜﻮﻥ ﺻﺎﺋﻤﺎ » .
⭕️ለዚህም ሲባል ነው ነብዩ ﷺ 《ውድእ ስታደርጉ ውሀ  በአፈንጫቹህ በደምብ ወደላይ ሳቡ ፆመኛ ከሆናቹህ ግን በፍፁም።》ያሉት።
🔰《ﻭﻋﻠﻰ ﻣﻦ ﻓﻌﻞ ﺫﻟﻚ اﻟﻘﻀﺎء ﻟﻬﺬا اﻟﺤﺪﻳﺚ، ﻭﻣﺎ ﺟﺎء ﻓﻲ ﻣﻌﻨﺎﻩ ﺇﻥ ﻭﺟﺪ ﻃﻌﻤﻬﺎ ﻓﻲ ﺣﻠﻘﻪ، ﻭاﻟﻠﻪ ﻭﻟﻲ اﻟﺘﻮﻓﻴﻖ.》
⭕️《የሆነው ሆኖ ግን አንድ ፆመኛ በአፍንጫው የአፍንጫ ጠብታ(ፈሳሽ የአፈንጫ መድሀኒት) ከተጠቀመ ፆሙ ተበላሽቷልና በሌላ ቀን ይህን ፆም መተካት ግድ ይለዋል።》ብለዋል
📚 المصدر
📚مجموع الفتاوى  (15/261 )
📚ምንጭ:
📚የሼኹ መጅሙዕል ፈታዋ(15/261)


#ክፍል6 ይ ቀ ጥ ላ ል

☑️ሼር
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
   T.me/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
#ፆምን_የሚያበላሹ_ነገራት
ክፍል6
━━━━━━━━━━━━━━━━
⭕️የአስም ህመምተኞች በፆም ላይ እያሉ  በአፍ የሚወሰድ  ቬንቶሊን ወይም ኢንሀለር በመባል የሚታወቀውን  ፈዋሽ አየርን መውሰድን የተመለከት ገለፃ
               فتاوى الصيام
🔰لفضيلة الشيخ العلامة عبد العزيز ابن باز رحمه الله الرسالة
📚رقم  ( 56 )
             مفسدات الصوم
⭕️ዓብድልዓዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና
السؤال رقم 1
🔰《 : ﻣﺎ ﺣﻜﻢ اﺳﺘﻌﻤﺎﻝ اﻟﺒﺨﺎﺥ ﻓﻲ اﻟﻔﻢ ﻟﻠﺼﺎﺋﻢ ﻧﻬﺎﺭا ﻟﻤﺮﻳﺾ اﻟﺮﺑﻮ ﻭﻧﺤﻮﻩ؟
⭕️《የአስም ታማሚዎች በፆም ላይ እያሉ ቢያማቸውና ቬንቶሊን የሚባለውን ፈዋሽ አየር በአፋቸው ቢወስዱ ፆማቸው ይበላሻልን????》ተብለው ተጠይቀው ሲመልሱ…
🔰《 : ﺣﻜﻤﻪ اﻹﺑﺎﺣﺔ ﺇﺫا اﺿﻄﺮ ﺇﻟﻰ ﺫﻟﻚ؛ ﻟﻘﻮﻝ اﻟﻠﻪ ﻋﺰ ﻭﺟﻞ: {ﻭﻗﺪ ﻓﺼﻞ ﻟﻜﻢ ﻣﺎ ﺣﺮﻡ ﻋﻠﻴﻜﻢ ﺇﻻ ﻣﺎ اﺿﻄﺮﺭﺗﻢ ﺇﻟﻴه》
⭕️《ሳያመው ዝም ብሎ እንዳይወስድ እንጂ አሞት ከወሰደው ፆሙ አይበላሽም።》
🔰《ﻭﻷﻧﻪ ﻻ ﻳﺸﺒﻪ اﻷﻛﻞ ﻭاﻟﺸﺮﺏ ﻓﺄﺷﺒﻪ ﺳﺤﺐ اﻟﺪﻡ ﻟﻠﺘﺤﻠﻴﻞ ﻭاﻹﺑﺮ ﻏﻴﺮ اﻟﻤﻐﺬﻳﺔ.》
⭕️ምክንያቱም …
《ይህ ፈዋሽ መድሀኒት እንጂ ምግብም አይደለም ወደ ሆድም አይደርስም።》ብለዋል።
📚 المصدر : مجموع فتاوى  (15/265 )
📚ምንጭ
📚የሼኹ መጅሙዕል ፈታዋ(15/265)
#ክፍል7 ይ ቀ ጥ ላ ል

