tg-me.com/Peace1st/7
Last Update:
በአንድ ዘመን የሚኖር አንድ ንጉስ ነበረ። ንጉሱም በሀገሪቷየሚኖሩትን ሰአሊወች አንድ ትዛዝ ያዛቸዋል። እሱም ሰላምን በስዕል እንዲገልፁ ነበር።ሰአሊወቹም የታዘዙትን ለመስራት ተነሱ።ከጥቂት ቀናት በኋላ ስራቸውን ይዘው ወደ ንጉሱ ቀረቡ። ሁሉም በራሱ አገላለፅ ሰላምን ሳሏት።
#አንደኛው ሰአሊ ሰላምን ሲስላት ሰፊ....ለ...ጥ.... ያለ አረንጓዴ..... መስክ ፥መስኩ ላይም ህፃናቶች ሲቦርቁ ሳለ።
#ሁለተኛው ሰአሊ ደግሞ ትልቅ... እንዲሁም ሰፊ....ሰማ..ያ...ዊ.. ሀይቅ በመሳል ሰላምን ገለፃት።
#የሶስተኛው ሰአሊ ሰላምን የገለፀበት መንገድ ከሁለቱ ይለይ ነበር። በጣም ከፍ ያለ ፏፏቴ በሀይል እየተምዘገዘገ ቁልቁል ሲወርድ ይታያል ከስሩ ደግሞ አንድ የድንጋይ አለት ነበር።ሌላው የሚገርመው ደሞ አንዲት እርግብ ከአለቱ ስር ለጥ.... ብላ ተኝታለች
እርግቧከላይ ተንደርድሮ ሚመጣው ፏፏቴ ይነካኛል ብላ ሳታስብ አለቱን ተማምና ተኝታ ነበር
ንጉሱም የሶስተኛውን ሰዐሊ ስዕል ከተመለከተ በኋላ ይሄ በትክክል ሰላምን ይገልፃል ብሎት ሰአሊውን ሸለመው።
የተወደዳቹ የአምላኬ ብሩካን በአሁን ሰአት ብዙዎች የሰላም ትርጉሙ ጠፍቷቸዋል። ሰላምን ለማግኘት የተለያዩ ነገሮችን ያደርጋሉ። ግን ሊያገኟት አልቻሉም ይበልጥ እራሳቸውን ወደተለያዩ ሱሶች እና ድብርት ውስጥ ይከታሉ በዚም እስከ ሞት ድረስ እራሳቸውን ያደርሳሉ። ሰላም ውጪያዊ ብቻ አይደለም ውስጣዊም ነው። የውስጣዊ ሰላማችን ካልተጠበቀ ደሞ በዙሪያችን ለምናያቸው የሰላም ችግሮች መፍትሄ ማግኘት ያቅተናል።
(ዩሐ 14:27) ክርርስቶስ በራሳችን ብቃት እና በአለም ባሉ ነገሮች የማናገኘውን ሰላም ሰቶናል። እሱ የሰጠን ሰላም በሁኔታዎች ላይ ያልተመረኮዘ፥ በማግኘት እና በማጣት ላይ ያልተመሰረተ እሱን በማመናችን ብቻ የተሰጠን እረፍት አለ።
እርግቢቷ የፏፏቴውን ሀይሉን እና ድምፁ ሳያሳስባት እሷን ሳይሆን አለቱን እንደሚመታው አምና ከስሩ ተኝታለች።
እኛም የሰላማችን አለት ክርስቶስ ነው የሚመጣው ማንኛውም ነገር ችግር ቢሆን መከራም ቢሆን ብቻ ህይወታችንን ሊያውክ የሚመጣ እኛን አያገኝም ውሀው አለቱን እንደመታው የሰላማችን ጠሮችም ክርስቶስን ነው ሚያገኙት። ስለዚ
(ኤፌ 2:14) ክርስቶስ ሰላማችን ነው::
🙏 ሰላማቹ በክርስቶስ ይብዛ
ወንጌል ለሁሉም
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFIS4nf6oUcao6PigQ
BY Peace
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/Peace1st/7