☑️ሼር
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
   T.me/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
#ፆምን_የሚያበላሹ_ነገራት
ክፍል7
#ትውከት(ማስመለስ)ና ፆም
━━━━━━━━━━━━━━━━
🔰سئل عبد العزيز ابن باز…
⭕️ዓብድልዓዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና
🔰السؤال رقم  :
《ﻣﺎ ﺣﻜﻢ ﻣﻦ ﺫﺭﻋﻪ اﻟﻘﻲء ﻭﻫﻮ ﺻﺎﺋﻢ- ﻫﻞ ﻳﻘﻀﻲ ﺫﻟﻚ اﻟﻴﻮﻡ ﺃﻡ ﻻ؟》
⭕️《ትውከት(ማስመለስ) ፆም ያበላሻልን(ያቋርጣልን)??? ተብለው ተጠይቀው ሲመልስ……
🔰 الجواب :
《ﺣﻜﻤﻪ ﺃﻧﻪ ﻻ ﻗﻀﺎء ﻋﻠﻴﻪ، ﺃﻣﺎ ﺇﻥ اﺳﺘﺪﻋﻰ اﻟﻘﻲء ﻓﻌﻠﻴﻪ اﻟﻘﻀﺎء؛ ﻟﻘﻮﻝ اﻟﻨﺒﻲ ﺻﻠﻰ اﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ: «ﻣﻦ ﺫﺭﻋﻪ اﻟﻘﻲء ﻓﻼ ﻗﻀﺎء ﻋﻠﻴﻪ، ﻭﻣﻦ اﺳﺘﻘﺎء ﻓﻌﻠﻴﻪ اﻟﻘﻀﺎء »
⭕️《ትኡከት በራሱ ግዜ ገፍቶ ከመጣና ካስመለሰ ፆምን ማያበለሽ ሲሆን ነገርግን ፇሚው(ፆመኛው) ግለሰብ ማስመለስ ፈልጎ ለማስመለስ የተለያየ ጥረት በማድረግ ካስመለሰ ፆሙ ይበላሻል።》ብለዋል።
📚 المصدر :
📚 مجموع الفتاوى  (15/26)
📚ምንጭ
📚የሼኹ መጅሙዕል ፈታዋ(15/26)

☑️ሼር
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
   T.me/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
•••••••••••••📖📖•••••••••••••
🌤ከሱሁር በፊት ጀናባ ሆኖ ሱብሒ አዛን ከተባለ ቡሀላ ጀናባ ለማውረድ መታጠብን የተመለከተ ገለፃ

عَنْ عَائِشَةَ وَأمُّ سَلَمَةَ رَضْيَ الله عَنْهُمَا:
ዓኢሻህ እና ኡሙ ሰለማህ አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና
أنً رَسُولَ اللهِ - صلى الله عليه وسلم - كَانَ يُدْركُهُ الْفَجْرُ وَهُوَ جُنٌبٌ مِنْ أهلِهِ. ثُمَّ يَغتَسِلُ وَيصُومُ.
ነብዩ ﷺ ጀናባ ኖሮባቸው ሳይታጠቡ ሱቢህ ይደርስና ታጥበው ሱብሒህ ሰግደው ይፆሙ ነበር።ብላለች
المعنى الإجمالي:
كان النبي صلى الله عليه وسلم يجامع  في الليل، وربما أدركه الفجر وهو جنب لم يغتسل،
ويتم صومه ولا يقضي.
ይህ ማለት ነብዩ ﷺ ለሊት ላይ ጂማዕ(ወሲባዊ ግንኙነት) ያደርጉና ሳይታጠቡ ሱብሂ ከደረሰና ሱብሂ ከገባ ቡሀላ ታጥበው ፆማቸውን ይቀጥሉ ነበር ማለት።
▫️وهذا الحكم في رمضان وغيره،
ይህ ደግሞ የረመዷን ፆም ይሁን ሌላ ፆም ልዩነት ሳይኖረው በእኩል ተፈፃሚነቱ የፀና ነው።
وهذا مذهب جمهور العلماء، ولم يخالفهم إلا قليل ممن لا يعتد بخلافهم، وقد حكي  بعضهم الإجماع على هذا القول.
ይህ የጁሙሁሩል ዑለማእ አቋም ሲሆን
ከጥቂቶች ሙስሊም ሙሁራን በቀር ይህንን አቋም የተፃረረ የለም።
አንዳንዶች ኢጅማዑል ዑለማም አፅንተውታል የሚሉ ሁሉ አሉ።
📣ما يؤخذ من الحديث:
ከዚህ ሀዲስ የምንገነዘባቸው ቁም ነገሮች
١- صحة صوم من أصبح جنباً، من جماع في الليل.
1ኛ:ጀናባውን ሳያወርድ ሱብሒ የደረሰበት ሰው ፇሚ ከነበረ ፆሙ ትክክል መሆኑ
٢- يقاس على الجماع الاحتلام بطريق الأولى، لأنه إذا كان مرخصاً فيه من المختار، فغيره أولى.
2ኛ:በጂማዕ(በወሲባዊ ግንኙነት) ላይ በመንተራስ በኢሕቲላም ምክንያት የተፈጠረ ጀናባም ከላይ ከተጠቀሰው የተለየ ህግ እንደማኖረው በአብላጫ የሙስሊም ሊቃውንት ብይን ተረጋግጧል።
٣- أنه لا فرق بين الصوم الواجب والنفل، ولا بين رمضان وغيره.
3ኛ:የጀናባ አለመውረድ በፆም ላይ ተፅዕና አለመፈጠሩ በግዴታ(ዋጅብ) ፆምም ሆነ በተወዳጅ(ሱና) ፆም ላይ እኩል ተፈፃሚ ነው።
٤- جواز الجماع في ليالي رمضان، ولو كان قبيل طلوع الفجر.
 4ኛ:የረመዷን ለሊቶችን እስከ ሱብሂ ድረስ ወሲባዊ ግንኙነት( ጂማዕ) ማድረግ የሚቻል(የሚፈቀድ) መሆኑ።
📚 المصدر : تيسيرالعلام شرح عمدة الأحكام / للعلامة عبدالله البسام رحمه الله، ج١ ص ٣١٨
📚ምንጭ
📚የዐብደላህ አልበሳም አላህ ይዘንላቸውና
ተይሲሩል ዓላም ሸርሁ ዑምደቱል አህካም
(1/318)

••••••••••••¶•••••••••••
@alfiqhulmuyser
••••••••••••¶•••••••••••
ዒድ ሙባረክ
  تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
كل عام وانتم بخير   عيد مبارك
ቀዷ መክፈል ወይስ ሸዋል መፆም ይቀድማል?

💧የረመዳን ክፍያም(ቀዷም) ሆነ ሌላ የግዴታ ክፍያ (ቀዷ) ፆም እያለብን ሸዋልንም ሆነ ሌላ ማንኛውንም የሱና (ተጨማሪ) ፆም መፆም ነው ያለብን ወይስ ያለብንን የክፍያ ፆም(የቀዷ ፆም)
መክፈል ነው ያለብን????።

💧 ﻗﻀﺎﺀ ﺭﻣﻀﺎﻥ مقدم من التطوع بصيام بشوال
وجاء رجل الى رسول الله
ﻓﻘﺎﻝ :
《ﻳﺎ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺇﻥ ﺃﻣﻲ ﻣﺎﺗﺖ ﻭﻋﻠﻴﻬﺎ ﺻﻮﻡ ﺷﻬﺮ ﺃﻓﺄﻗﻀﻴﻪ ﻋﻨﻬﺎ؟》
ﻗﺎﻝ : ‏( ﻧﻌﻢ ﺩﻳﻦ ﺍﻟﻠﻪ ﺃﺣﻖ ﺃﻥ ﻳﻘﻀﻰ ‏) ﺭﻭﺍﻩ ﺍﻟﺒﺨﺎﺭﻱ ﻭﻣﺴﻠﻢ،.
💧አንድ ሰው ወደ ነብዩ ﷺ
ዘንድ መጣና እናቴ የአንድ ወር ሙሉ ያልፆመችው የግዴታ(የረመዳን) ፆም እያለባት ሞተች እኔ ልክፈልላት? ብሎ ሲጠይቃቸው
ነብዩም ﷺ
አዎ ክፈልላት ያለተከፈለ የአላህ እዳ ከምንም ነገር በፊትና ቅድሚያ መከፈሉ ተገቢና አማራጭ ማይኖረው ግዴታ ነው ብለው።》 መልሰውለታል።
📚ይህን ሀዲስ
📚ኢማሙ ቡኻሪይና ሙስሊም መዝግበውታል።
💧وقال النبي قال الله تعالى في حديث القدسي
《وما تقرب إلي عبدي بشيء احب إلي مما افترضته عليه 》
📚رواه البخا ي
ነብዩﷺ
ሀዲሰልቁይ ላይ እንደገለፁት አላህ እንዲህ አለ ብለዋል
《ባሪያዬ ግዴታ ያደረኩበትን አምልኮ(ዒባዳህ) ከመተግበር የላቀ ወደኔ የሚቃረብበት ትልቅና ወደኔም ተወዳጅ የሆነ የዲን ተግባር የለም።》
📚ይህን ሀዲስ
📚ኢማሙ ቡኻሪይ መዝግበውታል።
💧قال ابن رجب رحمه الله :
《فمن كان عليه قضاء من شهر رمضان فليبدأ بقضائه في شوال فإنه أسرع لبراءة الذمة .》
📚 لطائف المعارف : (٢٢٣
💧ኡብኑ ረጀብ አላህ ይዘንላቸውና አንድ ሰው የረመዳን የክፍያ ፆም(ቀዷ) ካለበት የሸዋልን ፆም ፆሞ ከዛው ያለበትን የረመዳን የቀዷ ክፍያ ይክፈል ወይስ መጀመሪያ በቀጥታ የረመዳንን የቀዷ ክፍያ ይክፈል?ተብለው ተጠይቀው ሲመልሱ:
💧《መጀመሪያ ረመዳን ላይ ያጠፋውን ቁጥር ያህል ቀናት በሸዋል ቀናቶች አስቀድሞ ይክፈልና ቀዳውን ከፍሎ ሲጨርስ የሸዋል ወር ካላለቀ ሸዋልን ስድስት ቀን መፆም ይችላል ብለዋል።》
📚ለጣኢፉል አልመዓሪፍ(223)

በመሆኑም በተለያየ አጋጣሚ ያልፆምነው የረመዳን እዳ ያለብን ወንዶችም ሆን ሴቶች ከሸዋልም ሆነ ከሌሎች የተጨማሪ(ሱና) ፆሞች አስቀድመን ያልፆምነውን የረመዳን እዳ በመክፈል ላይ መጎበዝና መበርታት አለብን።


🔁ሼር
••••••••••••¶•••••••••••
T.me/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
••••••••••••¶•••••••••••
ረመዳንና የስድስቱ የሸዋል ቀናት ምንዳ
ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፡-
" ﻣَﻦْ ﺻَﺎﻡَ ﺭَﻣَﻀَﺎﻥَ ﺛُﻢَّ ﺃَﺗْﺒَﻌَﻪُ ﺳِﺘًّﺎ ﻣِﻦْ ﺷَﻮَّﺍﻝٍ ﻛَﺎﻥَ ﻛَﺼِﻴَﺎﻡِ ﺍﻟﺪَّﻫْﺮِ "
“ረመዳንን ፆሞ ከሸዋል ስድስት ቀን ያስከተለ ልክ አመት እንደፆመ
ነው፡፡” [ሙስሊም፡ 1160]
30 የረመዳን ቀናት + 6 የሸዋል ቀናት = 36 ቀናት
36 x 10 = 360
አላህ በቁርኣን እንዲህ ይላል፡-
﴿ ﻣﻦ ﺟﺎﺀ ﺑﺎﻟﺤﺴﻨﺔ ﻓﻠﻪ ﻋﺸﺮ ﺃﻣﺜﺎﻟﻬﺎ﴾ ﺍﻷﻧﻌﺎﻡ 160 :
“በመልካም ስራ የመጣ ሰው ለእርሱ አስር ብጤዎቿ አሉት፡፡” [አልአንዓም፡
160]
አላህ ለሻለት ሰው የመልካም ስራ ሽልማት ከዚህም በላይ እስከ
- 700 እጥፍ ወይም
- ከዚያም በላይ
ሊሆን ይችላል፡፡ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፡-
) ﻛُﻞُّ ﻋَﻤَﻞِ ﺍﺑْﻦِ ﺁﺩَﻡَ ﻳُﻀَﺎﻋَﻒُ ، ﺍﻟْﺤَﺴَﻨَﺔُ ﻋَﺸْﺮُ ﺃَﻣْﺜَﺎﻟِﻬَﺎ ﺇِﻟَﻰ ﺳَﺒْﻌﻤِﺎﺋَﺔ ﺿِﻌْﻒٍ ، ﻗَﺎﻝَ ﺍﻟﻠﻪُ ﻋَﺰَّ ﻭَﺟَﻞَّ
: ﺇِﻟَّﺎ ﺍﻟﺼَّﻮْﻡَ ، ﻓَﺈِﻧَّﻪُ ﻟِﻲ ، ﻭَﺃَﻧَﺎ ﺃَﺟْﺰِﻱ ﺑِﻪِ ، ﻳَﺪَﻉُ ﺷَﻬْﻮَﺗَﻪُ ﻭَﻃَﻌَﺎﻣَﻪُ ﻣِﻦْ ﺃَﺟْﻠِﻲ ) ﺭﻭﺍﻩ ﻣﺴﻠﻢ
( 1151 .
“እያንዳንዱ የአደም ልጅ (መልካም) ስራ ይታጠፋል፡፡ መልካም ስራ በአስር
አምሳያዎቿ ነው (የምትታሰበው)፣ እስከ 700 እጥፍ ድረስ፡፡ አሸናፊውና
የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፡ “ፆም ሲቀር፡፡ እሱ ለኔ ነው፡፡ እኔ (በተለየ)
እመነዳበታለሁ፡፡ ስሜቱንና ምግቡን ለኔ ሲል ስለተወ፡፡” [ሙስሊም፡ 1151]
ፆም የሶብር ክፍል ነው፡፡ ታጋሾችን በተመለከተ ደግሞ አላህ እንዲህ ይላል፡-
( ﺇﻧﻤﺎ ﻳﻮﻓﻰ ﺍﻟﺼﺎﺑﺮﻭﻥ ﺃﺟﺮﻫﻢ ﺑﻐﻴﺮ ﺣﺴﺎﺏ )
“ታጋሾቹ ምንዳቸውን የሚስሰጡት ያለ ሂሳብ ነው፡፡” [አዝዙመር፡ 10]
ማሳሰቢያ፡-
የሸዋል ስድስቱን ቀናት ከዒድ አልፊጥር በኋላ አስከትሎ መፆሙ በላጭ
ቢሆንም እስከ ወሩ መጨረሻ ድረስ መፆም እንደሚቻል በርካታ ዐሊሞች
ይገልፃሉ፡፡
ለቻለ ሰው በዒድ ቀን ማግስት (ሸዋል 2) መጀመሩም በላጭ ነው።


(Menqul)
http://T.me/የፊቅህትምህርቶች/com.alfiqhulmuyser
2024/04/30 02:50:40
Back to Top
HTML Embed Code: